ማክሰኞ 30 ኤፕሪል 2013

አንድ ሠው እንሁን

አንድ ሠው እንሁን

ለቤተክርስቲያን ዋልታ ጥላ ከለለዋ፣
ለክፉ ቀን ደራሽ ጋሻ መከታዋ፡፡
እንድንሆን አንድ ቀን ብዙም ሳንዘገይ፣
ቆመን እንገኝ የወደቀውን ሳናይ፡፡
በልጆቿ መጥፋት በጣሙን ተማራ፣
ቤተክርስቲያን "ሰው ሆይ" ብላ ስትጣራ፡፡
ልጆቿ ሆይ ሥሙ አድምጧት ድምⶑን፣
አለን እማ በሉ አሰሙ ድምፃችሁን፡፡
አጋር ሲያስፈልጋት ከጎኗ የሚቆም፤
ክርስቲያን ነኝ የሚል ጠበሏን የሚጠጣ፣
መስቀሏን የሚሳለም፣
ከለላ አጥር ሲያስፈልጋት ድንበር፤
በርቀት ሳንሆን በቅርበት ከጎኗ እንኑር፡፡
ብዙ ሰው ሲያስፈልጋት ተገን፤
እኛም ለእርዳታው አንድ ሰው እንሁን፡፡
ለቤተክርስቲያን ዋልታ ጥላ ከለለዋ፣
ለክፉ ቀን ደራሽ ጋሻ መከታዋ፡፡
እንድንሆን አንድ ቀን ብዙም ሳንዘገይ፣
ቆመን እንገኝ የወደቀውን ሳናይ፡፡
በልጆቿ መጥፋት በጣሙን ተማራ፣
ቤተክርስቲያን "ሰው ሆይ" ብላ ስትጣራ፡፡
ልጆቿ ሆይ ሥሙ አድምጧት ድምⶑን፣
አለን እማ በሉ አሰሙ ድምፃችሁን፡፡
አጋር ሲያስፈልጋት ከጎኗ የሚቆም፤
ክርስቲያን ነኝ የሚል ጠበሏን የሚጠጣ፣
መስቀሏን የሚሳለም፣
ከለላ አጥር ሲያስፈልጋት ድንበር፤
በርቀት ሳንሆን በቅርበት ከጎኗ እንኑር፡፡
ብዙ ሰው ሲያስፈልጋት ተገን፤
እኛም ለእርዳታው አንድ ሰው እንሁን፡፡

