ማክሰኞ 18 ማርች 2014

‹‹ቅዳሴ››

ያለው ዕለት ለንጋቱ ቦታውን ለመልቀቅ መሰናዶውን ያጠናቀቀ ይመስላል በቤቴ መስኮት ቀዳዳ የሚገባው የንጋት ብርሃንነግቷል ተነስ” ሚል ሰው ያህል ከፊት ለፊት በቀዳዳው እየገባ ይጎነትለኛል የጭላንጭሉን ብርሃን ተልዕኮ የሚያጨናግፈው ድብርትአይዞህ ተኛ ገና ነው” እያለ ያዘናጋኛል፤ አሁንም በመስኮቱ የሚገባው የብርሃን ጭላንጭል ገብቶ ገብቶ ቤቱን በሰፊው ተቆጣጥሮታል፣ አካላቴ ሁሉ ሳምንቱን መንገድ ሲጓዝ እንደከረመ አንጓዎቼ በሙሉ መዛል ስሜት ይሰማባቸዋል፡፡ ከሁለቱ አንደኛዋ አይኔ ብቻ ብርታት ይሰማታል እንጂ ሁለተኛዋ ጭራሽ የለችም ማለት ይችላል፤ አንደኛው ሲተኛ እርሷ ነቅታለች እርሱን ለመቀስቀስ ባደረገችው ጥረት እርሷም ድካም ተሰምቷት ማሸለብ ጀመረች የሌላት ልብሴን ገላልጣ ለመውጣት ጡንቻዋን ያፈረጠመችው ክንዴ ብርድ ሲያኮማትራት ተመልሳ ከብርድልብሱ ሾልካ ገባች ገና ተመኝታ የተገናኘች ይመስል እንቅልፍ ጣማት በዚያቹ በቀጫጫ ክንዷ ራሷን በራሷ እቅፍ አድርጋ ጋደም እንዳለች የእንቅልፍ ማዕበል ይዟት ጥርግ አለ፡፡ በልቦናዋ በብርቱው ምሽት ያሰበችው የዕለት ሰንበት የቅዳሴ መርሃግብርና ጠዋት በብርሃኑ ጭላንጭል መካከል ትዝ ላት ልቡናዋን እንደብል በልቶ ጨርሷታል ሰውነቴ ለእንቅልፍ ተማርካ ከሞቀው መኝታዋ በመሆን ቅዳሴን ታስቀድስ ጀመር፤ ልክ ከመቅደሱ ፊት እንደቆመ አስቀዳሽ አሁን ለዛለችው ገላዬ ንፍቁ ዲቆኑጸልዩ በእንተ ያበውኡ መባእ …” የሚለውን አዚሞ ሕዝቡምተወከፍ መባኦሙ ለአኃው” የሚለውን ጨርሶ ዲያቆኑ በድጋሜስግዱ ለእግዚአብሔር በፍርሃት” ብሏል የዛለው ገላዬምቅድሜከ እግዚኦ ንሰግድ ወንሴብሐከ” ብላ ሰግዳለች

ይድረስ ለመንግስታችን፡

አንዲት አገር በማደግ ላይ ካለች ችግሮች እንዳሉ ይታወቃል ህብረተሰቡም ደግሞ የሚቻለዉን ያህል ሊረዳና ችግሮችን ሊቋቋም ግድ ይላል እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ጨዋ ህዝቦች ከማንም በላይ ናቸዉ፤ ሆኖም ግን እየተካሄደ ያለዉ ግን ከመጠን በላይ እየሆነ ስለሆነ መንግስታችን እና ባለ ድርሻ አካላት አፋጣኝ የሆነ መፍትሄ እና ተለዋጭ አቅርቦቶችን ሊያቀርቡ ግድ ይላል፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ መብራት ሃይልም ሆኑ የኢትዮ ቴሌኮም ባለስልጣናት ከዚህ ቀደም አገልግሎት ለሚሰጡት ህዝባቸዉ የገቡት ቃል ኪዳን ሊጠበቅ ይቅርና ተጨማሪ ቃል ኪዳን የሚያስፈልገዉ ሆኖ እየተገኘ ያለ ሁኔታ ላይ እነገኛለን፡፡ የተቀሩትም እንደ ዉሃ እና ፍሳሽ ያሉት በብርሃን ፍጥነት እየተከተሉት ይገኛሉ ከዚህ ቀደምም አልተለዩትም፡፡ የአዲስ አበባ ነዋሪ ቁጥር ከዕለት ወደ እለት እየጨመረ መምጣቱ እየታወቀ ተመጣጣኝ የሆነ የዉሃ አቅርቦት ዝግጅት እንዳልተደረገበት መንግስታችንም የሚክደዉ ጉዳይ አይደለም፤ ምናልባት የተደረገ ተጨማሪ ነገር ቢኖር ለጽዳትና ዉበት ክፍያ ተጨምሯል በዉሃ ቢል ላይ፡፡

