UNESCO ባወጣዉ
ዘገባ አማካይነት በሳምንት አንድ ጋዜጠኛ እንደሚሞት ይፋ አድርጓል፡፡ የዚህ አንድ ጋዜጠኛ ህይወት የሚቀጠፈዉ ወይም ለመስዋዕትነት
የሚቀርበዉ ለአድባር ወይም ለአምልኮ ጣዖት አይደለም፤
ለሙያዉ ክብር ሲል እንጂ፡፡ ይህ ጋዜጠኛ ሥራን ለመስራት ላይ ታች ሲል ህይወቱ
በአንባገነኖች መዳፍ ዉስጥ ትወድቃለች፡፡
በአለም አቀፉ ደረጃ የፕሬስ ነፃነት በሚከበርበት ዕለት በወጣዉ መረጃ መሰረት
በፈረንጆች ዘመን አቆጣጠር ከ2006 እስከ 2012 ድረስ 502 ጋዜጠኞች የተገደሉ ሲሆን አሟሟታቸዉ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል፡፡መረጃዉም
ከዚህ እንደሚከተለዉ ተቀምጧል፡-
ዘመን
|
የሟች ቁጥር
|
2006
|
70
|
2007
|
59
|
2008
|
48
|
2009
|
77
|
2010
|
65
|
2011
|
62
|
2012
|
121
|
ይህ ድርጊት
እየተፈፀመ ያለዉ በታዳጊ አገራት እና ዲሞክራሲ ባልተስፋፋባቸዉ አገሮች ብቻ አይደለም፡ ባደጉት አገሮችና ዲሞክራሲ ጥርሱን በነቀለባቸዉም
አገራት ጭምር እንጂ፤ ይህ ደግሞ ለእንደ እኛ አገር እጅግ ትልቅ
ስጋት ነዉ፡፡
ይህ መረጃ የሚያሳየን ይህቺ ዓለም ለጋዜጠኞችና ለኢየሱስ ክርስቶስ (አንዳች
ሀሰት ያልተገኘበት) እንዳልተመቸች ነዉ