ሰኞ 11 ሜይ 2026

የስኬት ሚስጢር ምንድን ነው?

 የስኬት ሚስጢር ምንድን ነው?

የስኬት ሚስጥር ለአንዱ የሚሰራው ለሌላው ሊለይ ቢችልም፣ በአብዛኛው ስኬታማ ሰዎች ህይወት ውስጥ የሚታዩ ዋና ዋና ምሰሶዎች አሉ። ስኬት በአንድ ጀምበር የሚገኝ ሳይሆን የብዙ ጥቃቅን ነገሮች ድምር ውጤት ነው።

ጥቂቶቹን ዋና ዋና ነጥቦች እነሆ፦

1. ግልጽ ራዕይና ግብ መኖር

የምትፈልገውን ነገር በግልጽ ማወቅ የስኬት መጀመሪያ ነው። ግብ የሌለው ሰው መድረሻ እንደሌለው መርከብ ነው። የምትፈልገውን ነገር በዝርዝር አስቀምጥ፤ ምክንያቱም በግልጽ የታወቀ ግብ ግማሽ መንገድ እንደመጓዝ ይቆጠራል።

 2. ራስን መግዛትና ወጥነት (Consistency)

ብዙ ጊዜ ስኬት የሚገኘው ከችሎታ በላይ በጽናትና ሁልጊዜም ባለመታከት በስራ ላይ በመገኘት ነው። ስሜትህ ሲነሳሳ ብቻ ሳይሆን፣ ደክሞህም ቢሆን መደረግ ያለበትን ነገር በሰዓቱ የማከናወን ልምድ (Self-discipline) ወሳኝ ነው።

3. ለለውጥና ለትምህርት ዝግጁ መሆን

ዓለም በየቀኑ እየተቀየረች ነው። ስኬታማ ሰዎች መማርን በጭራሽ አያቆሙም። ከስህተታቸው ይማራሉ፣ አዳዲስ ክህሎቶችን ያዳብራሉ፣ እንዲሁም ለውጥን እንደ እድል እንጂ እንደ ስጋት አያዩትም።

4. ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም

ጊዜ የማይተካ ሀብት ነው። ስኬታማ ሰዎች ጊዜያቸውን ለሚረቡና ለዋና ዋና ግቦቻቸው ቅድሚያ በመስጠት ይጠቀሙበታል። "አስቸኳይ" በሆኑ ነገሮች ሳይሆን "አስፈላጊ" በሆኑ ነገሮች ላይ ማተኮር ይገባል።

5. መልካም ስነ-ምግባርና ግንኙነት

ብቻውን ሮጦ ስኬት ላይ የሚደርስ የለም። ከሰዎች ጋር በሚኖርህ ግንኙነት ታማኝ፣ አክባሪና ተባባሪ መሆን ለስኬትህ ትልቅ በር ይከፍታል። የሰዎችን እምነት ማግኘት ከገንዘብ በላይ ዋጋ አለው።

ባጭሩ፦ ስኬት ማለት በትክክለኛ አላማ ላይ ተመስርቶ፣ ሳይታክቱ በርትቶ መስራት እና በሂደቱ ውስጥ ከሚገጥሙ ፈተናዎች እየተማሩ ወደፊት መጓዝ ነው።

በግል ህይወታችን ላይ ትንሽ ቆይታ አድርገን ስኬትን እንመልከት፤

ቅዳሜ 9 ሜይ 2026

ልደቷ ለእመቤታችን

 ልደቷ ለእመቤታችን

የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት (ግንቦት 1) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እጅግ ደምቆ ከሚከበሩ በዓላት አንዱ ነው። ይህ በዓል ከታሪካዊ አመጣጡ እስከ ዛሬው የአከባበር ሥርዓት ድረስ ያለው ሂደት እንደሚከተለው ይቀርባል፦

1.      የታሪኩ መጀመሪያ (የእመቤታችን መወለድ)

እንደ ቤተክርስቲያን ትውፊትና እንደ "ነገረ ማርያም" አስተምህሮ፣ እመቤታችን የተወለደችው ከቅዱስ ኢያቄም እና ከቅድስት ሐና ነው።

