እሑድ 12 ጃንዋሪ 2020

ዳንኤልን እንኳን ሰዉ ሰይጣንም ይፈራዋል፤(special)


ነብዩ ዳንኤል ላይ ሹማምንቱ ለምን አሴሩበት?
ሹማምንቱ ንጉሡን ወጥመድ ዉስጥ ማስገባት ለምን ፈለጉ?
ዳንኤል ለምን ከነሱ የተለየ አቋም ኖረዉ?
የዳንኤል ከሹማምንቱ የተለየ አላማዉ ምንድን ነዉ?
ነብዩ ዳንኤል እዉን በሹማምንቱ ወጥመድ ይወድቅ ይሆን?
ንጉሡሥ በነብዩ ዳንኤል ላይ ዉሳኔዉ ምን ይሆን?
ዳንኤል መጨረሻዉ ምንድን ነዉ?
ዳንኤል ያቺ ሰላሳ ቀን እስክታልፍ ድረስ የልቡን እግዚአብሔር ስለሚያዉቀዉ እነሱ ያሉትን ለምን አይፈፅምም?
ዳንኤል ሹማምንቱ እንዳሉት በእጃቸዉ ቢወድቅ ሕጉ ቢፀናበት እንዴት ያልፈዋል?
እነዚህንና ሌሎችን ጥያቄዎች ቀጣይ ክፍል ይመልሰዋልና ይጠብቁን፡፡

ሐሙስ 2 ጃንዋሪ 2020

ዳንኤልን እንኳን ሰዉ ሰይጣንም ይፈራዋል፤ (ክፍል ሁለት)


መፅሐፍ ስለምርኮ በሚናገረዉ በዘመኑ ስለተደረጉት ዋና ዋና ድርጊቶች ሲተርክ በባቢሎን በስደት መኖርን ሲያነሳ ታላላቅ ሰዎች ብሎ ካነሳቸዉ መካከል ሕዝቅኤልና ዳንኤል ተጠቃሾች ናቸዉ፡፡

ብልጣሶር፡- ትርጉሙ ቤል (የባቢሎን ጣኦት) ንጉሥን ይጠብቀዉ ማለት ነዉ፤ ትንቢተ ኢሳይያስ 46÷1
1)    የናቡከደነፆር የልጅ ልጅ የናቡናዲስ ልጅ፡፡ የአዲሲቱ ባቢሎን መንግሥት የመጨረሻ ንጉሥ፡፡
በመጠጥ ግብዣ ጊዜ በቤቱ ግንብ ላይ ፅሕፈት የምትፅፍ እጅ ታያቸዉ ፅሕፈቱም ፡- ̎ማኔ ቴቄል ፋሬስ̎ የሚልነበረ፡፡
ንጉሡም ደንግጦ ትርጉሙን ሲፈልግ ዳንኤል እንዲህ ብሎ ተረጎመለት፡፡
̎ እግዚአብሔር መንግሥትህን ቆጠረዉ፣ ፈፀመዉ፣ በሚዛን ተመዝነህ ቀለህ ተገኘህ፤ መንግሥትህም ተከፈለ ለሜዶንና ለፋርስ ሰዎችም ተሰጠ፡፡̎ ዳንኤል 5÷25-28
በዚያ ሌሊት የባቢሎን መንግሥት በፋርስ እጅ ወደቀ፡፡ ይህም የሆነዉ በ539 ከክርስቶስ ልደት በፊት ነዉ፡፡ ዳንኤል 5÷1-30፣ 8÷1
  
2)    ለዳንኤልም የተሰጠ ሥም ነዉ፡፡ ዳንኤል 1÷7 በሥም እኩል በግብር ሥንኩል ማለት እንዲህ ነዉ፡፡

ዳንኤል ማን ነዉ?
የስሙ ትርጓሜ ፡- ̎ እግዚአብሔር ፈራጅ ነዉ̎ ማለት ሲሆን
ትዉልዱ፡- መጻሕፍት እንደሚሉት የተወለደዉ በ618 ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ነዉ፡፡ ትዉልዱም ከይሁዳ ነገድ  ስለሆነ ከንጉሳዊ/ከመሳፍንት ቤተሰብ እንደሆነ ይገመታል፤ የዮናኪር የልጅ ልጅ ነዉና፡፡ ምነዉ ቢሉ ዮናኪር የንጉሡ የኢዮአቄም (የእስራኤል ንጉሥ) ልጅ ስለሆነ፡፡ የኢዮአቄም ዘመነ ንግሥናዉም ከ609 እስከ 598 ከክርስቶስ ልደት በፊት ማለት ሲሆን የነገሠዉም በ18 አመቱ እንደሆነ ይነገራል፡፡ አንዳንዶችም በ25 አመቱ እንደነገሠ ይናገራሉ፡፡ ዳንኤል ግን መሾሙን መጽሐፍ ይናገራል፡፡  ዳንኤል 1÷6

