ዓርብ 26 ማርች 2021

አነጋገራችሁ ሁልጊዜ በጨው እንደተቀመመ ይሁን

 አነጋገራችሁ ሁሌ በጨው እንደተቀመመ ይሁን



እንደ እግዚአብሔር ቃል አነጋገሩ ሁሌ በጨው እንደተቀመመ የሚጣፍጠኝ ዴል ካርኒንግ የሚባል ሰው አለ።


አብዛኞቻችሁ ታውቁታላችሁ ፤ የመጽሐፍ ደራሲ ነው።


ምክሮቹ፣ ተግሳጾቹ እና ዘዬዎቹ በትንሽ መጽሐፍ ተሰድራ እንደ ብሉያት እና ሐዲሳት መጻሕፍት ከዘመን ዘመን ትሻገራለች።


"የጠብታ ማር" ትሰኛለች። 


በተደጋጋሚ አንብቤዋለሁ፣ ብዙ ጊዜ ገዝቼ ለሰው በስጦታ መልክ ሰጥቼዋለሁ፣ ብዙ ጊዜ ከመጽሐፍ መደርደሪያ ላይ ጠፍቶብኛል፣ ዘወትር ለምን ብዬ ጠይቃለሁ፣ ሁሌም ሳነበው አዲስ ይሆንብኛል።


ምሥጢሩ አልገባኝም።


ይኸው ዛሬም ምሥጢሩን እየፈለኩ አንድ ነገር ብልጭ አለብኝ። " እንደ አነጋገራችን አስተሳሰባችንም በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሆን ዘንድ።


በጨው የተቀመመ ነገር ከመጣፈጡም ባሻገር እንደ እናቶቻችን ሙያ ከሆነ አይበላሽም፣ ረጅም ጊዜ ይቆያል፣ ለብዙ ጊዜ የሚቆይ ረጅም መንገድ የሚያስጉዝ ስንቅ ይሆናል።


ከመቆየቱ ያለመበላሸቱ ድንቅ ነገር ነው። 


ጨው ሲንተራሱት ጸጉር የሚመልጥ ካልጣፈጠ ድንጋይ ነው ብለው የሚጥሉት ነገር እንዲህ ትልቅ ተግባር ሲኖረው እጅግ ድንቅ ነው። ዋጋውም ከማጣፈጫዎቹ ሁሉ እጅግ ርካሽ ነው።


የሰው አንደበትም፣ አስተሳሰብም፣ ቃላትም እንዲሁ ዋጋቸው ትንሽ ውጤታቸው ትልቅ የሆኑትን መተግበር ተስኖን አለማችን መራር ሆናለች።


አነጋገራችን እና አስተሳሰባችን ዘወትር በጨው የተቀመመ ጣፋጭ ይሁን። 


የትናንቱን እና የዛሬውን በማሰብ አስተሳሰባችንን ከማጥበብ ነገን እያሰብን ሐሳባችንን፣ ቃላቶቻችንን የጣፈጡ እንዲሁም ሰፊ እናርጋቸው።


ሰናይ እለተ ሰንበት ይሁንልን።

ይቆየን።


@deressereta

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...