ü  ተስፋው፦ ወላጆቿ ደግና እግዚአብሔርን የሚፈሩ ቢሆኑም ልጅ ስላልነበራቸው በሰዎች ይናቁ ነበር።

 "ፍሬ ከሰጠኸን ለእግዚአብሔር አገልግሎት እንሰጣለን" ብለው ይጸልዩ ነበር።

ü  ተአምራዊው ጽንሰት፦ እግዚአብሔር ጸሎታቸውን ሰምቶ በነሐሴ 7 ቀን ተጸነሰች።

ü  ልደቱ፦ በዘጠነኛው ወር በዛሬዋ ዕለት ግንቦት 1 ቀን በሊባኖስ ተራራ ተወለደች። ይህ ልደት "የሰው ልጅ የድኅነት መጀመሪያ" ተብሎ ይታመናል።

 2. የበዓሉ አከባበር ታሪካዊ አመጣጥ

የልደቷ በዓል በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ይከበር የነበረ ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ በስፋትና በይፋ እንዲከበር ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ዓፄ ዘርዐ ያዕቆብ (15ኛው ክፍለ ዘመን) ናቸው።ንጉሡ "መጽሐፈ ሥርዓት" እና "መጽሐፈ ማርያም" በሚባሉ ድርሳናት የበዓላቱን አከባበር ሥርዓት ደንግገዋል። በተለይም ግንቦት 1 ቀን የእመቤታችን ልደት መሆኑ ተረጋግጦ በታላቅ ድምቀት እንዲከበር አዘዋል።

ሐሙስ 26 ፌብሩዋሪ 2026

እንዴት ልጆችን በሁለንተናዊ መስክ እናሳድግ? ክፍል 2

 

ባለፈዉ በክፍል አንድ በይደር እንዳቆየነዉ ክፍል ሁለትን እነሆ ብለናል፤ ክፍል አንድን ያላነበባችሁ ወደዚህኛዉ ንባብ ከመሸጋገራችሁ በፊት ክፍል አንድን እንድታነቡት ይመከራል፡፡

ልጆችን እንዴት እናስተምር/ምንስ እናስተምራቸዉ?

1.     ልጆች እንደመሆናቸዉ እና በተለያየ እድሜ ክልል እንደመሆናቸዉ ቅርበት ይፈልጋሉና በቅርበት ሆነን ልናስተምራቸዉ ይገባናል፤ (የሙሴ እናት በግብፅ ምድር ለልጇ ሞግዚት ሆና ስታሳድገዉ ስለ ሕዝቧ እና ስለ አምላኳ ስታስተምሩ በቅርበት ሆና ነበር፤ እኛም በሥጋ ላልወለድናቸዉ ልጆች የመንፈሳዊ እዉቀት ወላጆች እንደመሆናችን ስለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ስለእስራኤል አምላክ ልንነግራቸዉ ይገባል፡፡ (የሙሴ እናት ይህንን ብቻ አይደለም ያደረገችዉ በግብጽ ጣኦት አምልኮ እንዳይወሰድ አድርጋም ታስተምረዉ ነበር፡፡ እኛም ስለ ተዋህዶ ትክክለኝነት ስለ ሌሎችም ስህተት ልናስተምራቸዉ ልዩነቶችንም በእድሜያቸዉ መጥነን ልናስተምራቸዉ ይገባል፡፡)

2.     መንፈሳዊ ተግባራትን በማለማመድ ልናስተምራቸዉ ይገባል፤ (ጸሎትን፣ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብን፣ ገድላትን፣ ስንክሳርን፣ የቅዱሳንን ነገር፣ ወዘተ )

3.     ስብእናን በማሳደግ፤ ልብ፡- በጎ መዝገብን የሚያወጣ ራሱን የሚገዛ፣ የማይቆጣ እንዲሆን ማለማመድ አለብን፡፡

ü  ምኞት፡- በጎ የሆኑትን ከክፉ መለየት እንዲችል ማሳወቅ፡፡

ü  አመክንዮ፡- የዚህን ዓለም ብልጭልጭ ነገሮችን ሳይሆን አስቀድሞ ጽድቁንና መንግስቱን እንዲሻ ማድረግ (ዮቶር ሙሴን መክሮ እንዳሳደገ እኛም መጥነን እንዳይሰለቹ በማድረግ ልናስተምራቸዉ ይገባል)

