ሰኞ 16 ዲሴምበር 2019

የጊዜ አጠቃቀም


የጊዜ አጠቃቀም


መግቢያ

ስኬታማ የጊዜ አጠቃቀም ያዳበረ ሰራተኛም ሆነ ግለሰብ ጊዜዉን በመርሃግብር እና በዕቅድ ይመራል፤ ይህ ሰዉ ህይወቱን የሚመራዉ በዕድል ሳይሆን ራሱ ነዉ፡፡ ስለዚህ ይህንን ዶክመንት ማዘጋጀት ግድ ሆኗል፡፡

ጊዜ -

በቀን 24 ሰዓት

በሳምንት 7 ቀን

በወር 30 ቀን

በዓመት 52 ሳምንት/ 365 ቀናት/ ብለን የምንጠራዉ ማለት ነዉ፤

ጊዜ ከሁሉ ነገር በላይ እጅግ የሚያስፈልገን ነገር ሆኖ ሳለ ከሁሉ ነገር በላይ በተበላሸ ሁኔታ የምንጠቀምበት ነገር ነዉ፤

ዊሊያም ፔን

                                    ዓላማ -

v የተቋማትን ፣አልያም የአገራችንን፣ ከዚያም አልፎ የየራሳችንን፣ ወዘተ … “የተለጠጠእቅድ ለማሳካት ዋነኛ ሃብት ጊዜ በመሆኑ ጊዜያችንን በመጠቀም ዉጤትን እንድናመጣ ግብን እንድናሳካ ግንዛቤ ለመፍጠር ነዉ፡፡


 የጊዜ አስፈላጊነት (ጥቅም)


Ø  ለመዉጣት ለመግባታችን የምንጠቀምበት

Ø  በመዉጣት በመግባታችን ዉስጥ የምናከናዉናቸዉን ነገሮች የምንፈፅምበት መሣሪያ

የአንድ ዓመት ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ክፍሉን የደገመን ተማሪ ጠይቀዉ

 የአንድን ሰዓት ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ለመገናኘት የተቀጣጠሩ ትኩስ ፍቅረኞችን ጠይቃቸዉ

የአንድን ደቂቃ ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ አዉቶቡስ ለትንሽ ያመለጠዉን ሰዉ ጠይቀዉ

v  ያለ በቂ ምክንያት፣ ከአቅማችን በታች በሆነ ጉዳይ ከሥራ ላይ የቀረንባቸዉ ቀናት ምን ያህል ግባችን ላይ ተፅዕኖ እንደፈጠሩ እንመልከት፤

የአንድን ሰከንድ ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ከአደጋ ለጥቂት ያመለጠን ሰዉ ጠይቀዉ

የጊዜ ባህርያት


ü  አንዴ ካለፈ በፍፁም ተመልሶ አይመጣም፣

ü  ለሚጠቀምበትም ሆነ ለማይጠቀምበት እኩል ይሰጣል ነገር ግን እኩል ዋጋ የላቸዉም፣

ü  በብዙ እድሎች የተሞላ ሃብት ነዉ፣

ü  ነፃ ስጦታ እንደመሆኑ መጠን በትርፋማነት ለመጠቀም ግን በደንብ ማሰብንና ዋጋ መክፈልን ይጠይቃል፣

ü  ጊዜ ጨካኝ ነዉ ላልተጠቀሙበት ሰወች ምህረትንና ሁለተኛ ዕድልን አይሰጥም፡፡

ሰወች ለምን ጊዜአቸዉን በአግባቡ አይጠቀሙም?

ü  ግድየለሽ/ቸልተኝነት / ዳተኝነት አመለካከት

ü  የሞራል ዉድቀት

ü  በህይወታችን ግብ እና አላማ ስለሌለን

ü  መዘናጋት/ ራስን መዋሸት/ ያለሰሩትን ሰራሁ፣ ያልጀመሩትን ጨረስኩ፣ጎበዝ ነኝ፣ ወዘተ ችግር ስላለብን

ü  የሥራን ትርጉም አለማወቅ / የሰራነዉ በቂ ይመስለናል/

ü  ማንነታችን /አስተዳደጋችን/ማህበረሰባችን/ የሥራን ዋጋ እየቀነሰዉ መምጣት/በአቋራጭ መበልፀግ/

ü  ለማህበረሰባችን እና ለራሳችን የሚረባን ነገር በመትከል አሻራችንን ትተን ለማለፍ ዝግጅት ማጣት

ü  ሥራን ለነገ ማሳደር እንደምንችል ማወቃችን (መጥፎ ባህል)

ü  ሥራን በዋናነት የእኔ ነዉ ብሎ አምኖ አለመቀበል


ጊዜአችን እንዴት እና በምን ያልፋል?

ጥናቶች እንደሚሉት (ጥናቱ የሁሉንም አዋዋል እንደማይወክል ግምት ዉስጥ ይግባ)

ü  8.5 ሰዓታት በእንቅልፍ

ü  1 ሰዓት ራስን በመንከባከብ

ü  2.5 ሰዓታት እንደ ፅዳት ዓይነት የቤት ዉስጥ ሥራን በመስራት

ü  8.5 ሰዓታትን በሥራ ወይም በትምህርት ቤት

ü  3 ሰዓታትን ለወዳጆቻቸዉ እንክብካቤን በመስጠት

እኛስ?

የጊዜን አያያዝ ጥበብ ለመገንዘብ ከመሞከራችን በፊት ምን እናድርግ?

ü  ራሳችንን የመገንዘብ ጉዞ መጀመር አለብን

v  ማን ነኝ

v  የት ነዉ ያለሁት

v  ምን ማድረግ ነዉ የምፈልገዉ

v  ይህንን ለማከናወን የፈለኩት ነገር ለመፈፀም ምን ያህል ጊዜ አለኝ

v  ሁኔታዉን ለማድረግ ምን ማድረግ አለብኝ

v  ከየት ልጀምር

v  ብዙም ሳይቆይ ጊዜዬን እንዴት ልጠቀም

ወደሚለዉ ቁልፍ ጥያቄ መድረሳችን የማይቀር ነዉ፡፡

እነዚህ ጥያቄዎች መጀመር ያለብንን ነገር እንድንለይ ልባችንን ያነቃቃል፤

ü  ጊዜን ከየት ማምጣት እንዳለብን መገንዘብ

ጊዜ ለማግኘት የትኛዉን ተግባሬን በማቆም ለአስፈላጊዉ ነገር ጊዜ ልፍጠርለት (ቁልፍ ነገር ነዉ) በሥራ ሰዓት ጡል እያልን የምንሄድባቸዉን መቀነስ


ጊዜአችንን እንዴት እንጠቀም?

ü  በአግባቡ (ያለ አግባብ መጠቀም ችግር ስላለዉ)/ከአግባብ በላይ/ከአግባብ በታች

ü  ከአግባብ በላይ መጠቀም ጭንቀት ድካም፣ የጤና ችግር፣ያመጣል

ü  ከአግባብ በታች መጠቀም ያስቀመጥነዉ ግብ እና ዓላማ እንዳናሳካ ያደርገናል

ü  የጊዜን መጠን በማወቅበጀትማዉጣት ፣መቆጣጠር እና መጠቀም

ü  ጊዜዬን በሚገባ እንዳልጠቀም ያደረገኝን የግሌን ችግር መለየት


ሰወች ጊዜአቸዉን እንዴት ነዉ እየተጠቀሙ ያሉት?

1)    እንደ አደጋ ጊዜ ተጠሪ (ምላሽ ብቻ መስጠት)

ü  አደጋዎች እዚህ እና እዚያ ሲፈጠሩ ምላሽ የሚሰጡ ነገር ግን ቁጭ ብሎ ጊዜዉን በሚገባ ለመጠቀም የሚረዳዉን ዕቅድ ለማዉጣትጊዜየሌላቸዉ

2)    ለማስደሰት የሚሰሩ

ü  እምቢለማለት ያለመቻል ችግር የተበተባቸዉ ለጠየቃቸዉ ሁሉእሺበማለት ቃል የሚገቡ፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰዉ ተጠይቆ እምቢ ከሚል መደበቁን ይመርጣል፡፡

3)    ጊዜ እንዳላቸዉ የሚያስቡ

ü  ሁሉንም ነገር የሚደርስበት መስሎ የሚታየዉ

ü  እዉቅና ሊያሰጠዉ ለሚችል ሥራ ብቻ ጊዜዉን የሚሰጥ

ü  ሲመቸዉ ወይምሙዱንሲያገኝ ብቻ የሚሰራ

ü  የጀመረዉን ነገር ለሌሎች ለማስተላለፍም ሆነ ለማቋረጥ ትንሽእንቅፋትየሚበቃዉ

ü  ህይወቱ በመላምት የተሞላ /ሊሆን ይችላል፣ መሰለኝ፣ ሳይሆን አይቀርም፣ …/ የሚያበዛ እርግጠኛ ያልሆነ ሰዉ፤

4)    ማህበረሰብ ተኮር

ü  ከሰዉ ጋር ሰፊ እና ፈጣን ተግባቦት ያላቸዉ

ü  የንግግር እና የመግባባት ችሎታ ያላቸዉ

ü  ሁሉም ቦታ ላይ ያሉ

ü  አንድ የሥራ ጊዜ በማህበራዊ ነክ ጉዳዮች ማሳለፍን እንደ ችግር የማያይ ዋና የሥራዉ አካል መስሎ የሚታየዉ

ü  ይህንን ዓይነት ሰወች አንዳንድ አለቆች /አሰሪዎች/ ወይም የሥራ ባልደረቦች ከዚህ እዚያ ሲል መዋሉን እንደ ታታሪ ሰራተኛ ይቆጥሩለታል፡፡

5)    የሰዎችን የሥራ ሰዓት የሚቆጣጠሩ

እኛስ?

