ሐሙስ 29 ኤፕሪል 2021

ጸሎተ ሐሙስ

 ምሴተ ሐሙስ / ጸሎተ ሐሙስ


" እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። "

የዮሐንስ ወንጌል 13፥1-15 ፣ ማቴዎስ 26፥1-
(በደረሰ ረታ)

በሕማማት ሳምንት በዕለተ ሐሙስ ጌታ ደቀመዛሙርቱን እግር ያጠበበት ነው፤ ሌሎቹ ፈቅደው ወደው ሲታጠቡ ቅዱስ ጴጥሮስ አታጥበኝም ብሎ አስቸግሮት ነበረ። ምሥጢሩን እና ምሳሌውን አላስተዋለም ነበረና።

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስተምሮ መክሮ ገስጾ መልሶታል። እርሱም ለመመለስ ልቡ ቅርብ ነበረና እሺ በጄ ብሎ ታጥቧል።

ይህ ዕለት የትህትና ዕለት ነው። ጌታ እግራቸውን አጥቦ ሲጨርስ እኔ መምህር ስሆን ዝቅ ብዬ የተማሪዎቼን / የደቀመዛሙርቴን እግር ካጠብኩ እናንተም እንዲሁ አድርጉ ብሎ አስተማራቸው።

ቅዱስ ያሬድም ስለዚች ዕለት ይለናል፦

“ሐዋርያቲሁ ከበበ
እግረ አርዳኢሁ ሐጸበ
ኮኖሙ አበ ወእመ
ወመሀሮሙ ጥበበ”

ሲተረጎም፦ ሐዋርያቱን ሰበሰበ፤ የደቀ መዛሙርቱንም እግር አጠበ፤ እንደ አባትና እናት ኾናቸው የትሕትና ጥበብን አስተማራቸው። ማለት ነው።

ከዚህ ዕለት ብዙ የምንማረው ነገር ቢኖርም አንዱና ዋነኛው የጌታን ትሕትና ነው። ጌታ ሲሆን እግር አጠበ። በተግባር ያሳየ የትህትና መምህር ነው።

ቅድስት የሆነች ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን በየአመቱ ይህን ምሥጢር በጸሎተ ሐሙስ ታከናውናለች። ከቅዱስ ፓትሪያርኩ ጀምሮ ዐዕይንተ እግዚአብሔር ካህናት በእርሱ ምሳሌ የምዕመኑን እግር ወገባቸውን ታጥቀው ዝቅ ብለው ያጥባሉ። ምሳሌ ነው።

መምህረ ትህትና ኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ጴጥሮስ እግሩን አልታጠብም ብሎ እንዳስቸገረ እንዲሁ መምህራንን ቅድስ ቤተክርስቲያንን አስተምሮቷን አንቀበልም የሚሉ ለሥርአቷ የማይገዙ ደንዳና ልብ ያላቸው አሉ። እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ ያሉ ትምህርት ሲያገኙ የሚመለሱ አሉ። እነዚህን አስተምራ ትመልሳለች እንደ ይሁዳ ያሉትን ልበ ደንዳኖች አውግዛ ትለያለች።

እኛም አስተምህሮቷ ገብቶን እና የምሥጢሩ በረከት ተገብቶ ይድረሰን።

የሰው ልጅ ክቡር እና እኩል ቢሆንም ቅሉ። ካለንበት እንዳለንበት ደረጃ በትህትና ዝቅ ብለን ልንታዘዝ፣ ልናገለግል ይገባናል።

ትሕትና የመንግሥተ ሰማያት መወጣጫ መሠላል ናትና ትሕትናን ገንዘብ እናድርግ። እርፍ የጨበጠ መሰላል ላይ የወጣ ከመጨረሻው እስኪደርስ ድረስ ወደኋላ አይልምና ዘወትር ትሕትና አይለየን።

ይሕ ቀን ሌላ ተግባር ተከናውኖበታል። በአልአዛር እና ኒቆዲሞስ ቤት ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ለደቀመዛሙርቱ ይህ ነገ የሚፈሰው ደሜ፣ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው ጠጡ ፥ብሎ ሰጣቸው። ምሥጢረ ቁርባንን የጀመረበት ዕለትም ነው። የአዲስ ኪዳን ተግባር የተጀመረበት ዕለት ነው።