4.     እዉቀትን በመስጠት፡- በአስኳላዉ የሚሰጠዉን፣ በዓለም ያለዉን የሚያዩትን የሚሰሙትን በማንሳት/በመጥቀስ ልናስተምራቸዉ

ማክሰኞ 13 ጃንዋሪ 2026

እንዴት ልጆችን በሁለንተናዊ መስክ እናሳድግ?

መግቢያ 
 ማሳደግ የወላጅ ሥራ/ሚና ነዉ፤
 ወላጅ ማለት
  የሥጋ ወላጅ (እናት እና አባት) 
  መንፈሳዊ ወላጅ (መምህረ ንሰሐ፣ መምህራነ ወንጌል፣ ልጆችን በእለተ ሰንበት የሚያስተምሩ) 
  የእዉቀት ወላጅ (በትምህርት ገበታ ላይ የሚገኙ መምህራኖች)
  በእድሜ የገፉ ሰዎች ወላጅነት (በሰፈር፣ በጎረቤት)
  የአከባቢ ሰዎች
  ሞግዚቶች (በቤት ዉስጥ እና ከቤት ዉጪ)
  ቴክኖሎጂ የወላጅነት ድርሻን እንደ ወላጅ ሆኖ ፈቃድ ተሰጥቶን ሚናችንን እየቀማን ያለ ወላጅ

‹‹ ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራዉ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይለም›› መጽሐፈ ምሳሌ 22÷6

ü  ኦርቶዶክሳዊ ልጆች ለማሳደግ መጀመሪያ ወላጆች ኦርቶዶክሳዊ መሆን አለባቸዉ፤

ü  ስለልጆች ስናስብ ከወላጆች ስብዕና

ዓርብ 30 ሜይ 2025

የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም

 የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም 

(በዲ/ ብርሃኑ አድማስ)


አፍጣኒተ ረድኤት ማርያም በጊዜ  ምንዳቤ ወአጸባ ለዐይን እምቀራንባ፤ አንቲ ውእቱ ረዳኢተ ያዕቆብ በቤተ ላባ፤ በኩሉ ኅሊናሃ ወበኩሉ አልባባ፤ዘኢታፈቅረኪ ነፍስ ትሠሮ እምሕዝባ፡፡

 የነገረ ማርያም ሊቅ(Marian Doctor) እየተባለ የሚጠራው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ እመቤታችንን በብዙ ምሳሌ እየመሰለ፣ እየተረጎመና እያመሰጠረ ብዙ ጊዜ አመስግኗታል፡፡ ምንም እንኳን እኛ የምናውቀው የምስጋና ድርሰቱ ለጸሎት የምንጠቀምበት ውዳሴ ማርያም ቢሆንም ከትርጓሜና ከስብከቶቹ ውጪ ከሦስት ሚሊዮን በላይ ስንኝ ያላቸው የምስጋና ድርሰቶችን(Hymns) መድረሱን ታሪክ ጸሐፊው ሶዝመን መዝግቦልናል፡፡ ከነዚህ የምስጋና ድርሰቶቹ መካከልም ‹‹በእንተ ልደት››(On Nativity) እና ‹‹በእንተ ቤተ ክርስቲያን›› (On the Church) በተባሉ ትልልቅ ድርሰቶቹም እመቤታችንን ደጋግሞ ያመሰግናታል፡፡

