ማክሰኞ 27 ኦክቶበር 2020

ከ"ሚሰበር ይሰንጠር"

 ከሚሰበር ይሰንጠር

ደረሰ ረታ
17/2/2013

አንዳንዶች ከትህትናም ይሁን ከስንፍና በተለይ መንፈሳዊ ነገሮችን ላለማድረግ እኔ ይቅርብኝ፣ እኔ ለዚህ ነገር ብቁ አይደለሁም፣ ከኔ የተሻሉ ሌሎች አሉ፤ በማለት ወደኋላ ሲያፈገፍጉ ይታያሉ።

ይሕ ተግባር ንሰሐ ለመግባት፣ ትዳራቸውን በመንፈሳዊ መንገድ ለመጀመር፣ በአገልግሎት ለመሳተፍ፣ ከዚህም አልፈው ስለአገራዊ ጉዳይ እነርሱን እንደማይመለከት ይሰማቸዋል። አገር የምትመራው በፖለቲከኞች ብቻ ይመስላቸዋል፤ ቢሆንም ቅሉ ፖለቲካን ይፈሩታል ይሸሹታልም።

ነገር ግን የእምነት ተቋምም ይሁን አገር ባላዋቂዎች ባህር ላይ እንዳለች ታንኳ ስትናጥ እነርሱም በዚህ ጉዳይ ጤናቸውን ያጣሉ። ደስታቸውም ሆነ ሰላማቸው ከሁለቱ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ነውና።

ስለዚህ:-

ጸሎት ከሚቀር በዝንጉእ ልቡናም ቢሆን ይጸለይ፣
ጾም ከሚቀር ንሰሐ ባንገባም ምጽዋት ባንሰጥም እንጹም፣ በጥቂቱ ስንታመን በብዙ የሚሾም ፈጣሪ ያበረታናልና።

ሥራችን ውጤት አልባ፣ ፍሬ ቢስ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን እኛ ብንደክምም፣ ጥቅም ባናገኝበትም እንሥራ፣ ጋን በጠጠር እንዲደገፍ አገርም የኔ ድጋፍ ያስፈልጋታልና።

ውሃ ቢወቅጡት እንቦጭ የሆነ ማንነት ቢኖረንም ቅሉ ተመልሶ ጭቃ ብንሆንም ንስሐ እንግባ፤ እንጹም፣ እንጸልይ፣ ሥጋውን ደሙን እንቀበል፣ እናገልግል፣ ከስንፍና በራቀ ትህትና ውስጥ ሆነን ማገልገል ይጠበቅብናል መንፈሳዊነትም ይገባናል እንበል።

ሰይጣን እና ውሻ አንድ ናቸው፤ ውሻ የእውሩን በትር እንቅስቃሴ አይቶ እንዲሸሽ አይነስውርነቱ ውሻን በበትሩ መከላከል እንዳያግደው ሁሉ እንዲሁ ሰይጣንም በኛ ጸሎት እንደዛው ነው የምንጠራው ሥመ አምላክ ሃይል አለውና። ምንም የልብ ንጽሕና ባይኖረንም የአፋችንን እንቅስቃሴ ተመልክቶ ይሸሻልና እንጸልይ። ጸሎት ካለመጸለይ ይሻላልና። አገርን ማገልገል ካለማገልገልና በሙስና አገርን ከማቆርቆዝ ይሻላልና። ሁሉም ባለበት መስክ ታማኝ ሆኖ ካገለገለ አገር ትበለጽጋለችና።

እያንዳንዱ ሰው በየቤቱ በሕይወቱ ውስጥ እምነቱ የሚያስገድደውን ተግባር በትንሹም ቢሆን ቢያከናውን ካለማድረግ ይሻላል። ከ"ሚሰበር ይሰንጠር" ይላሉና አበው፤ የአገር ጉዳይ የአብያተ እምነት ጉዳይ ተሰብሮ ከሚጣል ተሰንጥሮም ቢሆን ቢቀጥል ይሻላልና። ነገ ስንጥሩ መደፈኑ አይቀርምና።

ስለዚህ ከአገር እና ከየእምነት ሥፍራችን ጋር ያለን ቁርኝት ተሰብሮ ከሚቀር ተሰንጥሮም ቢሆን ይቀጥል ነገ ሌላ ቀን ነውና።

በሌሎች አስተማሪ ጽሑፎች እንድንገናኝ ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ።

My Facebook page link (በፌስቡክ ገጽ እንገናኝ)

https://www.facebook.com/deresse2020/

Main facebook account (ዋናው የፌስ ቡክ ገጼ ይቀላቀሉት)

https://www.facebook.com/DeresseReta

Follow me through telegeram (በቴሌግራም ሊከታተሉኝ ከፈቀዱ) ሁሉም ምልከታዬን የማጋራባቸው ማህበራዊ ድረ ገጾች ናቸው።

https://t.me/deressereta

ከአሥር አመት በላይ ከ50ሺ በላይ አንባቢዎች ያሉት መጦመሪያም አለ።

www.deressereta.blogspot.com 

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...