ቅዳሜ 13 ኤፕሪል 2013

3ኛ አመ ቱ ተከብሮ ዉሎአል



       


  ዛሬ መጋቢት 5 ቀን 2005 ዓ.ም.ከቀኑ 7፡00 ሰዓት እስከ 12፡00 ሰዓት ድረስ የቆየ በዉይይትና በተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች በአክሱም ሆቴል የዳንኤል ክብረት እይታዎች 3ኛ አመት ተከብሮ ዉሎአል፡፡ በበአሉም ላይ 5 የተለያዩ ሰዎች በሰሩት በጎ ስራዎች በዳንኤል እይታ አንባቢዎች ባገኙት ጥቆማ መሰረት ድምፅ ያገኙ ሲሆን ይህም ሁኔታ በየዓመቱ ቀጣይነት የሚኖረዉ ሲሆን ዋና ዓላማዉም የዛሬዎቹን በጎ አድራጊዎች ካላበረታታን እና እዉቅና ካልሰጠናቸዉ ነገ በጎ መስራት ታሪክ ሆኖ ይቀራል የሚል ስጋት ስላላቸዉ እንደሆነ የዝግጅቱ ባለቤት ዲ.ዳንኤል ክብረት አፅንኦት በመስጠት ተናግረዋል፡፡(እነዚህን ሰዎች ወደ ፊት ከሰፊ ትንታኔ ጋር ይዤ የምቀርብ መሆኔን አለበለዝያም በዳንኤል እይታዎች ላይ ሊቀርብ እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡)


       
የዳንኤል የጥሞራ መድረክ ከአምስት ሚልዮን በላይ አንባቢዎች በላይ ሲኖሩት በዚህ 3 ዓመት ጊዜ ዉስጥ ወደ አራት መቶ ሃያ የሚጠጉ በተለያየ ርእሰ ጉዳዮች ላይ የተፃፉ ሥነ-ፅሁፎች ይገኙበታል፡፡ በመርሃ ግብሩም አዳዲስ ጦማርያን ልምዳቸዉን አካፍለዉበታል፣ ከህብረተሰቡም ጋር ተዋዉቀዉበታል፣ታዳሚዎችም ጥያቆዎችን ሰንዝረዋል፣ አስተያየትም ሰጥተዉበታል፡፡ለጠነሱትም ጥያቄዎች መልሶች ተሰተዉበታል፤ 12፡00 ሰዓት ሲሆን የመርሃግብሩ ፍፃሜ ሆኑዋል፡፡   


ዳንኤል ማን ነዉ? ሥራዎቹስ? ለዚህ ትዉልድ ምን ፋይዳ ይኖረዋል? ከርሱ ምን እንማራለን? … ወዘተ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ወደፊት እንዳስሰዉ ይሁናል፡፡   
 

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...