ሥጋውን ደሙን ከመቀበላቸው አስቀድሞ በእግራቸው በኩል ሕሊናቸውን፣ ሰውነታቸውን፣ ነፍሳቸውን አጽድቶ አጥቦ ለቁርባን አቀረባቸው።

እኛም ርስት መንግሥተ ሰማያትን የሚያወርሰውን ሥጋውንና ደሙን እንድመገብ ንሰሐ ገብተን ጸድተን እና ነጽተን እንቀረብ፤ ለዚህም እግዚአብሔር ይርዳን።

አምላካችን ዐይን ያላየውን፣ ጆሮ ያልሰማውን፣ በሰው ልቡና ያልታሰበውን፣ እግዚአብሔር ለሚወዳቸው ያዘጋጀውን ርስት መንግስተ ሰማያትን ያውርሰን።

ይቆየን።
አሜን።

ሰኞ 26 ኤፕሪል 2021

ሰሙነ ሕማማት ሰኞ ( መርገመ በለስ)

 ሰሙነ ሕማማት ሰኞ ( መርገመ በለስ)

ማቴዎስ 21 : 10 - 19

ከእለተ ሆሳእና ማግስት ኢየሱስ ክርስቶስ ተራበ ይለናል። ፍጹም ሰው መሆኑን ለማጠየቅ ተራበ ተብሎ ተጻፈ። ስለተራበም ረሃቡን ማስታገሻ ምግብ ፈለገ። አንዲት በለስ ተመልክቶ ወደርሷ አመራ። ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም አላገኘባትምና " ለዘለዓለሙ ፍሬ አይገኝብሽ አላት " በሌሊትም ያንን ጊዜውን ደረቀች።

ወንጌላዊው ማቴዎስ በሰሙነ ሕማማት ሰኞ ስለተፈጸመው ተግባር ሲጽፍ ጌታ የረገማት በለስ ወዲያው እንደ ደረቀች የጌታ ደቀመዛሙርትም ይህን አይተው እንደተደነቁ ይነግረናል።

በሌሊቱ የተረገመችው በለመለመችና ፍሬ በምታፈራበት ወቅት ነበረ። ይህን ሲያስረግጥልን ቅዱስ ማርቆስ በምዕራፍ 11 ቁጥር 13 ላይ " የበለስ ወራት አልነበረምና " ይለዋል።

ታዲያ ቅዱስ ማርቆስ የበለስ ወራት እንዳልሆነ ካረጋገጠልን ጌታ ስለምን ከበለሲቱ ፍሬ ፈለገ? የሚል ጥያቄ ያስነሳል።

አባቶቻችን እንዲህ ብለው ይኸን ጥያቄ ይመልሱታል። ከበለሷ ፍሬ መፈለጉ፥
• አንዳንድ በኩረ በለስ አይታጣም ብሎ ነው ይላሉ፣
• አንድም አላዋቂ ሥጋን እንደ ተዋሃደ ለማጠየቅ ነው ይሉናል፣
• አንድም አውቃለሁ ብሎ ሥራውን አይተውምና በዚያው ሥራውን ለመሥራት ነው።
ቅዱስ ማቴዎስ እና ቅዱስ ማርቆስ የጻፉለት በለስ ምሳሌ አላት። በበለስ የተመሰለው:-
፩. እስራል ናት

በበለሷ በረሃብ ሰአት የሚባላ መልካም ፍሬ ሊያገኝባት በወደደ እና በፈቀደ ጊዜ እንዳላገኘባት ሁሉ በእስራኤልም እንዲሁ ሃይማኖት፣ ምግባር ባገኝባቸው ብሎ ሄደ። አንዳች አላገኘባቸውም እስራኤል ከመባል በቀር። ደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት። ያን ጊዜ ደግ ሰው ጠፋ።
" አቤቱ አድነኝ ደግ ሰው ጠፍቷልና " እንዲል ልበ አምላክ ንጉስ ዳዊት።

በለሷ እንደ ደረቀች እስራኤልም የተሰጣቸው የመመለሻ 40 ዘመን ሲያልቅ ምድረ እስራኤል ጠፋች።

፪. ህገ ኦሪት ናት

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እስራኤል ሰው ፣ ምግባር ፣ ሃይማኖት ፣ በጎነት ፣ፍለጋ እንደ ሄደ ነገር ግን የሚገድል እንጂ የሚያድን ህግ ሆኖ አላገኘውም።

ህገ ኦሪት ሰውን አልጠቀመምና ህገ ኦሪትን አሳለፈው። ሻረው።

ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ሮሜ ሰወች በላከው መልዕክቱ ምዕራፍ 8፥2 ላይ " በክርስቶስ ኢየሱስ ያለው የሕይወት መንፈስ ሕግ ከኃጢአት ከሞት ሕግ አርነት አውጥቶኛልና። " እንዲል ሕገ ኦሪት የሞት ሕግ ነበረ ማለት ነው።

ኦሪት ሕግና ሥርአት ነበራት የማይጠብቋትን መቀጣጫ ናት።

፫ . ኃጢአት ናት

ኃጢአት እንደ በለስ ቅጠል ሰፍታ በዚህ ዓለም ሞልታ አግኝቷታልና ረገማት። ኃጢአት በሶስት ነገር በበለስ ተመስላለች።
1. አዳምን ከገነት ያህል ቦታ እንዲወጣ እግዚአብሔርን ከመሰለ ጌታ የለየችው ዕፀበለስ ናትና።
2. የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደመሆኑ መጠን የኃጢአትም መንገድ ሊጓዙበት የሚያመች ሰፊ መሆኑን ሲያጠይቅ።
3. በለስ ሲበሉት እንደሚጣፍጥ ሲቆይ እንዲመር ኃጢአትም ሲሰሩት ለሥጋ ደስታን የሚሰጥ ፣ ስሜትን የሚያረካ ነገር ግን ፍፃሜው ሞት እና መከራ ያለበት ህይወት ነው።
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክብር ይግባውና ስለ ናትናኤል ሲናገር " ፊሊጶስ ሳይጠራህ ከበለስ በታች ሳለህ አየሁህ አለው " ዮሐንስ 1፥49

በለስ የኃጢአት ምሳሌ ነውና ኃጢአት ሰርተህ በበለስ ስር በተሸሸግህ ጊዜ አውቅሃለሁ ማለቱ ነበር። በአንድ ወቅት ናትናኤል የሰው ሕይወት አጥፍቶ በበለስጨስር ቀብሮ ነበረና።

በለስን መርገሙ ኃጢአትን መርገሙ ነው። መርገሙ ከዚህ በኋላ በሃጢአት አንዳች ሰው አይያዝ ማለቱ ነው።

ለዚህም ነው አባቶቻችን በቀመራቸው የሕማማትን ሰኞ መርገመ በለስ ብለው መሰየማቸው።

ምድራችን የሰው ልጅ ከኃጢአት ርቆ ከእግዚአብሔር ተጣብቆ የሚኖርባት ትሆንልን ዘንድ የእግዚአብሔር አምላካችን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን።

ይቆየን።
አሜን።


የእለት ተለት ጽሑፎቼን ለመከታተል ከዚህ በታች ባሉት ሁሉ እገኛለሁና ይከታተሉኝ። ከተመቸዎት ለሌሎች ያጋሩት።
My Facebook page link (በፌስቡክ ገጽ እንገናኝ)

https://www.facebook.com/deresse2020/

Main facebook account (ዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ይቀላቀሉት)

https://www.facebook.com/DeresseReta

Follow me through telegeram (በቴሌግራም ሊከታተሉኝ ከፈቀዱ) ሁሉም ምልከታዬን የማጋራባቸው ማህበራዊ ድረ ገጾች ናቸው።

https://t.me/deressereta

ከአሥር አመት በላይ ከ50ሺ በላይ አንባቢዎች ያሉት መጦመሪያም አለ።

www.deressereta.blogspot.com

https://anchor.fm/deresse-reta/episodes/ep-ev5j5o

ረቡዕ 21 ኤፕሪል 2021

አቤቱ የሆነብንን አስብ

 "አቤቱ የሆነብንን አስብ" ሰቆቃው ኤርሚያስ 5 : 1


ኢትዮጵያ እንደ አገር ሕዝቦቿም እንደ ሕዝብ በአራቱም አቅጣጫ ያልሆነባት ነገር የለም። ሕዝቦቿ አንዱን መከራ ተሻገርን ሲሉ ሌላ መከራ ይደቀንባቸዋል።