መብራት ኃይልና ቴሌ ግን ከዕለት ወደ ዕለት ህብረተሰቡን በብርሃንና በኔትወርክ  ማጥት ከማስመረሩ ባሻገር የዕለት ከዕለት ስራዉን እያደናቀፈበት ይገኛል፡፡ መብራት ኃያሎችም ባንድ ወቅት ካሁን በኃላ ሻማ የምታበሩት ለልደት ብቻ ነዉ  በማለት አላግጠዉብን ነበር፤ ቴሌዎችም ኦፕቲካል ፋይበሩን ዘርግተን ስንጨርስ …. … … ወዘተ ወዘተ ብለዉ ያወሩት ጉዳይ ኦፕቲካል ፋይበራቸዉ አንጀት ሆኖ ይኸዉ በኔትወርካቸዉ አንጀታችንን በክፍያቸዉ ኪሳችን እየመለጡት ይገኛሉ፡፡(ይሁን እንግዲህ እነሱን አያሳጣን ማንን እናማ ነበር አንድም ማን ላይ ቁጭብለሽ ማንን ታሚያለሽ እንዲሉ…..)
ክቡር መንግስታችን የሆነዉስ ሆነና፡-

ዓርብ 14 ፌብሩዋሪ 2014

የቤቱ ስርአት


ሰወቹ እጅግ የተከበሩ እንዲያዉም ለምድር ለሰማይ የከበዱ ፣ የታፈሩ፣ ባእለጠጋ፣ሳርቅጠሉ አንቱ እያለ የሚያከብራቸዉ፣እነርሱን በመንገድ እንዃን ሰዉ ቀድሞ የማይሻገራቸዉ፣በእግሩ የሚሄድ ቆሞ፣ በፈረስ ያለዉ ወርዶ እጅ ነስቶ አክብሮ የሚሸኛቸዉ፣የሰዉ ፍቅር እንደ ምድር አሸዋ የበዛላቸዉ፣… ሁለት ሰዎች ነበሩ በትዳር ምሥጢር አንድ የሆኑ፤ መቸስ ላለዉ ይጨመርለታል ነዉና

ዋሊያዎቹ


የከሳቴ ብርሃን ተሰማ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ዋሊያ የሚለዉን ቃል በሁለት መልኩ ይፈታዋል፤

1ኛ. መጠንዋ ከወፍ ላቅ ከዶሮ ዝቅ ያለች ላባዋ ቡላ ሆድዋ ነጭ መብልዋ ማሽላ አዳርዋ ከዛፍ ላይ ነዉ፡፡

2ኛ. የበረሐ እንስሳ በእያንዳንዱ ቀንድ ላይ ብዙ ቀንድ የሚያበቅል፡

በማለት ይገልፁታል፡፡

ወክፒድያ የተባለዉ ደግሞ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኝ የአይቤክስ ዝርያ ይለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ወክሎ በእግር ዃስ የሚጫወተዉም ቡድን ስያሜዉን ያገኘዉ ከዚህ ብርቅዬ እንስሳ በመነሳት ዋሊያ ብርቅዬዉ በሰሜናዊዉ በረሐማ እና ተራራማ ስፍራ የሚኖር የኢትዮጵያ ኩራት እንደመሆኑ እነዚህም ተጫዋቾች ተራራ ሸለቆ ሜዳ ገደል ሳይሉ በየብስ እና በአየር ላይ እየተጓዙ አገርንና ህዝብ ስም የሚያስጠሩ የኢትዮጵያ ኩራቶች ናቸዉ፡፡

