እሑድ 11 ኦክቶበር 2020

በኛ ይብቃ ...

 በኛ ይብቃ ...

ደረሰ ረታ
1/2/2013

አደጋዎች በሽ ናቸው።

የትራፊክ አደጋ፣ በህክምና ስህተት የሚደርስ አደጋ፣ በብሔር ግጭት የሚደርስ አደጋ፣ በሃይማኖት ጥላቻ የሚደርስ አደጋ፣ በፖለቲካዊ አስተሳሰብ የሚደርስ አደጋ፣ በተፈጥሮ ክስተት የሚደርስ አደጋ፣ በሰው ሰራሽ በእቅድ የሚደርስ አደጋ፣ ወዘተረፈ በእነዚህና በሌሎች አደጋዎች የብዙዎች ንብረት ወድሟል፣ አካል ጎድሏል፣ ለስደት ተዳርገዋል፣ ለሞት ተዳርገዋል።

የተረፉት፣ የተጎጂዎች ቤተሰብ፣ የቅርብ ሰዎች በየሚድያው ይቀርቡና "በኛ ይብቃ ... ከኛ ተማሩ" ሲሉ ይደመጣል።

ከመች ወዲህ ነው ጥቃት መማሪያ የሚሆነው?

ከመች ወዲህ ነው ጥቃት መማሪያ የሆነው?

በምን መልኩ ነው መገደል መማሪያ ሊሆን የሚችለው?

እነማንስ ተምረው ድርጊታቸውን አቆሙ?

ከዚህ ልምድ የሚቀስሙት ገዳዮች ወይስ ሟች ነው ትምህርት የሚወስደው?

እኔ በበኩሌ ከዚህ አልማርም፤ በገዳዮች ስሕተት መሞት በቃኝ። በአጥፊዎች ተገፍቼ መኖር በቃኝ። በአሳዳጆች መፈናቀል በቃኝ።

እመራሃለሁ የሚለኝ መንግሥት ከስጋት ነጻ ሊያደርገኝ ይገባል፣ በዚህ ላይ ለተሰማሩት ፍርዲ ሊሰጥልኝ ይገባል፣ ሁሉንም እኔ እየሆንኩ በኔ ይብቅ እያልኩ መኖር በቃኝ።

በብሔር ግጭት የምሰደድ የምሞት እኔ፣ በፖለቲካ ሽኩቻ ንብረቴ የሚዘረፍ እና የሚወድም እኔ፣ በሐይማኖት ግጭት የምገፋ የማምለክ ነጻነቴን የማጣ እኔ፣ ... በቃኝ።

በኛ ይብቃ እያልኩ አልኖርም፤ ፍትህ ይገባኛል።

በሕክምና ስሕተት ህይወት የሚቀጥፉ፣ በፖለቲካ ቁማር ጫወታ ሕዝብ የሚያሰቃዩ አገር የሚያተራምሱ፣ በተረኝነት መንፈስ በሕዝብ ገንዘብ የሚጫወቱ፣ በግዴለሽነት በትራንስፖርት በመኪና አደጋ አካል የሚያጎድሉ ንብረት የሚያወድሙ ሕይወት የሚቀጥፉ የሚቀጡበት ሕግ ይሻሻልልን። ደማችን ፈሶ፣ ንብረታችን ተዘርፎ፣ ተስፋችን ሰልሎ፣ ሕይወታችን አልፎ አይቅር።

"በኛ ይብቃ" ይብቃን። በእነርሱም ተመጣጣኝ ቅጣት ይጣል።

#በወሊድ_ምክንያት_በሕክምና_ስሕተት_መሞት_በቃን
#በመኪና_አደጋ_መሞት_በቃን፣
#በሐይማኖት_ተለይቶ_መሞት_በቃን፣
#በእርስ_በርስ_ግጭት_መሞት_በቃን፣
#በተረኝነት_መገፋፋት_በቃን።

@deressereta

ከወደዱት ያስተምራል ብለው ካሰቡ like እና share ያድርጉ።
My Facebook page link (በፌስቡክ ገጽ እንገናኝ)

https://www.facebook.com/deresse2020/

Main facebook account (ዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ይቀላቀሉት)

https://www.facebook.com/DeresseReta

Follow me through telegeram (በቴሌግራም ሊከታተሉኝ ከፈቀዱ) ሁሉም ምልከታዬን የማጋራባቸው ማህበራዊ ድረ ገጾች ናቸው።

https://t.me/deressereta

ከአሥር አመት በላይ ከ50ሺ በላይ አንባቢዎች ያሉት መጦመሪያም አለ።

www.deressereta.blogspot.com 

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...