የተፈጥሮ ሲባል ፣ ሰው ሰራሽ ፣ ሰው ሰራሹን አለፍን ሲሉ ሌላ ይደቀናል።


ወደ መንግስት ጮኽን ወደ አንተ አንጋጠጥን መልስ አላገኘንም። አቤቱ እባክህ ቸሩ ሩህሩህ ይቅር ባይ አምላካችን ሆይ የሆነብንን አስብ።


• ሴት ልጅ እስከ ጽንሷ ተገድላ ከሜዳ ላይ ተጥላለች፣

• ህጻናት ያለወላጅ ቀርተዋል፣

• አባት በሚስቱ እና በልጆቹ ፊት ተገድሏል፣

• ልጃገረዶች ተደፍረዋል፣

• ወጣቶች ተሰደዋል ተገድለዋል፣

• የሰው ልጅ እንደ እንስሳ ተቆጥሯል፣

• አሟሟታችን ከእንስሳት አንሷል፣

• ተገድለን ቁልቁል እየተሰቀልን፣

• ሞተን መቀበር ቅንጦት ሆኗል፤ አቤቱ የሆነብንን አስብ።

• በአሕዛብ ፊት መሰደቢያ ሆነናል፣

• የመገናኛችን ቤተመቅስ ተቃጥሏል አጥር ቅጥርህ ተደፍሯል፣

• አምላኬ ሆይ፥ በፊትህ የምንለምን ስለ ብዙ ምሕረትህ ነው እንጂ ስለ ጽድቃችን አይደለምና ጆሮህን አዘንብለህ ስማ፤ ዓይንህን ገልጠህ ጥፋታችንና ስምህ የተጠራባትን ከተማ ተመልከት። አቤቱ፥ ስማ፤ አቤቱ፥ ይቅር በል፤ አቤቱ፥ አድምጥና አድርግ፤ አምላኬ ሆይ፥ ስምህ በከተማህና በሕዝብህ ላይ ተጠርቶአልና ስለ ራስህ አትዘግይ።" ትንቢተ ዳንኤል 9 : 16 - 19

እስላም ክርስቲያኑ በአንድነት ጸሎት አውጆ ከፊትህ ተንበርክኳል ወደ አንተ ይጮዃል ያነባል። አቤቱ የሆነብንን አስብ።


ረሐብ ቸነፈር በሽታ አንበጣ ጦርነት ስድት በዚህ ያልጠና ሰውነት እንዴት ይቻለናል?


ስለህጻናቱ ስትል ማረን፣ ጤዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው ስለሚማልዱት ብለህ ማረን፣ በጾም በጸሎት በፊትህ በአንድነት ስለወደቁት ብለህ ማረን፣ ይልቁንም ከሴቶች ሁሉ ስለተለየችው ጸጋን ስለተሞላችው ቅድስት ድንግል ማርያም ስትል ማረን፣ ስለአለሙ ሁሉ ስትል በቀራንዮ አደባባይ ስለቆረስከው ስጋህ ስላፈሰስከው ደምህ ብለህ ማረን ይቅርም በለን።


የሰው ልጅ ወደ ልቡ ይመለስ ዘንድ በዘር ከመከፋፈል ይልቅ ከአንድ አዳም መፈጠሩን ያስብ ዘንድ ሁሉም አንድ መሆኑን የቋንቋው እንደ የቀለሙ መለየት ልዩነት እንዳያደርግ በዚህም ተከፋፍሎ እንዳይተላለቅ እባክህ ፍቀድ።


በሽታውን አስታግስልን፣

ለነፍሰ ገዳዮች ልብ ስጥልን፣

የተጨነቁትን ልባቸው የተሰበረውን አካላቸው የጎደለውን አጽናናልን፣ ነፍስ ከሥጋቸው በክፉዎች ያለፉትን ማረፊያ በአንተ ዘንድ አዘጋጅላቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ፍጹም መጽናናትን አድልልን።


አቤቱ የሆነብንን አስብ።


ቤተመቅደስ ሲቃጠል ግድ ይበልህ።


እኛ ቤተመቅደሶችህ ስንገደል ግድ ይበልህ።


በስም የተጠራን ልጆችህ እረኛው እንደተመታ መንጋ ስንበተን፣ ስንሳደድ ግድ ይበልህ።


እንባችን በላያችን ደርቋልና በግፍና በበደል ደማችን በከንቱ ፈሷልና የምህረት ዐይንህ ወደኛ ይመልከት።


አቤቱ ሆይ ፥የሆነብንን አስብ።


አሜን።

ይቆየን።


የእለት ተለት ጽሑፎቼን ለመከታተል ከዚህ በታች ባሉት ሁሉ እገኛለሁና ይከታተሉኝ። ከተመቸዎት ለሌሎች ያጋሩት።

My Facebook page link (በፌስቡክ ገጽ እንገናኝ)


https://www.facebook.com/deresse2020/


Main facebook account (ዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ይቀላቀሉት)


https://www.facebook.com/DeresseReta


Follow me through telegeram (በቴሌግራም ሊከታተሉኝ ከፈቀዱ) ሁሉም ምልከታዬን የማጋራባቸው ማህበራዊ ድረ ገጾች ናቸው።


https://t.me/deressereta


ከአሥር አመት በላይ ከ50ሺ በላይ አንባቢዎች ያሉት መጦመሪያም አለ።


www.deressereta.blogspot.com 


https://anchor.fm/deresse-reta/episodes/ep-ev5j5o

ሰኞ 19 ኤፕሪል 2021

መንፈስ ወደ ምድረበዳ ወሰደው

 መንፈስ ወደ ምድረበዳ ወሰደው


ልበ አምላክ ዳዊት "ወደ ቤተ እግዚአብሔር እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ" ይለናል።
ንጉስ ስለሆነ ወደ ወንዝ ዳርቻ፣ ከአለም ጥግ ሌላው ጥግ ድረስ፣ አሉ በተባሉ መዝናዎች፣ ትላልቅ አለም አቀፍ ክንውኖች ዘንድ፣ ከቤተመንግሥቱ ሕንጻ አናት ላይ ሆኖ አየር መቀበል እና ከተማውን መቃኘት፣ የቤተመንግሥቱን ጊቢ አየር መቀበል ይችል ነበረ። ደስታን ከሚፈጥሩ ክንውኖች መካከል እነዚህ ተጠቃሾች ስለሆነ።

በጌታ ደስ ይበላችሁ እንዲል ንጉስ ዳዊትን ምድራዊው ነገር አላስደሰተውም። ይልቁንም ወደ እግዚአብሔር ቤት መሄድ እንጂ የፈለገው።

መንፈሳዊነት የሚገለጥበት ሰው ከሚያዝናናው ነገር ይልቅ ነፍሱን ወደሚያጸድቀው ነገር ያደላልና።

ቅዱሳንን መንፈስ ቅዱስ ወደ ገዳም ይመራቸው ነበረ።
መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መንፈስ ወደ ምድረበዳ ወሰደው ይለናል። መንፈስ ቅዱስ ያላለው መንፈስ ቅዱስ ለአብና ለወልድ ሕይወታቸው ስለሆነ ነው አንድም የራሱ ፈቃድ ስላነሳሳው ነው።

ምድረበዳ አለ፤ ገዳም ለማለት ነው።

ወደ ገዳም ስንሄድ ከፈቃደ እግዚአብሔር ውጭ አይቻልም። ሰው ያስባል እግዚአብሔር ይፈጽማልና መንፈስ ቅዱስ ያነሳሳናል። ለመንፈስ ቅዱስ ማደሪያነት የተመቸ ሰውነት ሲኖረን።

ወደ ገዳም የመሄድ ዝንባሌ ያለው ሰው መንፈስ ቅዱስ የሚያነሳሳው ሰው ነው።

ላይሞላ ነገር የዓለም ፈቃድ ወደኋላ ይስበናል። በዚህ ቀን ደፋ ቀና ከምንለው፣ ከምንሄድበት መርሃግብር ሁሉ የሚበልጥ ለቤታችንም፣ ለሕይወታችንም፣ ለቤተሰባችንም የሚሆን የነፍስ ገበያ ገብይተን የምንመለስበት ሥፍራ ገዳም ነው።

መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶ እየመራ እግራችንን ወደ ገዳም ይውሰደን። ወደ ቤተ እግዚአብሔር እንሂድ ስንባል ከምክንያታችን በላይ ነፍሳችንን የሚያስደስት ነገር ያድርግልን።

ይቆየን
አሜን።

አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል

 " አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል "


" በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ደኅና ሁኑ። ፍጹማን ሁኑ፥ ምክሬን ስሙ፥ በአንድ ልብ ሁኑ፥ በሰላም ኑሩ፥ የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።"
2ኛ ቆሮንቶስ 13 : 11

ለሶስተኛ ጊዜ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቆሮንቶስ ሰወች በሄደ ጊዜ በመጨረሻው ምእራፍ ላይ ያስቀመጠላቸው መልእክት ነው።

ደህና ሁኑ የሚለው ቃል ሁላችንም እንደምንረዳው የስንበት የመለያየት የመጨረሻ ቃል ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በመግቢያው እንደተናገረው " ነገር በሶስት ይጸናልና " እንዳለው ትምህርቱ በልባቸው እንዲጸና ለሶስት ጊዜ ተመላልሶ አስተምሯቸዋል።

በመቀጠልም " ፍጹማን ሁኑ " አላቸው። የሰው ልጅ በመንፈሳዊ ህይወት ሲኖር የሚደርስበት የፍጹምነት ደረጃዎች አሉና እነርሱን ለማስመዝገብ ዝም ብላችሁ ቃሉን የምትሰሙ ነገር ግን የማትተገብሩት ሳትሆኑ በሕይወት የምትኖሩ ሁኑ ሲላቸው ነው።

አንድም በቃሉ የምትሰናከሉ ሳትሆኑ ለሌሎች ምሳሌ የምትሆኑ ሁኑ ሲላቸው ነው።

አንድም እንዲሁ በከንቱ ያለምንም ዋጋ ላይ ታች የምትሉ ሳትሆኑ 30፣ 60፣ 100 ያማረ ፍሬ አፍርታችሁ የዘላለም መንግሥትን ገነትን ውረሱ ሲላቸው ፍጹማን ሁኑ አላቸው።

በመጨረሻም ሲያስተምራቸው ሲመክራቸው እንደመክረሙ ሁሉ ማሳረጊያ " ምክሬን ስሙ፥ በአንድ ልብ ሁኑ፥ በሰላም ኑሩ፥ የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል " አላቸው።

ምክሩም እንዲህ የሚል ነው " በአንድ ልብ ሁኑ፥። በሰላም ኑሩ " ወንድሞች በአንድ ልብ እና በሰላም ሲኖሩ መልካም ነውና። ፍጻሜውም ያማረ ነውና። ቅዱስ ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ወንድሞች አስረግጦ እንደተናገረው የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእኛ ጋር ይሆናል።

ዓለም ለምንድን ነው ከጫፍ ጫፍ ፍቅርና ሰላም ያጣችው?

ለምንስ የዓለማችን ሃያላን አገራት መሪዎች ሰላምን ለማምጣት ያልተቻላቸው?

ለምንስ ነው የየእምነት ተቋማት መሪዎች ፍቅርና ሰላም በምድር ላይ እንዲሰፍን ማድረግ የተሳናቸው?

ለምንስ ነው አባወራዎች የቤቱ እራስ እንደመሆናቸው ፍቅርና ሰላምን በቤታቸው ጣሪያ ስር ማምጣት ያልቻሉት?

ወንድም እህቶቼ የቅዱስ ጳውሎስን ምክር ካለመስማታችን የተነሳ አይመስላችሁም። እኔ በበኩሌ ያለምንም ማመንታትና ጥርጥር ምክንያቱ እርሱ ይመስለኛል፤። ነውም ደግሞ። እስኪ ሁላችንም ሕይወታችንን እንፈትሽ ሠላምና ፍቅራችን አንጻራዊ ነው ወይስ ፍጹም ሠላምና ፍቅር ነው።

ካልሆነ ሕይወታችንን እንፈትሽ በአንድ ልብ በሰላም እንኑር። ያኔ የሰላምና የፍቅር አምላክ ልዑል እግዚአብሔር እንደ ዓለም ሰላም ያልሆነውን ፍቅር እና ሰላም ሊሰጠን ከእኛ ጋር ይሆናልና።

ሁላችንም እንደ ቃሉ ተመላልሰን በአንድ ልብ በሰላም ኖረን ዓለምና በዓለም ያለን የጎደለውን ፍቅርና ሰላም እግዚአብሔር ያድለን።

አሜን።
ይቆየን።
እያተረፉ እውቀት ለመገብየት በሁሉም ሚዲያ ይከታተሉን።

My Facebook page link (በፌስቡክ ገጽ እንገናኝ)

https://www.facebook.com/deresse2020/

Main facebook account (ዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ይቀላቀሉት)

https://www.facebook.com/DeresseReta

Follow me through telegeram (በቴሌግራም ሊከታተሉኝ ከፈቀዱ) ሁሉም ምልከታዬን የማጋራባቸው ማህበራዊ ድረ ገጾች ናቸው።

https://t.me/deressereta

ከአሥር አመት በላይ ከ50ሺ በላይ አንባቢዎች ያሉት መጦመሪያም አለ።

www.deressereta.blogspot.com

https://anchor.fm/deresse-reta/episodes/ep-ev5j5o

እሑድ 28 ማርች 2021

በአንድ አፍ ሁለት ምላስ

 በአንድ አፍ ሁለት ምላስ

አስገዳጅ ሕግ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሆነ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ እና ጤና ሚኒስተር ከሰኞ ጀምሮ እንደሚተገብር የጋራ መግለጫ ሰጥቷል።

ምክንያቱ ደግሞ ከህብረተሰቡ ልቅ እንቅስቃሴ በመነሳት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ መጠን መጨመር፣ በቫይረሱ የሚያዙ ሰወች መጨመር፣ በቫይረሱ የሚሞቱ ሰወች ቁጥር መጨመር፣ ተጎጂዎችን ተንከባክቦ ማከሚያ ሥፍራዎች መሙላት፣ የጤና ባለሙያዎች እረፍት አልባ አገልግሎት ማብቂያ ማጣት፣ የኢኮኖሚ ድቀት ወዘተ ናቸው።

በሳምንት ውስጥ ወደ 13ሺ የሚጠጉ ሰወች በቫይረሱ ተይዟል።

ይሁን እንጂ መንግሥት ቁርጠኛ አቋም እንደሌለው ማሳያዎች ብዙ መሆናቸው እሙን ቢሆንም ህብረተሰቡ ሕይወቱን በኪራይ መልክ ያገኘው ይመስል የሚጠበቀውን ያህል ጥንቃቄ እያደረገ አይደለም።

ለምሳሌ በዛሬው ዕለት በሸገር ባስ በነበረኝ እንቅስቃሴ ሰአት እንኳን ኮቪድ 19 ያለ በሠላማዊ ወቅት ሊጭን ከሚገባው በላይ ነው።

የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በተለመደው ሁኔታ አሰራራቸው ያለምንም ጥንቃቄ በአንድ ክፍል ውስጥ ርቀታቸውን ሳይጠብቁ ተጨናንቀው መስኮት ሳይከፍቱ የእለት ተለት ተግባራቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።

የንግድ ስፍራዎች፣ የግብይት ስፍራዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሌሎችም ሕዝብ የሚንቀሳቀስበት ሥፍራዎች እንቅስቃሴዎች እንደወትሮው የሰው ትርምስ ይታይባቸዋል።

ይህንን በታዘብኩበት ሰአታት ውስጥ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር እና አቃቤ ሕግ የጋራ መግለጫ እንዳወጡ ሰማሁ። በአንድ አፍ ሁለት ምላስ ብዬዋለሁ። መነሻዬም ክልከላውም ልል ቁጥጥሩም ከራሱ ስፍራ ስለሆነብኝ ነው።

ብዙዎች በሕክምና ላይ ናቸው፣ ብዙዎች ታመው ድነዋል፣ ሌሎች ሞተዋል፣ ሌሎቻችን በመያዘ እና ባለመያዝ ሁለት ምርጫ መካከል ነን። የትኛውን መምረጥ እንዳለብን የታመነ ቢሆንም ህብረተሰቡ ያለው የቫይረሱ ንቀት እና ጥንቃቄ አልባ እንቅስቃሴ ስጋት ያጭርብኛል።

መንግሥት ያቀደውን ለማሳካት ከሚረዱት አካሄዶች አንዱ የሚያስተዳድረውን የትራንስፖርት አገልገሎት ሰጪ ተቋም ሸገር ባስ፣ አንበሳ ባስ ላይ የተሳፋሪውን ቁጥር በመቀነስ ርቀትን መጠበቅ አንዱ መንገድ ነበረ። ነገር ግን ሲሆን አይታይም።

ለዚህም ነው በመነሻዬ ላይ መንግሥት ቁርጠኝነት ይጎድለዋል ያልኩት። ህዝቡም አንድ ነፍስ ብቻ እንዳለው እና አንዴ ካመለጠች መተኪያ የላትምና መልእክቴን አድርሱልኝ።

• አካላዊ ርቀታችንን እንጠብቅ
• ማስክ እናድርግ
• እጃችንን በውሃ እና በሳሙና በደንብ እንታጠብ ካልሆነም ሳኒታይዘር እንጠቀም
መንግሥትም በአንድ አፍ ሁለት ምላስ ከሚሆንብን ሕዝብህን ለመታደግ ቁርጠኝነትህን አሳየን። አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰድክ ትውልዱን ታደግ።

ዓርብ 26 ማርች 2021

አነጋገራችሁ ሁልጊዜ በጨው እንደተቀመመ ይሁን

 አነጋገራችሁ ሁሌ በጨው እንደተቀመመ ይሁን



እንደ እግዚአብሔር ቃል አነጋገሩ ሁሌ በጨው እንደተቀመመ የሚጣፍጠኝ ዴል ካርኒንግ የሚባል ሰው አለ።


አብዛኞቻችሁ ታውቁታላችሁ ፤ የመጽሐፍ ደራሲ ነው።


ምክሮቹ፣ ተግሳጾቹ እና ዘዬዎቹ በትንሽ መጽሐፍ ተሰድራ እንደ ብሉያት እና ሐዲሳት መጻሕፍት ከዘመን ዘመን ትሻገራለች።


"የጠብታ ማር" ትሰኛለች። 


በተደጋጋሚ አንብቤዋለሁ፣ ብዙ ጊዜ ገዝቼ ለሰው በስጦታ መልክ ሰጥቼዋለሁ፣ ብዙ ጊዜ ከመጽሐፍ መደርደሪያ ላይ ጠፍቶብኛል፣ ዘወትር ለምን ብዬ ጠይቃለሁ፣ ሁሌም ሳነበው አዲስ ይሆንብኛል።


ምሥጢሩ አልገባኝም።


ይኸው ዛሬም ምሥጢሩን እየፈለኩ አንድ ነገር ብልጭ አለብኝ። " እንደ አነጋገራችን አስተሳሰባችንም በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሆን ዘንድ።


በጨው የተቀመመ ነገር ከመጣፈጡም ባሻገር እንደ እናቶቻችን ሙያ ከሆነ አይበላሽም፣ ረጅም ጊዜ ይቆያል፣ ለብዙ ጊዜ የሚቆይ ረጅም መንገድ የሚያስጉዝ ስንቅ ይሆናል።


ከመቆየቱ ያለመበላሸቱ ድንቅ ነገር ነው። 


ጨው ሲንተራሱት ጸጉር የሚመልጥ ካልጣፈጠ ድንጋይ ነው ብለው የሚጥሉት ነገር እንዲህ ትልቅ ተግባር ሲኖረው እጅግ ድንቅ ነው። ዋጋውም ከማጣፈጫዎቹ ሁሉ እጅግ ርካሽ ነው።


የሰው አንደበትም፣ አስተሳሰብም፣ ቃላትም እንዲሁ ዋጋቸው ትንሽ ውጤታቸው ትልቅ የሆኑትን መተግበር ተስኖን አለማችን መራር ሆናለች።


አነጋገራችን እና አስተሳሰባችን ዘወትር በጨው የተቀመመ ጣፋጭ ይሁን። 


የትናንቱን እና የዛሬውን በማሰብ አስተሳሰባችንን ከማጥበብ ነገን እያሰብን ሐሳባችንን፣ ቃላቶቻችንን የጣፈጡ እንዲሁም ሰፊ እናርጋቸው።


ሰናይ እለተ ሰንበት ይሁንልን።

ይቆየን።


@deressereta

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...