ዓርብ 5 ጁን 2020

"አንዱ ስለ ሁሉ ቤዛ ሞተ"

"አንዱ ስለ ሁሉ ቤዛ ሞተ"

መምህር ዘለአለም ወንድሙ
፪ቆሮንቶስ 5: 14
አንዱ:- ማን ነው? አካላዊ ቃል ወልድን ነው። ከሶስቱ አካል አንዱ ወልደ እግዚአብሔር ነው
በምን ሞተ:- ለባህሪው ሞት የማይስማማው ጌታ በፈቃዱ ሞተ። ነፍሱን ሊጥላት እና ሊያነሳት ስልጣን አለውና ዮሐንስ 10: 17
የሞተው በፍቅሩ ነው ሮሜ 5: 8 ሐጢያተኞች ሳለን
ፍቅር ኋያል ወልድን ከመንበሩ ሳበው እንዲል
በግፍ ተሰቅሎ ሞተ
ዮሐንስ15: 22
ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ብዙ የመጽናኛ ቃል እየተናገረ፣ ድውያንን በተአምራት፣
መዝሙር 68: 4 በከንቱ የሚጠሉት በዙ፣ በረቱ
በስጋ ሞተ
፩ ጴጥሮስ 3: 18 ሞት በሚስማማው በስጋ ሞተ በባህሪው/በመንፈስ ህያው ነው
ለምን እንደሞተ:-
ጠላችን ዲያብሎስን ሊሽርልን ነው ለ5ሺ 5 መቶ ዘመን ወደ ሲኦል ስንጋዝ የነበርነውን የሰው ልጅ ነጻ ያወጣ ዘንድ ሞተልን
እብራዊያን 2: 14- በሞቱ በሞት ላይ አለቃ የነበረውን ከስልጣኑ ሰይጣንን ሊሽረው ሞተልን።
በሥጋ ምክንያት የሞተውን አዳምን በስጋ ማርያም አድሮ ከርሷ ተወልዶ፣ መከራ ተቀብሎ ፣ ሞቶ አዳነን።
ዮሐ3: 16 የዘለአለም ህይወት እንዲሰጠን ሞተ
ከሲኦል ባርነት ሊያወጣን ሞተ
ቆላሲስ 2: 14 በመከራ ሳለን የሚቃወመንን የእዳ ደብዳቤ ሊሽር፣ ነጻ ሊያወጣን፣ ሞትን በመስቀል ላይ ሊጠርቀው እኛን ነጻ ሊያወጣን፣ ህይወት ሊሰጠን፣ ሞተልን።
በህገ ልቡና የነበሩ ሌዋውያን ካህናት፣ ቅዱሳን፣ የተሰውት የእንስሳት መስዋእት ሊያድነን አሌቻለም። ይህ አልተቻላቸውም።
ትንቢተ ሆሴእ 13: 14 በትንቢት እንደተናገረ የሞትን መውግያ ሠበረ፣ ድል ነሳው።
ሞታችንን በሞቱ ሊያስወግድልን ሞተ
ሮሜ 15
ከርሱ አስቀድሞ አንዳችም ሃይል አልነበረም።
ዮሐንስ 11: እኔ ትንሣኤ እና ህይወት ነኝ እንዳለ ከሞት ቀስቅሶ በስጋ ሞቶ ህይወት ሰጠን።
፩ ቆሮንቶስ15: 3 ስለኛ ሃጢያት በሥጋ ሞተ በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ፤ ሞቶ አልቀረም። መቃብሩን ባዶ አድርጎታል። ሞት ሊያስቀረው፣ ሊያሸንፈው አልቻለም።
ኢሣይያስ 25 :8 - ሞትን ለዘለዓለም ይውጣል፣ይሽረዋል፣ ያስወግዳል ተብሎ እንደተጻፈ
እንባችንን አበሰ፣ ስድባችንን ያስቀር ዘንድ ተሰደበ፣ መከራችሁን በቃችሁ ሊል መከራ ተቀበለ፣ ሞተልን፣ የትንሣኤ በኩራት ይሆን ዘንድ ተነሳ።
፩ቆሮ15: 20
እኛም የማይቀረውን ሞት ስንሞት ምተን አንቀርም እንነሳለን። ከሞት በኋላ መቃብር እንዳለው ከመቃብር በኋላ ትንሣኤ አለ።
ለእርሱ ክብር እንድንነሳ ሞተልን ፩ ቆሮንቶስ ፭: 14
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንድንኖር ሞተልን የአይናችንን አምሮት የሥጋችንን ፍላጎት እንዳንኖር ውድ ዋጋ ከፈለልን።
፩ ቆሮንቶስ 6: 19
ስለዚህ በሥጋችን እንድናከብረው የሞት ዋጋ ከፈለልን
ሮሜ 8: 12 የሥጋና የደሙ እዳ አለብን።
የምንሰማው ቃሉ፣ የምንጠራበት ሥሙ፣ የተቀበልነው ሥጋና ደሙ፣ እዳ አለብን።
በፈቃዳችን ፈቃደ ሥጋችንን ለፈቃደ ነፍሳችንን አስገዝተን ልንኖር ይገባል። ሐብታችን፣ እውቀታችን፣ ሠውነታችን ጣኦት ሊሆንብን አይገባም። ከዚህ እስር
ኤፌሶን 5: 14 አንተ በሐጢያት አለም መካከል የምትተኛ በንሰሐ ንቃ ከአእምሮ ሞት ንቃ የእግዚአብሔር ፍቅር ልብህን ይግዛው።
ከእርሱ ጋራ ለዘለዓለም እንድንኖር ስለኛ ሞተ።
፩ ተሰሎንቄ 5: 9
የህይወትን አክሊል እንድንቀዳኝ ሞተ
እግዚአብሔር ለምን ወደክ ሳይሆን ለምን አትነሳም ነው አለማው። ንሰሐ አዘጋጅቶልናል። በንሰሐ እንድንነሳ፣ በሕይወት አብረን እንድንኖር ሞተ።
በሞት እንድንመስለው እንዲሁ ደግሞ በትንሣኤው ልንመስለው ይገባናል።
ስለዚህ የተከፈለልንን ዋጋ አስበን ወልድ ወደዚህ አለም የመጣበትን አላማ እያሰብን በንሰሐ ሁላችንም ከወደቅንበት ኃጢአት እንነሳ፣ በህይወት እንመላለስ፣ በክብር ለዘለዓለም የተከፈለልንን ዋጋ የሚመጠን የጽድቅ ኑሮ እንኑር።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...