በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖታዊ ሥርዓት መሠረት የዛሬዋ እሁድ በዓለ ጰራቅሊጦስ ይባላል።
"ወላጆች_እንደሌላቸው_ልጆች_አልተዋችሁም" (ዮ.ሐ14፥18)
✍️ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት
#መጽንኢ በእምነት የሚያጸና፣
#መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣
#ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣
#መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣
#ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡
#መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣
#ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣
#መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣
#ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡
#ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ👉 (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት ባባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ)