መንፈስ ወደ ምድረበዳ ወሰደው
ልበ አምላክ ዳዊት "ወደ ቤተ እግዚአብሔር እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ" ይለናል።
ንጉስ ስለሆነ ወደ ወንዝ ዳርቻ፣ ከአለም ጥግ ሌላው ጥግ ድረስ፣ አሉ በተባሉ መዝናዎች፣ ትላልቅ አለም አቀፍ ክንውኖች ዘንድ፣ ከቤተመንግሥቱ ሕንጻ አናት ላይ ሆኖ አየር መቀበል እና ከተማውን መቃኘት፣ የቤተመንግሥቱን ጊቢ አየር መቀበል ይችል ነበረ። ደስታን ከሚፈጥሩ ክንውኖች መካከል እነዚህ ተጠቃሾች ስለሆነ።
በጌታ ደስ ይበላችሁ እንዲል ንጉስ ዳዊትን ምድራዊው ነገር አላስደሰተውም። ይልቁንም ወደ እግዚአብሔር ቤት መሄድ እንጂ የፈለገው።
መንፈሳዊነት የሚገለጥበት ሰው ከሚያዝናናው ነገር ይልቅ ነፍሱን ወደሚያጸድቀው ነገር ያደላልና።
ቅዱሳንን መንፈስ ቅዱስ ወደ ገዳም ይመራቸው ነበረ።
መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መንፈስ ወደ ምድረበዳ ወሰደው ይለናል። መንፈስ ቅዱስ ያላለው መንፈስ ቅዱስ ለአብና ለወልድ ሕይወታቸው ስለሆነ ነው አንድም የራሱ ፈቃድ ስላነሳሳው ነው።
ምድረበዳ አለ፤ ገዳም ለማለት ነው።
ወደ ገዳም ስንሄድ ከፈቃደ እግዚአብሔር ውጭ አይቻልም። ሰው ያስባል እግዚአብሔር ይፈጽማልና መንፈስ ቅዱስ ያነሳሳናል። ለመንፈስ ቅዱስ ማደሪያነት የተመቸ ሰውነት ሲኖረን።
ወደ ገዳም የመሄድ ዝንባሌ ያለው ሰው መንፈስ ቅዱስ የሚያነሳሳው ሰው ነው።
ላይሞላ ነገር የዓለም ፈቃድ ወደኋላ ይስበናል። በዚህ ቀን ደፋ ቀና ከምንለው፣ ከምንሄድበት መርሃግብር ሁሉ የሚበልጥ ለቤታችንም፣ ለሕይወታችንም፣ ለቤተሰባችንም የሚሆን የነፍስ ገበያ ገብይተን የምንመለስበት ሥፍራ ገዳም ነው።
መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶ እየመራ እግራችንን ወደ ገዳም ይውሰደን። ወደ ቤተ እግዚአብሔር እንሂድ ስንባል ከምክንያታችን በላይ ነፍሳችንን የሚያስደስት ነገር ያድርግልን።
ይቆየን
አሜን።
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