በተጠቀሱት ሁለቱም ድርሰቶቹ እመቤታችንን ለማመስገን ከተጠቀመባቸው ምሳሌዎች ውስጥ አንዱ "ዐይን" ነው፡፡ ሊቁ ስለ ቤተክርስቲያን በደረሰው የምስጋና መዝሙሩ ውስጥ እንዲህ ይላታል፤ ‹‹ዐይን ጥርት የሚለው ከፀሐይ ብርሃን ጋር ተዋሕዶ ከብርታቷ ኃይልን ከውበቷም ነጸብራቅን ሲቀበል ነው፤ በዚህ ጊዜ በግለቷ ይሰነገላል፣ያበራል፤ በውበቷም ያጌጣል፤ልክ እንደዚሁ ማርያም ዐይን ናት፤ብርሃን (ጌታ) ማደሪያውን በእርሷ አዘጋጀና መንፈሷን ጽሩይ አደረገ፤አሳቦቿን አጠራ፣ኅሊናዋንም ንጹሕ አደረገ፤የድንግልናዋንም ክብር አበራው ›› /Hymns on the Church, 36, 1-2/

ሊቁ በዚሁ ድርሰቱ ውስጥ ሌላ ቦታ ላይ ደግሞ፤ለዚህ ዓለም ሁለት ዐይኖች ተሰጡት፤ ማየት ያልተቻላት የግራ ዐይን ሔዋን ስትሆን፣ የምታበራው የቀኝ ዐይን ደግሞ (እመቤታችን) ማርያም ናት፡፡በማታየው በጨለማዋ ዐይን ምክንያት መላው ዓለም ጨለመ፤ ስለዚህም ሰዎች በጨለማ ጥላ ውስጥ ሆነው ሲዳብሱ ያገኙት ሁሉ አምላክ ሐሰቱም እውነት መሰላቸው፡፡ነገር ግን ዓለም እንደገና በሌላ ዐይኑ ባበራና (ባየና) ሰማያዊው ብርሃንም በዚች ዐይን ሰሌዳ ውስጥ ባንጸባረቀ ጊዜ ሰዎችም ቀድሞ ያገኙትን(ያመለኩትን) የኑሮአቸው ውድቀት(የባሕርያቸው መጎስቆል) መሆኑን ተረድተው ወደ ማንነታቸው ተመለሱ (አንድነታቸውን አገኙ)›› ይላል /Ibid, 37, 5-7/::

 በዚህ መሠረት የእመቤታችን ልደት ዓለም ማየት የጀመረበት

ማክሰኞ 22 ኤፕሪል 2025

የጋብቻ እና ቤተሰባዊ ሕይወት #2

 የሰናፍጭ ቅንጣት |የጋብቻ እና ቤተሰባዊ ትምህርት ክፍል 2


የጋብቻ እና ቤተሰባዊ ሕይወት

በዚህ ክፍል የጋብቻን ትርጉም

የጋብቻን ዓላማ

በጋብቻ ዉስጥ ስላሉ እዉነታዎች

ዓለማዊ እና መንፈሳዊ ጋብቻ ልዩነታቸዉ ምንድን ነዉ 

 ... የሚሉትና ሌሎችም ይዳሰሱበታል፡፡

ሐሙስ 20 ማርች 2025

ክርስቲያናዊ ሕይወት እና ሥነምግባር

 

ክርስቲያናዊ ሕይወት እና ሥነምግባር

ሥነ ምግባር፡- ማለት ደግነት፣ በጎነት፣ መልካም ጠባይ ማለት ሲሆን ክርስቲያን የሚለው ቃል ሲጨመርበት ደግሞ የተሟላና የተለየ ያደርገዋል፡፡ መልካም ጠባይ ማንም ሰው ሊኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን የተሟላ ዘላቂና የሁልጊዜ ሆኖም ለሰማያዊ መንግሥት የሚያበቃው በክርስትና እምነት ሲኖሩ ነው፡፡

ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር፡- በምድር እያለን ሰማያዊ ኑሮ ኖረን ለሰማያዊ መንግሥት የምንበቃበት ሕይወት ነው፡፡ ሰውን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ማስደሰት ነውና፡፡ በመሆኑም ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር በሚከተሉት ሕግጋት ሊለካ ይችላል፡፡

1. ሕገ እግዚአብሔር

መጀመሪያውና ዋነኛው የክርስቲያን ሥነ ምግባር መለኪያው ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ አንድ ሰው ምናልባትም ሕይወቱ በሰው ፊት ሲታይ የሚያስደስት በአፍአ ያለው ጠባዩ እንከን የማይወጣለት ሊሆን ይችላል፡፡ በሕገ እግዚአብሔር ተመዝኖ ካላለፈ ዋጋ የለውም። በሰው ፊት መልካም ሆኖ የሚታይ ምግባር እግዚአብሔርን ሊያስደስት ያስፈልጋል፡፡ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ፡፡ኤፌሶን.66

