ሐሙስ 29 ኦክቶበር 2020

ሁለት ምርጫ አለን

 ሁለት ምርጫ አለን

ደረሰ ረታ
19/2/2013

ሕጻናት ንጽሕ ናቸው፤ ለዚህም ነው ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋእለ ሥጋዌው ስለ መንግሥተ ሰማያት ሲያስተምር " እንደ ሕጻናት ካልሆናችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት አትወርሱም" ሲል ያስተማረው።

ሕጻናት:-
ከእናት እና ከአባታችሁ ማንን ትወዳላችሁ?
ከከረሜላ እና ከቸኮሌት የቱን ትመርጣላችሁ?
ከእናት ከአባት ከእህት ወንድማችሁ ማንን የበለጠ ትወዳላችሁ?
ወዘተረፈ
ተብለው ለምርጫ ሲጠየቁ
እናቴንም አባቴንም፣
ከረሜላም ቸኮሌትም፣
እናቴንም አባቴንም እህት ወንድሜንም ይሏችኋል።
ደግማችሁ ከሁለቱ አንዱን ምረጡ ብላችሁ ስታስገድዷቸው ሁሉቱንም/ሁሉንም ብለው ድርቅ ይላሉ። ሕጻናት ንጽህ ናቸውና። እምቢ ብትሏቸው እንኳን እምቢ ተጣልቼሃለው/ሻለሁ ብለው ጥለዋችሁ ይሄዳሉ አንዱን ብቻ አይመርጡም። ሌላኛውን ማጣት አይፈልጉምና።

እኛስ?

ከገንዘብና ከሰው፣
ከእምነትህ እና ከፖለቲካ፣
ከአገርህ እና ከጥቅምህ፣
ከወንድምና ከእህትህ፣
ከሥራህ እና ከሃላፊነትህ፣
ወዘተረፈ
ተብለን ስንጠየቅ ምላሻችን ብለን የምንሰጠው ይበልጣል ብለን ያሰብነውን አንዱ ነው እንጂ ምንም አይነት ማስረጃ አግኝተን አይደለም።ተልቀናል/አድገናል ብለን ስለምናስብ ስሌት ( calculation) ውስጥ እንገባለን።

አለማወቃችን ግን ከልጆች የዋህነት እና የልብ ንጽሕና ስለማይበልጥ ምርጫችን ስሕተት ይኖርበታል። በምሳሌ ስንመለከት ጥያቄው ከእናት እና ከአባት ለመምረጥ ምን መስፈርት ተቀምጦልን ነው አንደኛቸውን የመረጥነው? ከገንዘብ እና ከሰው እንዴት ልንመርጥ ቻልን? ሁለቱን አንድ የሚያደርጋቸው ምን መለኪያ ተገኝቶ ነው? እነዚህም እስኪ ይቅሩና ማን ነው አንዱን ብቻ ምረጡ ያለን? እንዲሁ ከሁለት ነገሮች መካከል አንዱን መምረጥ በምርጫ ሕግ ሥለምናውቅ እንጂ።

ሕጻናት ግን በቅንነት እና በፍቅር ሁለቱንም ይመርጣሉ።

አንዳንዶች ሰውን ከገንዘብ፣ ገንዘብን ከሰው ጋር ያነጻጽሩልንና አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ አድርገው በግድ አንዱን ምረጥ ይሉናል። ሁለቱም አስፈላጊነታቸውና መለኪያቸው ለየቅል ነውና።

ስለዚህ እንደ ሕጻናት ስንሆን ሁሉም የኛ ይሆናል። በ"እውቀት" ውስጥ ያጣነውን በየዋህነት እና በቅንነት ውስጥ ሁለቱንም እናገኘዋለን።

ሕይወትን በስሌት መኖር ሐጥያት ባይሆንም ቅሉ በየዋሕነት ሁለቱንም መምረጥ ግን ብልሕነት ነው ሁለቱንም ያስገኘናል እንጂ አያሳጣንም።

ገንዘብንም ሰውንም ይዞ መኖር ይቻላልና።

ከገንዘብ እና ከጤና ምረጡ ለሚሏችሁ ገንዘብንም ጤናንም እንደምትመርጡ ንገሯቸው።

አገርና እምነትን ለሚያስመርጧችሁ ሁለቱንም እንደምትመርጡ ንገሯቸው።

ከፖለቲካ እና ከመንፈሳዊነት ሲያስመርጧችሁ ሁለቱም ምርጫችሁ እንደሆኑ አረጋግጡላቸው።

የሰውን ልጅ ትክክል የሚያደርገው ከሁለት አንዱን መምረጡ ሳይሆን የመረጠውን እንዴት ይጠቅምበታል የሚለው ነውና። አንዳንዶች ገንዘብ ሃጢያት እንደሆነ ያወሩናል ድሕነት ጽድቅ ነው ወይ? ብዬ እጠይቃቸዋለሁ።

እንደዛ ቢሆን ኖሮ ድሆች ሁሉ ጻድቅ ሐብታም ሁሉ ሐጥአን በሆኑ ነበር። ነገር ግን እውነታው ሐብትን በአግባብ መጠቀም አለመቻል ነው ጽድቁም ሐጥያቱም።

ስለዚህ ሁላችንም ሁለት ምርጫ አለን። አንድም ሁለቱን አንድም ሁሉንም መምረጥ።

#######$$#######$$$#######

እኔን ለማግኘት ጽሁፎቼን ለመከታተል ከዚህ በታች የተጠቀሱት ሁሉ ወደ'ኔ ይመሩዎታል።

My Facebook page link (በፌስቡክ ገጽ እንገናኝ)

https://www.facebook.com/deresse2020/

Main facebook account (ዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ይቀላቀሉት)

https://www.facebook.com/DeresseReta

Follow me through telegeram (በቴሌግራም ሊከታተሉኝ ከፈቀዱ) ሁሉም ምልከታዬን የማጋራባቸው ማህበራዊ ድረ ገጾች ናቸው።

https://t.me/deressereta

ከአሥር አመት በላይ ከ50ሺ በላይ አንባቢዎች ያሉት መጦመሪያም አለ።

www.deressereta.blogspot.com 

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...