ሰኞ 29 ኤፕሪል 2013

ቃለ መጠይቅ


የሰዉ ልጅ መሰረታዊ የተባሉትን አስፈላጊ ነገሮችም ሆነ የቅንጦት ነገሮች ለማሟላት ገንዘብ አስፈላጊ እንደመሆኑ መጠን ሥራን መስራት ግድ ይላል፤
ሥራ ስንል የቀን ስራ ፣ የመንግስት ስራ፣ የግል ድርጅት ስራ፣ የዓለም አቀፍ መስሪያ ቤቶች ስራ፣ ተደራጅቶ የሚሰራ ስራ፣በግል የሚሰራ ስራ፣ … ወዘተ ተጠቃሾች ናቸዉ፡፡
እነዚህን ስራ ለመስራት መቀጠር ቀዳሚ ተግባር እንደሆነ የታመነ ነዉ፤ ለመቀጠር ደግሞ ሊያሟሉ የሚገባዎት መሰረታዊ ነገሮች እንዳለ ሆነዉ ዘመድ ወይም ቃለመጠይቅ ከነርሱ ዉስጥ የሚጠቀስ ነዉ፡፡ ለዛሬዉ ቃለመጠይቁን እንመለከታለን፡፡
(ለቃለመጠይቅ ፈተና እድሉን ያገኙ ተወዳዳሪዎች ስም ዝርዝራቸዉ ተለጥፈዋል ሁሉም ለጀማሪ ሰራተኝነት ሳይሆን ለዉስጥ ዕድገት የሚወዳደሩ ይመስላሉ አለባበሳቸዉን ለተመለከተ ሴተም አጭር ቀሚስ ረጅም መጫሚያ ወንዱም ሙሉ ልብሱን ከነከረቫቱ ለብሷል )
(ለቃለመጠይቁ በፈታኝነት የተመደቡት ቦታ ቦታቸዉን ይዘዉ ፈተናዉን ጀምረዋል ተፈታኞችም አንድ በአንድ እየገቡ ደቂቃዎችን እያሳለፉ ሲወጡ ሲገረፉ የቆዩ ፣አቧራቸዉ ቡን ብሎ፣ላብ በላብ ሆነዉ፣ጠቋቁረዉ ይወጣሉ፤ አንዱ ተረኛ ገባ … )
ተጠያቂ፡- ገብቶ ከፈታኞች ፊት ለፊት ቆመ
ጠያቂ 1 ፡- እንካን ደህና መጣህ
ተጠያቂ፡- እንካን ደህና ቆያችሁኝ
ጠያቂ 2 ፡- ቁጭ በል
ተጠያቂ፡-አመሰግናለሁ( በማለት ወነበሩ ላይ ተቀመጠ)
ጠያቂ 1፡-ለምን መጣህ
ተጠያቂ፡- ድርጅታችሁ ባወጣዉ ማስታወቅያ መሰረት (የማስታወቅያ ቁጥሩን፣ የወጣበት ክፍል፣የሰዉ ብዛት፣ … ወዘተ ጠቅሶ) የፅሁፍ ፈተና በማለፌ ዛሬ ደግሞ ለቃለ መጠይቅ ተጋብዤ ነዉ የመጣሁት፤
ጠያቂ 1፡-(እንዳኮረፈ ሰዉ በመሆን) እስኪ ካሪኩለም ቪቴህን( CV ) አብራራልን
ተጠያቂ፡-እድሉን ስለሰጣችሁኝ በጣም አመሰግናለሁ፤ ሥሜ፡-(ሙሉ ስሙን ተናገረ)፣የትዉልድ ዘመን፡-(የተወለደበትን ዘመን ተናገረ)፣ትምህርት መቼ እንደጀመረ፣ የት እንደተማረ፣ የትምህርት ደረጃዉን በደንብ አስረዳ … …
ጠያቂ 2 ፡- በቃህ (ድምፃቸዉ የቁጣ ነበር )
ጠያቂ 3 ፡-የምትቀጠርበትን የስራ ክፍል ሥራ ተናገር
ተጠያቂ ፡- ገና አዲስ ምሩቅ እንደመሆኔ መጠን ምንም ዓይነት የስራ ልምድ ሥለሌለኝ በአሁኑ ሰዓት ሥለማላዉቀዉ ክፍል መናገር ይከብደኛል፤
ጠያቂ 1፡-ታድያ ምን ልትሰራልን ነዉ?(የቁጣ ፊታቸዉ ምንም አልተቀየረም )
ተጠያቂ ፡- ማስታወቂያ የወጣዉ በዜሮ የስራ ልምድ ስለሆነ (ብሎ እየተናገረ እያለ )
ጠያቂ 4፡-ስለርሱ አትነግረንም አሁን ይልቅስ ስለፕላኒንግ (Planning) የምታዉቀዉን ንገረን፤
ተጠያቂ ፡-የማኔጅመንት የማዕረግ ተመራቂ እንደመሆኑ መጠን በግልፅ እንግሊዝኛ አብጠርጥሮ ተናገረ፤
ጠያቂ 1፡- የት አገር ነዉ plan (ዕቅድ) እንዲህ አይነት ትርጉም ወይም ትንታኔ የኖረዉ?
ተጠያቂ ፡- (እየሆነ ያለዉ ነገር ከቁጥጥር ዉጭ ሆነበትና እርሱም ቆጣ በማለት) Planning & Plan has a big difference በማለት የሁለቱን ልዩነት ወደ ማስረዳት ገባ (አሁንም ጠያቂ 2 አቋረጡት)
ጠያቂ 3፡-እስኪ ስለ ሪፖርት ንገረን?
ተጠያቂ ፡- ያለማቋረጥ ለአምስት ደቂቃ ይክል ከተናገረ በኋላ በአጭሩ ይህን ይመስላል (ሁሉም ጠያቂዎች በጣም ተደመሙ ይህንን ሰዉ እንዴት ይጣሉት የሚፈለገዉ የሰዉ ብዛት አንድ ነዉ ማስታወቂያዉ ሲወጣ ሊቀጠር የታሰበ ሠዉ ግን ተዘጋጅቶበታል በጣም ተጨነቁ )
ጠያቂ 4፡-ጥያቄያችንን አጠናቀናል በመጨረሻ ከአንድ ደቂቃ ባለሰ የምትለን ነገር ካለ ተናገር፤
ተጠያቂ ፡- የምለዉ ነገር የለኝም ሁለት ጥያቄ ግን አለኝ፡ 1ኛ. የኛ ባልሆነ ቋንቋ ይህንን ያህል ሰዓት ፈጅተን በራሳችን የመግባብያ ቋንቋ ከአንድ ደቂቃ ባነሰ ምን ማለት ይቻላል?
2ኛ. የአገራችን የሥራ ቋንቋ አማርኛ (የአፍ መፍቻችን ነዉ) ወይንስ እንግሊዝኛ ነዉ? ጨርሻለሁ!