ፈሪሳውያን ከእነርሱ ውጪ የሆነውን ሁሉ የናቁ ያለእኛ ሕገ እግዚአብሔርን አክባሪ ከእኛም በላይ ጻድቅ የለም ባዮች ነበሩ፡፡ነገር ግን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግብዞችና ሥራቸው ሁሉ ከንቱ እንደሆነ ነገራቸው፡፡ እንዲያውም ጽድቃችሁ ከጻፎችና ከፈሪሳውያን ጽድቅ ካልበለጠ ወደ መንግሥተ ሰማያት ከቶ አትገቡም ማቴ.520 በማለት ደቀ መዛሙርቱን አስጠነቀቀ፡፡

እንዲያውም ከእነርሱ እርሾ /ትምህርት/ እንዲጠበቁ አስጠነቀቃቸው፡፡ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁማቴ.166 አለ፡፡

ሐሙስ 6 ማርች 2025

የጋብቻ እና ቤተሰባዊ ሕይወት #1

 የሰናፍጭ ቅንጣት |Part 1 የጋብቻ እና ቤተሰባዊ ሕይወት ትምህርት

የጋብቻ እና ቤተሰባዊ ሕይወት

በዚህ ክፍል የጋብቻን ትርጉም

የጋብቻን ዓላማ

በጋብቻ ዉስጥ ስላሉ እዉነታዎች

ዓለማዊ እና መንፈሳዊ ጋብቻ ልዩነታቸዉ ምንድን ነዉ 

 ... የሚሉትና ሌሎችም ይዳሰሱበታል፡፡

 