በአካለ መጠን ያልገዘፉ ከማንም ግን የማያንሱ በጥበብ የተካኑ እለት እለት በብቃት እየበለፀጉ ያሉ ከ31 ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያን ታሪክ ለመቀየር የበቁ ጀግኖች መጠሪያ ነዉ፤ ለዓለምም ሆነ ለወገኖቻቸዉ ብርቅ የሆኑ ታሪክ የማይዘነጋቸዉ ድልን የተቀናጁ ታሪክን የፃፉ ናቸዉ፤ ዋሊያዎቹ፡፡

ዋሊያዎቹ ከዚህ ቀደም ለ20ኛዉ ዓለም ዋንጫ ዝግጅት የተለያዩ ፍልሚያዎችን ማድረጋቸዉን መዘገባችን የሚዘነጋ አይደለም፤ ከአፍሪካ ምርጥ 10 አገሮች አንዷ ሆና በስተ መጨረሻ ደግሞ ለዓለም ዋንጫዉ ፍጥጫ ለመሳተፍ ከአቻዋ ከናይጄሪያ ጋር ተመድባ በደርሶ መልስ ጨዋታ በጨዋታና በተለያዩ ምክንያቶች ከዉድድሩ በሽንፈት ተገላለች፡፡ ይህንንም የመጀመሪያዉን ግጥሚያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደጋፊዉ ፊት በኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ስታድየም ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ መካሄዱ ግድ ቢለንም ሽንፈቱ ተስፋችንን አላሟጠጠዉም ነበር እዛዉ ናይጀሪያ ላይ ተስፋ ይኖረናል የሚል ዕድል ነበርና እስከዚያች ቀን ድረስ ኢትዮጵያዉያን በመላዉ ዓለም እንደ ድር አብረን ዋልያዎቹን ስንደግፍ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ዉጤቱ አስደንጋጭ ቢሆንም … …

ዋሊያዎቹ ለ20ኛዉ የዓለም ዋንጫ የመጨረሻዉን የማጣሪያ ጨዋታ ከአቻዉ የናይጀርያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ደርሶ መልስ ጨዋታን በማድረግ ድል ከቀናዉ ለዓለም ዋንጫዉ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዉን ጉዞ ወደ አዘጋጅ አገርዋ ብራዚል ያደርግ ነበር ግን አልሆነም፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከአቻዉ ከናይጄሪያ ቡድን ጋር ወደ ሰባት ጊዜ ተገናኝተዉ አምስቱን ድል በመደረግ አንዱን አቻ በመዉጣት አንዱን በበላይነት ተለያተዋል፡፡ ያ ሁሉ አልፎ በዘመናችን ያላየነዉን ድል ያሳየን፣ እግር ኳስን እንደምንችልና አይደለም ለአፍሪካ ለዓለም ዋንጫ መቅረብ እንደሚቻል ያሳየን እና ያሳመነን የዘመናችን የእግር ኳስ ጀግና የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰዉነት ቢሻዉ ዋልያዎቹ ከዓለም ዋንጫ መሰናበትን ተከትሎ እና ከዚያም በኃላ በተደረጉት ዉድድሮች ሰበብ ጨዋነት በጎደለዉ ስርአት፣ ዉለታዉን በዘነጋ ድርጊት፣ የርሱንም ሆነ የስፖርት ቤተሰቡን ልብ በሚሰብር ሁናቴ በጨዋ ደንብ ቁጭ ብለዉ ሳይነጋገሩ እና ሳይመካከሩ ከአሰልጣኝነት እንደሸኙት እሱም እኛም ከሚዲያ ሰማን (አቶ ሰዉነት እንዳለዉ)፡፡ ለመሆኑ እነዚህ ሰዎች ህዝብ መርጦ እስካስቀመጣቸዉ ድረስ ያለ ህዝብ ተሳትፎ እና ዉይይት ምንም እንኳን ቢደክም ዉጤቱ ባያምር የትላንትናዉን አንበሳችንን ጀግናችንን እንዲህ እንደ ደሃ መቃብር ለማሰናበት ፈጠኑ? ሰዉነት እኮ እኛን ብቻ አልነበረም ያስደሰተዉና ያስፈነደቀዉ ዓለማችንን ያሳየን ከሰዉ እኩል በኣለም መድረክ እንድንጣወቅ ባንዲራችን እንዲዉለበለብ ያደረገዉ እነሱንም ጭምር እንጂ (የፌዴሬሽኑን ሰዎች ጨምሮ)፡፡  

በእዉነት ሰዉ ሳያዘጋጁ እሱን ማባረር ያስፈለጋቸዉ ምስጢሩ ምን ይሆን?

