እሑድ 28 ማርች 2021

በአንድ አፍ ሁለት ምላስ

 በአንድ አፍ ሁለት ምላስ

አስገዳጅ ሕግ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሆነ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ እና ጤና ሚኒስተር ከሰኞ ጀምሮ እንደሚተገብር የጋራ መግለጫ ሰጥቷል።

ምክንያቱ ደግሞ ከህብረተሰቡ ልቅ እንቅስቃሴ በመነሳት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መጠን መጨመር፣ በቫይረሱ የሚያዙ ሰወች መጨመር፣ በቫይረሱ የሚሞቱ ሰወች ቁጥር መጨመር፣ ተጎጂዎችን ተንከባክቦ ማከሚያ ሥፍራዎች መሙላት፣ የጤና ባለሙያዎች እረፍት አልባ አገልግሎት ማብቂያ ማጣት፣ የኢኮኖሚ ድቀት ወዘተ ናቸው።

በሳምንት ውስጥ ወደ 13ሺ የሚጠጉ ሰወች በቫይረሱ ተይዟል።

ይሁን እንጂ መንግሥት ቁርጠኛ አቋም እንደሌለው ማሳያዎች ብዙ መሆናቸው እሙን ቢሆንም ህብረተሰቡ ሕይወቱን በኪራይ መልክ ያገኘው ይመስል የሚጠበቀውን ያህል ጥንቃቄ እያደረገ አይደለም።

ለምሳሌ በዛሬው ዕለት በሸገር ባስ በነበረኝ እንቅስቃሴ ሰአት እንኳን ኮቪድ 19 ያለ በሠላማዊ ወቅት ሊጭን ከሚገባው በላይ ነው።

የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በተለመደው ሁኔታ አሰራራቸው ያለምንም ጥንቃቄ በአንድ ክፍል ውስጥ ርቀታቸውን ሳይጠብቁ ተጨናንቀው መስኮት ሳይከፍቱ የእለት ተለት ተግባራቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።

የንግድ ስፍራዎች፣ የግብይት ስፍራዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሌሎችም ሕዝብ የሚንቀሳቀስበት ሥፍራዎች እንቅስቃሴዎች እንደወትሮው የሰው ትርምስ ይታይባቸዋል።

ይህንን በታዘብኩበት ሰአታት ውስጥ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር እና አቃቤ ሕግ የጋራ መግለጫ እንዳወጡ ሰማሁ። በአንድ አፍ ሁለት ምላስ ብዬዋለሁ። መነሻዬም ክልከላውም ልል ቁጥጥሩም ከራሱ ስፍራ ስለሆነብኝ ነው።

ብዙዎች በሕክምና ላይ ናቸው፣ ብዙዎች ታመው ድነዋል፣ ሌሎች ሞተዋል፣ ሌሎቻችን በመያዘ እና ባለመያዝ ሁለት ምርጫ መካከል ነን። የትኛውን መምረጥ እንዳለብን የታመነ ቢሆንም ህብረተሰቡ ያለው የቫይረሱ ንቀት እና ጥንቃቄ አልባ እንቅስቃሴ ስጋት ያጭርብኛል።

መንግሥት ያቀደውን ለማሳካት ከሚረዱት አካሄዶች አንዱ የሚያስተዳድረውን የትራንስፖርት አገልገሎት ሰጪ ተቋም ሸገር ባስ፣ አንበሳ ባስ ላይ የተሳፋሪውን ቁጥር በመቀነስ ርቀትን መጠበቅ አንዱ መንገድ ነበረ። ነገር ግን ሲሆን አይታይም።

ለዚህም ነው በመነሻዬ ላይ መንግሥት ቁርጠኝነት ይጎድለዋል ያልኩት። ህዝቡም አንድ ነፍስ ብቻ እንዳለው እና አንዴ ካመለጠች መተኪያ የላትምና መልእክቴን አድርሱልኝ።

• አካላዊ ርቀታችንን እንጠብቅ
• ማስክ እናድርግ
• እጃችንን በውሃ እና በሳሙና በደንብ እንታጠብ ካልሆነም ሳኒታይዘር እንጠቀም
መንግሥትም በአንድ አፍ ሁለት ምላስ ከሚሆንብን ሕዝብህን ለመታደግ ቁርጠኝነትህን አሳየን። አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድክ ትውልዱን ታደግ።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...