ü  ራሳችንን በየትኛዉ ቦታ ላይ አገኘነዉ

ü  ካላገኘነዉ ራሳችንን በምን ዓይነት ሁኔታ አገኘነዉ

ü  ጊዜ አጠቃቀማችንን ሙሉ እና ስኬታማ ነዉ ብለን እናስበዋለን

ጊዜን በአግባቡ/በጥበብ/ መጠቀም ያለዉ ጥቅም

ü  የስኬታማነታችንን ሁኔታ ይወስናል

ü  ጊዜን በቁጥጥር ስር ስታደርገዉ ስኬትን የሚያስቀሩ/የሚያርቁ ሁኔታዎችን ታስወግዳለህ

ü  በጊዜ ባላለቁ የተጠራቀሙ ሥራዎች የሚመጣ ዉጥረትና ጭንቀትን መቀነስ

ü  የአዕምሮ ሰላምና የመከናወን ስሜት

ü  የጉልበት መጨመር (የጉልበት እና የጊዜ ነፃነት ማግኘት)

ü  ጥራት ያለዉ እና ጠንካራ የቤተሰብ ትስስር (የጊዜ አጠቃቀማችን ችግር ካለበት ተግባሮችህን በጊዜዉ ስለማትጨርሳቸዉ ከቤተሰብ ጋር ሊኖርህ የሚገባዉን ጊዜ የመንካት ባህሪ ይኖረዋል፡፡/ሥራ ቦታ ማምሸት፣ ሥራን ወደ ቤት ይዞ መሄድ፣ቅዳሜ እና ዕሁድ እረፍት ማጣት፣ በእንቅልፍ ሰዓት በጭንቅት መቃዠት፣ )

ü  የተሻለ ጤንነት /ጊዜህን በአግባቡ ተጠቅመህ ተግባራትህን ካጠናቀቅህ በቀሪዉ ጊዜህን ጤንነትህን መንከባከብ የሚያስችል አቅም ይኖርሃል/

v  ጥናቶች እንደሚያመለክተዉ በአግባቡ የዓመት ፈቃዳቸዉን ወስደዉ የሚያርፉበት ሰወች ከሌሎች ሰራተኞች 20 በመቶ የልብ በሽታን ይቀንሳል፡፡

ጊዜን በጥበብ ያለመጠቀም ጉዳቶች

ü  የባከነ ህይወት ( “ የባከነ ሃብት በሥራ ይተካል፣ የባከነ ዕዉቀት በጥናት ይተካል፣ የጠፋ ጤንነት በመድሃኒት ይመለሳል፣ የባከነ ጊዜ ግን ለዘለዓለም ጠፍቷልና መተኪያ የለዉምሳሙኤል ስማይልስ)

ü  የድካም ህይወት

ü  የማይረካ ህይወት

ü  ተፈላጊነት የሌለዉ ህይወት

ü  በግዳጅ ዉስጥ የሚኖር ህይወት

ü  ዕቅድ የለሽ ህይወት

ü  መዘዘኛ ህይወት

የጊዜ አጠቃቀም እንቅፋቶች
ሙያ ነክ እንቅፋቶች
ዉጫዊ እንቅፋቶች
ስነ ልቦናዊ እንቅፋቶች
ü  የተግባር ዝርዝር አለማዉጣት
ü  የድካም እና የህመም ስሜት
ü  ግልፅ ያልሆነ ግብ እና የሥራ ቅደም ተከተል
ü  ለሥራ ቀጠሮን እና የጊዜ ገደብን አለመመደብ
ü  የኑሮ ሁኔታ መለወጥ
ü  ፍርሃት
ü  ለሥራዉ የማይስማማ ሰዓት መመደብ
ü  ግርግር የሞላበት አከባቢ /ምቹ ያልሆነ የሥራ አካባቢ/
ü  የድብርትሥጋት
ü  ለሥራዉ በቂ ጊዜ አለመመደብ
ü  የሰዎች ተፅዕኖ
ü  ለሰወች መኖር
ü  ለሥራዉ የማይመጥን ማንነት

ü  ፍፁማዊነት
ü  የአሰራር ሂደት ጉድለት





for more information join my telegram channel
https://t.me/deressereta

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...