ያኔ አይዞህ በርታ ከጎንህ ነን ድል ይቅናህ  ጀግናችን ነህ ያሉት ባለስልጣኖቻችን ዛሬ ሲባረር ወዴት ይሆኑ?

እንደሆነ ከጥቁር አበሻ እስከ ነጭ ፈረንጅ ድረስ ቀያይረን አሰልጣኝ አምጥተን ነበረ ነገ ደግሞ ማን ይመጣ ይሆን?

የሰዉነታችንስ መድረሻስ ወዴት ይሆን?

እኛንማ ቅስማችንን ሰብረዉ ጥለዉናል፤ ሰዉነት ለምን ተነሳ ዘለዓለሙን ይቀመጥ የሚል ከንቱ አመለካከት የለኝም አቶ ሰዉነት ራሱም እንዲህ አይነት አቋም እንደሌለዉ ለዉጥ እንደሚያስፈልገን በአደባባይ ተናግሯልና እኔም እንዲሁ ለዉጥ እፈልጋለሁ፡፡ የሚመጣዉ ግን የሚበላ እና የማያበላ ለዉጥ ለማምጣት ብቻ ይሁን፡፡ ቸር ይገጠመን ለእግር ኳሳችን ዳግም ትንሳኤ ይሁንለት፡፡

ሰኞ 20 ጃንዋሪ 2014

በዓላትና አከባበራቸዉ



በዓላትና አከባበራቸዉ
ወደ አዲስ ዓለም ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ለማቅናት 12፡00 ሰዐት ከመኖሪያ ሰፈሬ የመገናኛ ታክሲ በመያዝ ጉዞዬን ከጀመርኩ ከ1፡15 ሰዓት በኃላ ጦርኃያሎች ደረስኩ፤ ከጦር ኃይሎች 18 በመባል ወደ ሚጠራዉ ሰፈር በመጓዝ ላይ እያለሁ አደባባዩን ሳልሻገር መዳረሻዉ ላይ ወቅቱ የጥምቀት ወቅት ቀኑም የጥምቀት ዋዜማ (ከተራ) ነበርና፡፡ በዚህ ዘመን ወጣቱ ትዉልድ የሃይማኖተኝነት (በዓልን የማክበር )ሞራሉ የተነቃቃበት ወቅት ነዉና የተለያዩ ባነሮችን፣ሰንደቅ ዓላማዎችን፣የታቦቱ መዉጫ መግቢያ ላይ ሻማዎችን ማብራት ፣ የተለያዩ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶችንና መፈክሮችን አሳትሞ ቲሸርቶችን መልበስ የጥምቀት በዓል መድረሱን ማብሰሪያ ምልክቶች ናቸዉ፡፡

ሰኞ 30 ሴፕቴምበር 2013

መስቀል ክፍል 3



ባለፈዉ በሁለት ተከታታይ ክፍል ስለ ቅዱስ መስቀል ተመልክተን በክፍል ሦስት እንደምንገናኝ ተቀጣጠረን ተለያይተን ነበር እግዚአብሔር ፈቅዶ አባቶቻችን እና ወንድሞቻችን በቃልና በመጽሐፍ ያቆዩልንን ትምህርት ሳልጨምር ሳልቀንስ ለንባብ እንዲመች በክፍል በክፍል አቅርቤላችኋለሁ፤ ክፍል ሦስት እነሆ! በክፍል አራት ያገናኘን፡፡