ማክሰኞ 31 ዲሴምበር 2019

"ዳንኤልን" እንኳን ሰው ሠይጣንም ይፈራዋል ( ክፍል አንድ )

"ዳንኤልን" እንኳን ሰው ሠይጣንም ይፈራዋል
12 ምእራፍ እያንዳንዳቸው ትንሹ 13 ቁጥር ሲኖረው ትልቁ 49 ቁጥር አለው። በአማካይ አንድ ምእራፍ 30 ቁጥር ይኖረዋል።
የመጽሐፉ ክፍል "የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም በነገሠ በሶስተኛው አመት የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ከበባት።" ብሎ ይጀምርና። " አንተ ግን እስከ ፍጻሜው ድረስ ሂድ አንተም ታርፋለህ: በቀኑም መጨረሻ በእጣ ክፍልህ ትቆማለህ።" በማለት ይዘጋዋል።
የሥሙ ትርጓሜ " እግዚአብሔር ፈራጅ ነው " ማለት ሲሆን የተረጎማቸው ሕልሞችና ያያቸውን ራእዮች ብዙ ምሥጢር ያለባቸው ከመሆኑ የተነሣ ብዙዎች አይስማሙበትም።
አላማው እኔ ልግነን፣ ልታወቅ፣ ብዙ ተከታዮች ይኑሩኝ፣ አድናቆትን ላትርፍ፣ ወዘተ ... አይደለም። እግዚአብሔር እና ሕዝቡ እንደሚያሸንፍ ለመግለጥ እንጂ።
የመጽሐፉ ክፍሎች በአሥር የተከፈሉ ሲሆኑ በአብዛኛው የሚያወሩት ስለ ምርኮ፣ ሕልም፣ ትርጉም፣ አራት መንግሥት፣ ጦርነት፣ ስለ እግዚአብሔርም ሕዝብ መከራ ... ወዘተ ነው።
"ዳንኤልን" እንኳን ሰው ሠይጣንም ይፈራዋል::
በይፋ ተጀመረ።
ይቆየን።

ከትናንት እስከ ዛሬ …

በነገራችን ላይ   ከ ፈረንጆቹ Thursday, March 22, 2012 እስከ ዛሬይቱ ቀን ድረስ ………. 


https://deressereta.blogspot.com/

የደረሰ ረታ እይታዎች የፀሐፊዉ ያላሰለሰ ስንፍና እንዳለ ሆኖ በአገራት ኢትዮጵያና አሜሪካ እንደ ቅደም ተከተላቸዉ ብዙ አንባቢያን ያሉበት ሲሆን በመቀጠል ኬንያ፣ ሩሲያ እና ኢንዶኔዥያ ከ1 እስከ 3 ያለዉን ተራ ይይዛሉ፡፡
ከሚለጠፉት ፅሑፎች ደግሞ ትልቁን የቀዳሚነት ድርሻ የያዘዉ ፍቅር በፌስቡክ ክፍል ሁለት ሲሆን አጋጣሚ ክፍል አራት እና ለመጪዉ ትዉልድ ልማትን እንጂ ልመናን አናወርስም የሚሉት ሁለተኛ እና ሶስተኝነትን ይይዛሉ፤ እኔን በስነ ፅሑፍ ዘመኔ እጅግ ዋጋ ያስከፈለኝ እና በወቅቱ ከ1500 በላይ ኢ-ሜይል የተቀበልኩበት እና አንባቢ ያገኘዉ ብዙ ጊዜም ሲመራ የቆየዉ ዋጋ የሚያስከፍሉ ጥፋቶች

ሰኞ 16 ዲሴምበር 2019

የጊዜ አጠቃቀም


የጊዜ አጠቃቀም


መግቢያ

ስኬታማ የጊዜ አጠቃቀም ያዳበረ ሰራተኛም ሆነ ግለሰብ ጊዜዉን በመርሃግብር እና በዕቅድ ይመራል፤ ይህ ሰዉ ህይወቱን የሚመራዉ በዕድል ሳይሆን ራሱ ነዉ፡፡ ስለዚህ ይህንን ዶክመንት ማዘጋጀት ግድ ሆኗል፡፡