ማክሰኞ 3 ዲሴምበር 2024

ትቶ እና ችሎ

 ትቶ እና ችሎ

ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ


በደረሰ ረታ

ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። በምክራቸውም ይሁን በሕይወታቸው ያስተማሩን ይህንን ነው። በዘመናቸው የመጡትን ፈተናዎች በመተው እና በመቻል ነበረ ያሳለፉት። የሚተወውም ሆነ የሚቻለው ነገር እንዲህ ቀላል ሆኖ አልነበረም። ሁሉን በሚችል/በሚያስችል በአምላካቸው ቸርነት ችለውት እንጂ። የአባታችን በረከታቸው በሁላችን ላይ ይደርብን።
የቤተእምነት አባቶች እንደ የ ደረጃቸው ይህ አይነት አስተዋይነት በመሪነታቸው ወቅት ይጠበቅባቸዋል። መንጋውን ለመጠበቅም ይሁን ለአስተዳደራዊ ውሳኔ ሰጪነታቸው ይህን መንገድ መከተል ግድ ነው።
በመንግሥት ደረጃም ያሉ ባለስልጣናት (የክልልም ሆነ የፌዴራል) ሕዝባቸውን ሲያስተዳድሩ፣ ውሳኔ ሲሰጡ፣ ግጭቶችን ሲፈቱ፣ ይህ የሚጠበቅባቸው ጉዳይ ነው።
የተቋማት አስተዳዳሪዎች በየእርከናቸው ሰራተኞቻቸውን ሲመሩ እና ሲያስተዳድሩ፣ ውሳኔ ሲያሳልፉ እና ልዩነቶችን የመፍትሔ አቅጣጫ ሲጠቁሙ በማስተዋል ሊሆን እንደሚገባ አስተማሪ ተግባር የሚሻ ቃል ነው ትቶ እና ችሎ መኖር።
ሰው ከብቸኝነት ወጥቶ ሁለት እና ከዚያ በላይ ሆኖ ሲኖር፣ በትዳር ሲጣመር፣ የጋራ ዓላማ ካለው ወዘተ ሁሌም ሁሉም ወገን አንድ ነገር ያስባል፤ በአንድ ነገር ላይ በእኩል ያምናል ብሎ መጠበቅ የዋህነት ነው።
አብሮ ለመኖር፣ የጀመሩትን ለማስቀጠል፣ ልዩነቶችን ለማጥበብ፣ ግጭቶችን ለማስቀረት አማራጭ ከሌላቸው መፍትሔዎች አንዱ ትቶ እና ችሎ መኖር ነው።
ትቶ እና ችሎ ሲባል የምንተወው እና የምንችለው ነገር የማይጠቅም እና የሚቻል ሆኖ አይደለም። ነገር ግን ሁለቱም ከአብሮነት ስለማይበልጡ እንጂ። አንድም በማጣት ውስጥ ማግኘት ስላለ እንጂ። አንድም በዚህ የተነሳ የምናገኘው ከምናጣው ነገር ስለማይበልጥ እንጂ።
በዓለም ላይ መንግሥታት ሆኑ ሁለት ተደራዳሪዎች ችግሮችን የሚፈቱት ወደ አንድ የሚመጡት win win በሆነ መንገድ ነው። win win ሲባል ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት መንገድ ነው። አሸናፊነት ስንል ሁሌም ማግኘት ማጣት የሌለበት ማለታችን አይደለም። የተወሰነ ሰጥት የተወሰነውን ተቀብሎ፤ የሆነውን ነገር እየተወ የሆነለትን አስከብሮ መሄድ እንጂ።
ለምሳሌ በትዳር ውስጥ እውነቱን ከተነጋገርን አብዛኛውን ጊዜ ከምንግባባበት የማንግባባበት ይበልጣል። ምክንያቱ ግን ስለምንጠላላ አይደለም። ከሁለት ዓለም፣ ከሁለት ቤተሰብ የአስተዳደግ ሁኔታ ውስጥ፣ ከተለያየ ልማድ እና አስተሳሰብ ካለው ማኀበረሰብ ውስጥ፣ ከተለያየ አመለካከት እና አረዳድ ውስጥ ስለመጣን እንጂ።
በየተቋማቱ በአመራር ደረጃ ላይ ያሉ ከሚመሯቸው እና ከሚያስተዳድሯቸው ጋር የሐሳብ ልዩነት ሊፈጠር ይችላል። ነገር ግን ልዩነትን በተለመደ ቋንቋ በጠረጴዛ ዙሪያ መፍታት ይጠበቅባቸዋል። (በጠረጴዛ ዙሪያ ሲባል ጠረጴዛ ችግሩን ይፈታዋል ማለት ሳይሆን በአንድ ጉዳይ ላይ ወደ አንድ ነጥብ ላይ መስማማትን መግባባትን ለማመላከት ነው።) በጠረጴዛ ዙሪያ ብቻ መሰባሰብ ችግር መፍታት እንደማይችሉ ዓለም ላይ የተከናወኑ የጠረጴዛ ውይይቶች ማሳያ ናቸው።