3ኛ. ቅድስት እሌኒና መስቀለ ክርስቶስ
ጌታችን መድሓኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ በሐዋርያት ስብከት የወንጌሉ ፋና ለዓለም ሲበራ በዕፀ መስቀሉ ልዩ ልዩ ተአምራት ይደረጉ ነበር፡፡ አስቀድመዉ ጌታን የሰቀሉ አይሁድ አሁን ደግሞ በሰቀሉበት መስቀል ተአምራት ሲደረግ በማየታቸዉ በቅንአት መስቀሉን ከኢየሩሳሌም አጠገብ ቀብረዉ በአዋጅ ቆሻሻ በየእለቱ እንዲደፋበት አደረጉ፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ሥራዉን የሚሰራበት የራሱ ጊዜ አለዉና በ327ዓ.ም. የታላቁ ንጉስ የደጉ ቆስጠንጢኖስ እናት ንግስት እሌኒን አስነሣ፡፡ እርሷም አስቀድማ ከአረማዊዉ ንጉስ ቁንስጣ የወለደችዉ ልጅዋ ክርስቲያን ከሆነላት ከቁስጥንጥንያ ወደ ኢየሩሳሌም ተሻግራ የጌታችንን ዕፀ መስቀል ልታወጣ ብፅዐት ገብታ ነበር፡፡ በልዑል እግዚአብሔርም ፈቃድ ልጅዋ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ስለሆነላት በመስከረም 17 ቀን ቁፋሮዉን አስጀምራ መጋቢት 10 ቀን አወጣችዉ፡፡
መስቀሉ የተቀበረበት ቦታ ለ300 ዓመታት ያህል ቆሻሻ እየተደፋ ስለተከመረበት ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ ነበር፡፡ ነገር ግን በወቅቱ በኢየሩሳሌም በነበረዉ አበዉ መሪነት ደመራ አስደምራ፣ ዕጣን አስጨምራ፣ ጸሎት ስታስደርግ የዕጣኑ ጢስ ወደ ላይ ወጥቶ መስቀሉ በተቀበረበት ቦታ ላይ ሰገደ፡፡ በጢሱ ምልክትነትም ቦታዉ ስለታወቀ ለሰባት ወራት ያህል ተራራዉ ተቆፍሮ ሊወጣ በቅቷል፡፡ ዛሬ በክርስቲያኖች ዘንድ ደመራ የሚደመረዉም ይህንኑ ለማስታወስ ነዉ፡፡
መስከረም 17 ቀን ወይም በዋዜማ፣ በዓለ መስቀሉን ስናከብር ከመስቀሉ ቀጥለን የምናስባት ቅድስት እሌኒ ናት፡፡ ቅድስት ዕሌኒ የመስቀሉ ጥበብ ተገልጾላት ክብሩና ሞገሱ በግልጽ ታይቶአት፣ መድኋኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን ቅዱስ መስቀል የት ባገኘሁት እያለች ለብዙ ጊዜ ታስብና ትመኝ ነበር፡፡ በተለይም ልጄ መምለኬ እግዚአብሔር ንጉስ ቈስጠንጢኖስ፣ መክስምያኖስ ከሚባል ጠላቱ ጋር ሲዋጋ፣ …

