ልጥፎችን በመለያ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ
ልጥፎችን በመለያ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ በማሳየት ላይ። ሁሉንም ልጥፎች አሳይ

ቅዳሜ 22 ኦገስት 2020

+ እግዚአብሔር እንዴት ይፈርዳል? +



+ እግዚአብሔር እንዴት ይፈርዳል? + 
(ጊዜ ወስደው ያንብቡት አያጥር ነገር ታሪክ ሆኖ ነው)
አንድ ግብፃዊ መነኩሴ ለገዳሙ መርጃ የእጃቸው ሥራ የሆኑትን ቅርጫቶች ሊሸጡ ወደ እስክንድርያ ለመጓዝ በጠዋት ተነሡ፡፡
በመንገድ ላይ ታዲያ ትልቅ የቀብር ሥነ ሥርዓት ለማድረግ የሚጓዝ ሕዝብ ገጠማቸው፡፡ ሟቹ ዝነኛ አረማዊ ገዢ ሲሆን በዘመነ ሰማዕታት በሺህ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖችን የገደለ ሰው ነበር፡፡ አሁን ዕድሜ ጠግቦ ሞቶ ነው፡፡ ቀኑ ውብ ፀሐያማ ቀን ነበርና የሀገሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ገዢያቸውን እየቀበሩ ነው፡፡
ይህንን ያዩት መነኩሴ ጉዳያቸውን ፈጽመው ወደ ገዳም ሲመለሱ አሳዛኝ ዜና ሰሙ፡፡ ለስድሳ ዓመታት በበረሃ በብሕትውና ቅጠልና የበረሃ ፍሬ ብቻ እየበላ የኖረ ባሕታዊ በዚያች ዕለት በጅብ ተበልቶ ሞቶ ነበር፡፡
መነኩሴው እጅግ ጥልቅ ኀዘን ውስጥ ሆነው እንዲህ ሲሉ አሰቡ ፦
‘በሺህ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖችን የገደለው አረማዊ ሰው በታላቅ ክብር ታጅቦ ሲቀበር ሕይወቱን ሙሉ በጾምና በጸሎት ፈጣሪውን ያገለገለው ባሕታዊ በጅብ ተበልቶ የተዋረደ አሟሟት ሞተ፡፡ይህ እንዴት ዓይነት ፍርድ ነው? እግዚአብሔር ከመልካምነቱ ሁሉ ጋር ኢፍትሐዊ ነገሮች ሲሆኑ ዝም ብሎ ይፈቅዳል፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ሰዎች የፈጣሪን መኖር ይጠራጠራሉ፡፡ እኔም ፍርዱን እንዲገልጽልኝ መጸለይ ይኖርብኛል’ አሉ፡፡
ከዚያች ቀን ጀምሮ መላልሰው ወደ ፈጣሪ ‘’ፍርድህን ግለጽልኝ’ ብለው ደጋግመው ጸለዩ፡፡ ብዙም ሳይቆይ እግዚአብሔር ፍርዱን እንዲህ ገለጠላቸው፡፡
ከሳምንታት በኋላ እንደተለመደው ወደ እስክንድርያ የሦስት ቀን ጉዞ ሊሔዱና ቅርጫታቸውን ሊሸጡ ተነሡ፡፡መንገዱን እንደጀመሩ ድንገት አንድ ወጣት መነኩሴ ወደ እርሳቸው ሲመጣ ተመለከቱ፡፡
‘’አባቴ ይባርኩኝ’
‘እግዚአብሔር ይባርክህ ልጄ’
‘አባቴ ወዴት ይሔዳሉ?’ አለ ወጣቱ መነኩሴ
‘ወደ እስክንድርያ ቅርጫቴን ልሸጥ እየሔድኩ ነው’ አሉት
‘ጥሩ አጋጣሚ ነው አባ እኔም ወደዛ እየሔድኩ ነው’ አለ በትሕትና
‘ጎሽ አብረን እንጓዛለና’ አሉ አባ፡፡ ወጣቱ መነኩሴ ከእጃቸው ሸክማቸውን ተቀበለ፡፡ ጥቂት እንደሔዱ እንዲህ አላቸው፡፡

ረቡዕ 8 ኖቬምበር 2017

ትዳር ክፍል 3



ከዚህ ቀደም በሁለት ክፍሎች ስለትዳር መነጋገራችን ይታወሳል፤ ክፍል ሶስትን እነሆ፡፡
"ሰዉ እናቱንና አባቱን ይተዋል፤ … " ባል ከሚስቱ ሚስትም ከባሏ ጋር ይተባበራሉ ሁለቱም አንድ ስጋ ናቸዉና፡፡ በትዳር ዓለም ዉስጥ በባህልም በሃይማኖትም የምንስተዉ ስህተት ይህ ነዉ አንድ አለመሆናችን አለመተባበራችን፡፡ ትዳር አዲስ አለም መመስረት እንደመሆኑ መጠን ሁሉ ከአዲስ መንደር ባልተናነሰ መልኩ ብዙ መሟላት ያለባቸዉ የህይወት መሰረተ ልማቶች አሉ፡፡ እስካልተሟላ ድረስ ችግሮች መኖራቸዉ አይቀሬ ነዉ፡፡ ወደ አንድ የሚያመጣ የፍቅር መንገድ፣ ቁጣን የሚያበርድ የትዕግስት ዉሃ፣ ብዥታን የሚያጠፋ የመተማመን ብርሃን (መብራት)፣ አረፍተ ዘመን እስኪገታን ስንቅ የሚሆን የፍቅር ምግብ፣ አንዳችን ለአንዳችን መከታ ሆነን የምንኖርበት የተስፋ መጠለያ፣
… ወዘተ ግድ ያስፈልጉናል፤ ይህን ጊዜ ሰዉ እናት እና አባቱን ይተዋል፡፡
ባል/ሚስት ይህን መሰረተ ልማት (ትዳር) ሲያጡ የፍቅር ረሃብ ለማስታገስ እናታቸዉ ጋር፣ ተስፋ በማጣት መከታ ወደ ሆነ አባት መሄድ ግድ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ለነዚህ ችግሮች መፍትሔ ሁለቱም ግዴታ አለባቸዉ፡፡ በመሰረቱ እነዚህ ጎደሉ ተብሎ የትም አይኬድም፤ ስንጀምር እንዳነሳነዉ በባህልም በሃይማኖትም የምንስተዉ ስህተት ስለሆነ እንጂ፡፡
ብዙሃን ኢትዮጵያዊያን ትዳር የምንመሰርተዉ እስከቤተሰቦቻችን ስለሆነ አብዝቶ ችግሩ ይስተዋላል፤ ባልም ሚስትን ቤተሰቦቼንማ አትንኪብኝ፣ ሚስትም ባልን በቤተሰቤማ አትምጣብኝ፣ ወዘተ መባባሉን ይጀምራሉ፡፡ ችግሮችን በጋራ እንደመፍታት ችግር ለመፍጠር እንደተደራጀ ቡድን እለት እለት ጭቅጭቅ እና ንዝንዝ የበዛበት ህይወት ይመራሉ፡፡

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...