በጠረጴዛ ዙሪያ ለውይይት የሚቀመጡ ወገኖች ሊሸነፉበት የሚገቡ ነገሮች እንዳሉ አምነው መቀመጥ ይኖርባቸዋል። ይህንንም ሲያደርጉ ከበስተጀርባ የሚመሩትን ሕዝብ (ሰራተኛ ) ጥቅምና እና ጉዳት ከግምት ውስጥ ሊያስገቡ ይገባል።
እንደዚህ አይነቱ ልዩነት ጤናማ ነው። ከሁለት የሚወጣ አንድ ጥሩ እና ጠንካራ ነገር ስለሚገኝ። ይኽ እስኪሆን ደግሞ የሚያለያየንን ጉዳይ በመተው እና በመቻል ማሳለፍ ይጠበቅብናል። እኔ ብቻ የበላይ ልሁን እኔ ብቻ ላሸንፍ የምንል ከሆነ በዚህም መካከል በሚፈጠር አለመግባባት ከምናገኘው/ልናስከብር ወይም ልናስፈጽም ከምንችለው በላይ እናጣለን።
ስለዚህ ነገሮችን መቋጨት ያለብን በሰጥቶ መቀበል መርህ መሆን አለበት። ይህ መርህ ሁለቱንም ወገን አሸናፊ ያደርጋል።
ካልሆነስ ነው?
አያድርግብንና ከሆነ ምላሹ የከፋ ነው። አንድነት ይከፈላል፣ ትዳር ይበተናል፣ ቤተሰብ ይፈርሳል፣ ልጆች ወላጅ (እናት/አባት) አልባ ይሆናሉ፣ ጠንካራ የነበረው የኑሮ ደረጃ ይናጋል፣ አገር ማህበረሰብ ዘመድ አዝማድ መሠረቱ ይናጋል።
በጥቂት የቃላት ጦርነት የተጀመረ አለመግባባት ነፍጥ አስመዝዞ ጦርነት ሊያስከትል ይችላል። ጸብ ይፈጠራል። ሥራ ይበደላል። ኢኮኖሚው ይናጋል። የሰው አኗኗር ይበላሻል። ሕይወት ይቀጠፋል። ንብረት ይወድማል። አካል ይጎድላል። እንደዚህ ሲሆን ሊተመን የማይችል ኪሳራ ይደርሳል።
መሰል ችግሮችን መፍታት የሚቻለው በጥልቅ አስተዋይነት እና በበሳል አመራርነት ነው። በሳል አመራርነት እኔ ይድላኝ፣ እኔ ያልኩት ይሁን፣ እኔ ብቻ ትክክል ነኝ፣ ወዘተ ሳይሆን የሚለው በመሸነፍ ለማሸነፍ ከእኔ ይቅር በማለት እያወቀ ይተዋል። ይሸነፋልም።
በትዳር ውስጥ ለሚከሰቱ ልዩነቶች በጎ አስተዋጽኦ ያላቸው ሰዎች እንዳሉት ሁሉ ተግባራቸው ከሰይጣን የሚብሱ አሉ። በሰው ቁስል እንጨት እየቆሰቆሱ የራሳቸውን የሚኖሩ ነገር ግን በሌላው ላይ ከዳር ሆነው የሚፈርዱ አሉ። ልዩነቶቻቸውን በማስፋት፣ ግጭታቸውን በማጉላት እርባና ቢስ የሆነ ፍርድ የሚሰጡ አሉ።
አጀማመሩ ትንሺ የሚመስል አፀፋው ግን ከባድ የሆነ ችግር ይዞ ይመጣል። የስነልቦና ቀውስ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ፣ ወዘተ ይዞ ይመጣል። ስለዚህ ሁሉም ሰው ከእንዲዚህ አይነት ክስተት ከሚመጣ ጉዳት ራሱን ለመታደግ አስቀድሞ የሥነልቦና ዝግጅት ማድረግ ይጠበቅበታል። ደግ አሳቢ መስለው የተለኮሰው ላይ ቤንዚን የሚረጩ እና የሚያቀጣጥሉትን በንቃት መከታተልና ሊከላከላቸው ይገባል።
እንዲህ አይነት ተግባራት በአገራችን እንኳን በፖለቲካው፣ በየ ቤተ እምነቱ፣ በትዳር ውስጥ፣ ወዘተ ክስተቶችን መታዘብ ከጀመርን ከረምረም ብለናል። አሁንም ለነዚህ ተግባራት የሚተውን ትቶ የሚቻለውን ችሎ በጠረጴዛ ዙሪያ በንግግር መፍታት የሰጥቶ መቀበልን መርህን መከተል ግድ ነው። ካልሆነ ውጤቱ ብዙ ዋጋ ያስከፍለናል።
ሁላችንንም እግዚአብሔር ይርዳን፤ ያጋጠሙንን ችግሮች የምንተውበትን እና የምንችልበትን ጸጋ ያድለን።
ይቆየን።

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

የስኬት ሚስጢር ምንድን ነው?

  የስኬት ሚስጢር ምንድን ነው ? የስኬት ሚስጥር ለአንዱ የሚሰራው ለሌላው ሊለይ ቢችልም፣ በአብዛኛው ስኬታማ ሰዎች ህይወት ውስጥ የሚታዩ ዋና ዋና ምሰሶዎች አሉ። ስኬት በአንድ ጀምበ...