ዓርብ 27 ሴፕቴምበር 2013

መስቀል ክፍል ሁለት

2ኛ.መስቀል ከቀራንዮ በኋላ


ብዙ ሰዎች መስቀልን የማክበራችን ምሥጢር ማወቁ ይሳናቸዋል፣ይከብዳቸዋል ፣ይፀናባቸዋል፡፡ እኛ ግን መስቀልን የምናከብረዉ ስላከበረን ነዉ፡፡ክብር ምስጋና ይግባዉና አካላዊ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ መስቀልን ታግሶ በደሙ ክሶ፣ በቀራንዮ ዉሎ ዓለምን ከቀደሰልን በኋላ፣ መስቀል የርግማን፣ የኋፍረትና የኋጢያት ምልክት መሆኑ ቀርቶ
መስቀል መርገመ ኦሪት የተሸረበት፣ ሰላምና ነጻነት የታወጀበት፣የኛ ድህነት ፣ የበረከትና የነፃነት አርማ፣ የወለወደ እግዚአብሔር ክርስቶስ የሰለም ዙፋን ሆኖ ዓመተ ፍዳ እና ዓመተ ኩነኔ ተሸሮ ዓመተ ምህረት የታወጀበት የነፃነት ዋስትናችን ነዉ፡፡ ለዚህም ቅዱስ ጳዉሎስ፡- «ወለነሰ ተሣየጠነ ክርስቶስ እመርገመ ለኦሪት በዘወጽአ በእንቲአነ ወጾረ መርገማ፣እኛንስ ክርስቶስ በኦሪት መርገም ዋጅቶናል፡፡ ስለኛ ሕግን በመፈጸሙና የኦሪትን መርገም በመሸከሙ፡፡» ብሏል፡፡ ገላትያ 3፡13
በነብዩ « ዉእቱ ነስኣ ደዌነ ወፆረ ሕማማነ በእንቲአነ ሓመ፣ወንሕነኒ ርኢናሁ ሕሙመ ወዉእቱሰ ቈሰለ በእንተ ኋጢአትነ ወሐመ በእንተ ጌጋይነ ፤ ትእምርተ ሰላምነ፤ ወበቁስለ ዚአሁ ሐየወነ ቁኢስለነ፡፡»
እሱ ደዌያችንን ገንዘብ አደረገ፣ ሕማማችንንም ተሸከመ ስለ እኛም ታመመ እኛ ታሞ በመከራም ተጨንቆ አየነዉ፡፡ እሱ ግን ስለ ኋጢያታችን ቈሰለ ስለበዳላችንም ታመመ፣የፍቅር የአንድነታችንም (የሰላማችንም) ምልክት እሱ ነዉ፡፡ በእሱ ቁስልም ከቁስላችን ዳንን … …፡፡ ተብሎ ተጽፎ ነበርና ትንቢት እንዲሁም ኦሪታዊ መርገመ መስቀል እንዲያከትም አምላክ ወልደ አምላክ ደዌያችንን ተሸክሞ በቀራንዮ ዋለልን፡፡ት.ኢሳይያስ53፡4-5 ዮሓንስ 19፡1-42
ቅዱስ ጳዉሎስ ለሮሜ ሰዎች በጻፈዉ መልዕክቱ ምዕራፍ 8፡3 ላይ «ወኮነና ለይእቲ ኋጢያት በነፍሰቱ ኋጢአትን በሰዉነቱ ቀጣት፡፡»ያለዉን እንደነ ቅዱስ አትናትዎስ የመሰሉ አበዉ ሊቃዉንት ደግሞ
«ወአስተሐፈረ ኋጢአት በዲበ ምድር፤ ወአበ ጠለ ሞተ በዉስተ ሲኦል ወሰዐረ መርገመ በዲበ ዕፀ መስቀል ወነሰተ ሙስና በዉስተ መቃብር፡፡ወዘኢየሐምም ሐመ በሥጋ ሐማሚ ተዋህዶ ቃል ምስለ ሥጋ ወገብረ ዘንተ ከመይፁር ሕማመ ዚአነ ወያእትቶ እምኔነ ወየሀበነ ዘዚአሁ ሕይወተ፤ ወአዕረገ ርእሶ መሥዋዕተ በእንቲአነ»
በምድር ላይ ኋጢአትን አሰፈረ፤ በሲኦልም ሞትን አጠፋ፤በመስቀል ላይ መርገምን ሻረ፤ በመቃብር ዉስጥም ሙስና መቃብርን አጠፋ፡፡ የማይታመመዉ በሚታመምዉ ሥጋ ታመመ ቃል ከሐማሚ ሥጋ ጋር ተዋሐዶ ሕማምን ከሥጋ ያርቅ ዘንድ፣ ከእኛም ያርቀዉ ዘንድ የርሱንም ሕያወት ይሰጠን ዘንድ ይህን አደረገ፡፡ስለኛም ራሱን መሥዋእት አድርጎ አቀረበ በማለት ይገልጹታል፡፡
ሃይማኖተ አበዉ ዘቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ 30፡40 ንፁሐ ባህርይ ክርስቶስ ከሥራዉ ስህተት ከአንደበቱ ሐሰት ሳይገኝበት፣ በኋጢአተኞች ዘንድ፣ ኋጥእ በደለኛ ተብሎ መስቀል ላይ ዋለ መባሉ እዉነት ነዉ፡፡ሆኖም ክርስቶስ መስቀል ላይ የዋለበት አንድ ዐብይ ምክንያት እንዳለ ግን መዘንጋት የለበትም፡፡ይኸዉም ዕዳ በደላችንን ደዌ ኋጢአታችንን ተሸክሞ በደሙ ካሣ መርገማችንን ሽሮ ከኋጢአት ባርነት ነፃ ያወጣን ዘንድ መሆኑን ነዉ፡፡ ስለዚህም፤

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...