ጊዜ -

በቀን 24 ሰዓት

በሳምንት 7 ቀን

በወር 30 ቀን

በዓመት 52 ሳምንት/ 365 ቀናት/ ብለን የምንጠራዉ ማለት ነዉ፤

ጊዜ ከሁሉ ነገር በላይ እጅግ የሚያስፈልገን ነገር ሆኖ ሳለ ከሁሉ ነገር በላይ በተበላሸ ሁኔታ የምንጠቀምበት ነገር ነዉ፤

ዊሊያም ፔን

                                    ዓላማ -

v የተቋማትን ፣አልያም የአገራችንን፣ ከዚያም አልፎ የየራሳችንን፣ ወዘተ … “የተለጠጠእቅድ ለማሳካት ዋነኛ ሃብት ጊዜ በመሆኑ ጊዜያችንን በመጠቀም ዉጤትን እንድናመጣ ግብን እንድናሳካ ግንዛቤ ለመፍጠር ነዉ፡፡


 የጊዜ አስፈላጊነት (ጥቅም)


Ø  ለመዉጣት ለመግባታችን የምንጠቀምበት

Ø  በመዉጣት በመግባታችን ዉስጥ የምናከናዉናቸዉን ነገሮች የምንፈፅምበት መሣሪያ

የአንድ ዓመት ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ክፍሉን የደገመን ተማሪ ጠይቀዉ

 የአንድን ሰዓት ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ለመገናኘት የተቀጣጠሩ ትኩስ ፍቅረኞችን ጠይቃቸዉ

የአንድን ደቂቃ ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ አዉቶቡስ ለትንሽ ያመለጠዉን ሰዉ ጠይቀዉ

v  ያለ በቂ ምክንያት፣ ከአቅማችን በታች በሆነ ጉዳይ ከሥራ ላይ የቀረንባቸዉ ቀናት ምን ያህል ግባችን ላይ ተፅዕኖ እንደፈጠሩ እንመልከት፤

የአንድን ሰከንድ ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ከአደጋ ለጥቂት ያመለጠን ሰዉ ጠይቀዉ

ረቡዕ 31 ጁላይ 2019

ስኬት/Success/


ስኬታማ መሆን ይፈልጋሉ?
Believe That Success Is Your Birth Right
የስኬት ህጎች
መጀመሪያ ሊያዉቋቸዉ የሚገባዎትን ጠንቅቀዉ ሳያዉቁ ስኬታማ ለመሆን አስበዉ ያዉቃሉ?
ስለስኬት ህጎች ሳያዉቁ ስኬታማነትን ማሰብ ፡- ስለማሽከርከር ህግ ሳያዉቁ እና የመንገድ ደህንነት ህጎችን ሳይረዱ መኪና እንደማሽከርከር ይቆጠራል፡፡ ሆኖም ስኬት የምርጫ ጉዳይ እንጂ በሌላ ሰዉ የሚጫኑት አይደለም፡፡
የስኬትን ህግ ካወቁና ከተገበሩ ስኬታማነትን ባይፈልጉ እንኳን የተሳካለት ሰዉ ነዎት፡፡ የተለያዩ የሰዉን ልጅ ለስኬት የሚያበቁ ክንዉኖች አሉ የእርስዎ ስኬት የትኛዉ እንዲሆን ይፈልጋሉ?
Ø  ሃብት ፡- የገንዘብ ብዛት ከአስተሳስብ ድኅነት አያድንምና የእርስዎ ሃብት ምን እንዲሆን ይሻሉ?
Ø  ዕዉቀት፡- ወደ ተግባር የማይለወጥ ዕዉቀት የጋን ዉስጥ መብራት ነዉና የእርስዎ እዉቀት ለርስዎ እና በዙሪያዎ ላለዉ ምንድን አደረገ?
Ø  ጥበብ፡- ጥበብን መፈለግ እንቁን ከመፈለግ በእጥፍ ይሻላል እርስዎ ጥበብን ለመፈለግ ምን ያህል ዋጋ ይከፍላሉ?
Ø  ትዳር/ቤተሰብ፡- ቤተሰብ የአገር መሰረት ነዉና ትዳሮትን ምንድን ላይ ነዉ የመሰረቱት አለት ላይ ወይንስ አሸዋ ላይ?
Ø  ስራ፡- ዕለት ተዕለት ጥሮ ግሮ የሰዉ ልጅ ህይወቱን እንዲመራ የአምላክ ትዕዛዝ ነዉ እርስዎ ስራዎን ሲሰሩ ዉጤታማ ለመሆን ነዉ ስራዎን ለማጠናቀቅ ብቻ ነዉ የሚሰሩት …
Ø  ወዘተ …

1.    የመፈለግ ህግ
"አንድን ነገር እጅግ ጠንካራ በሆነ ፍላጎት ከፈለጉት እንደሚያገኙት አይጠራጠሩ ፤"
Ø   ንካራ ፍላጎት የስኬት መነሻ ሲሆን እንዲሁም ግብን ያሳያል አንድ ሰዉ ጠንካራ ፍላጎት ካለዉ በልቡ የሞላዉን ፍላጎቱን ለማሳካት ይጥራል፤ ያሳካዋልም፡፡
Ø  ንካራ ፍላጎት ነገሮችን በድል ለመስራት ትልቅ ሃይል ነዉ፤ (እኤአ 2000 ላይ ኃይሌ ገብረ ስላሴ በሲዲኒ ኦሎምፒክ ህመሙን ታግሶ አንደኛ በመዉጣት ያሸነፈዉ ፖልቴርጋት ቀሽም ስለሆነ ወይንም ተወዳዳሪ ስላልነበረ ሳይሆን ኃይሌ የማሸነፍ ጠንካራ ፍላጎት ስለነበረዉ ነዉ፡፡ለኃይሌ መሸነፍ ወይም ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ማጠናቀቅ አማራጭ አልነበረም / አይደለምም) ፤ ለጊዜዉ ስሙን የማላስታዉሰው የጦር ጀነራል የነበረ አንድ ሰዉም የሀገርን ዳር ድንበር ለማስከበር ተልዕኮዉን ለመወጣት ሰራዊቶቹን ይዞ ባህር አቋርጦ በሄደ ጊዜ የተሻገረበትን መርከብ በማቃጠል እና ድልድዩን በመስበር ነበር ጦርነቱን የጀመረዉ ምክንያቱም ጠላትን ድል ሳያደርግ የሃገርን ዳር ድንበር ሳያስከብር ወደ ኋላ የመመለስ ህልም አልነበረዉምና፤ ጠንካራ ፍላጎቱ ድል እንጂ ወደ ኋላ መሸሽ/መመለስ አልነበረምና ነዉ፡፡ መርከቡ እና መሸጋገሪያዉ ድልድይ ቢኖር ፈሪዎች ወደ ኋላ መመለስን እንደ አማራጭ ይጠቀሙበት ነበርና ነዉ፡፡ ስለዚህ እኛም ወደ ኋላ የሚመልሱንን ከስኬት ከተሻለ ለዉጥ ወደ ኋላ የሚያሰቀሩ መንገዶችን ልናቃጥል አዉጥተን ልንጥል ይገባናል፡፡
Ø  ኞትና ተራ ፍላጎት ስኬትን አያስገኙም፤ ምኞት ማለት የቀረበን እንጀራ

ማክሰኞ 30 ጁላይ 2019

COMPETENCY/ ብቃት/ክፍል ሁለት/


ክፍል አንድን ለመዳሰስ እንደሞከርነዉ ሁሉ ክፍል ሁለትን እንዲህ እንቃኘዋለን፤ መልካም ንባብ፡፡
2.5.  የሰብአዊ ግንኙነት ክህሎት #
አንድ ተቋም የሚፈጠረዉ እና የሚንቀሳቀሰዉ በሰዉ ነዉ፤ በእርግጥ ለሰዉ ሥራ ማቀላጠፊያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ቁሳቁሶች ሰወችን ይደግፉ ይሆናል እንጂ በራሳቸዉ ሰዉን አይተኩም፡፡ ስለሆነም በየትኛዉም የስልጣን እርከን ይሁን በየትኛዉ የስራ መስክ ላይ የሚሰራ ሰራተኛ የሰብአዊ ግንኙነት (የሰዉ ለሰዉ ግንኙነት) ክህሎት አካል የሆነዉን የስሜት ብልህት (Emotional Intelligence/Quotient) ሊያዳብር ይገባዋል፡፡
  Øአንድ መሪ የግሉንና የሌሎች ሰዎችን ስሜት የማወቅና የመቆጣጠር እንዲሁም ለራሱና ለሌሎች ሰዎች ስሜት ሊሰጥ የሚገባዉን ትክክለኛ ምላሽ ለይቶ የማወቅ ግላዊ እና ማኅበረሰባዊ ብልት ችሎታ ሊኖረዉ ይገባል፡፡
የሰብአዊ ግኙነት ማለት መሪዉ የሚመራዉን ሰራተኛ በአግባቡ ስሜቱን የማወቅ እና የመረዳት ችሎታ ሲሆን ሰራተኛዉ ደግሞ የሚያስተናግደዉን ደንበኛ፣ አብሮት የሚሰራዉን ሰራተኛ፣ እንዲሁም የሚመራዉን የቅርብ አለቃዉን ስሜት የመረዳት ችሎታ ማለት ነዉ፡፡ ይህ ካለ መሪዉ ሰራተኛዉን የማበረታታት፣ ለስራ የማነሳሳትን፣

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...