ሐሙስ 25 ኤፕሪል 2013

ተስፋዬ ማን ነው?


ልዑል እግዚአብሔር ሆይ ተስፋዬ ማን /ምንድን/ ነው? ከወደየትስ ነው?
       እንደምን አደርክ እንደምን ዋልክ እንዳልልህ ባህሪህን መመራመር አይቻለኝም ስለጤንነቴም እንዳልነግርህ ሁሉን የምታውቅ ቸር አምላክ ነህ፤ እንዳለምንህ ሁሉን ነገር ሳይጠይቁህ በልግስና አውቀህ የምትሰጥ ነህ፡፡ ስላደረክልኝ ዋጋ እንዳልከፍልህ እንደምድራዊ ነገስታትና መኳንንት እጅ መንሻን የምትሻ አይደለህምና፣ ብቻ የባህርይ ገንዘብህ የሆነውን ምስጋና ላቅርብልህ፤ ዘወትር ከኔ ሳትርቅና ሳትለየኝ የረድኤት እጅህ ሳይታጠፍብኝ የምህረት ዓይንህ ከእኔ ሳይነቀል እንዲሁ የምትናፍቀኝ ከውኃ ጥማት ከእንጀራ ረሃብ ሁሉ የምትብስብኝ መለኪያ መጠን የሌለው ፍቅርህ የሚስበኝ አምላኬ ሆይ አስቀድመህ ሰማይና ምድርን በምድርም ላይ የሚመላለሱትን በእግር የሚሽከረከሩ፣ በልባቸው የሚሳቡ፣ በክንፋቸው የሚበሩ፣ በሰማይና በምድር ለኔ ፈጠርክ፤ እፅዋትንም ሳይቀር ከአዝርዕት ጋር እመገባቸው እገለገልባቸው ዘንድ ለእኔ አዘጋጀህ /አደረግህ/፡፡ ከዚያም ባሻገር ከሁሉ በላይ ራስህን በማዕከለ ምድር በቀራንዮ አደባባይ አይሁድ ምራቃቸውን እየተፉብህ እንደብርሃን የሚያበራ ፊትክን በጥፊ ተፀፋህ ቸርና ለጋስ እጆችህን የወንጀለኞች መቅጫ በነበረው (አሁን ግን ትምክህታችን በሆነው) መስቀል ቀኝና ግራ እጆችህን ቸነከሩህ ደረትክን በጦር ተወጋህ ደምህን አፍስሰህ ሥጋህን ቆርሰህ ለኔ ተሰዋህ፤
       ለእውራን ብርሃን ለአንካሶች መሄጃቸው ጤና ላጡ ጤናቸው ሰላም ላጡ ሰላማቸው የሆንክ ደግ አምላክ ሆይ ለእንደኔ አይነቱ ደካማ ፍጡር ብርታት የሆንክ አምላኬ ሆይ ባህሪህን ካላስቆጣሁና ካላስከፋሁህ አንድ ነገር እጠይቅሃለሁ፤ እባክህ አምላኬ ሆይ ተስፋዬ ምንድን ነው? ማንስ ነው? ከወደየትስ ነው? ብዬ ጥያቄ ሳቀርብልህ ዘወትር የማይለኝን አፅናኝ መልስህን ከምድር በማንጋጠጥ የምጠይቅህ የዘወትር ጠያቂህ /ለማኝህ/ ምዕመን ነኝ፡፡
ተፃፈ ለልዑል አምላክ

በቅርብ ለማውቅህ ወንድሜ‹‹ … የቀድሞ ፍቅርህን ትተሃል›› ክፍል - 2


ጊዜው ከባለፈው ምንም ለውጥ የለው ሁለመናው ተመሳሳይነትና አንድነት አለው ግን እኔና አንተ ተለውጠናል ነቀፌታ በዝቶብናል በሥጋ ሥራ ወጥመድ ተጠምደን በውዳሴ ከንቱ ተጠልፈን በትዕቢት ወድቀናል የትላንት ማንነታችንን ዘንግተን ዛሬን ጠፍተናል ለሁሉ ነገር የነበረንን የቀድሞ ፍቅራችንን ትተናል፤
ወንድማለም በደንብ በቅርብ አውቅሃለሁ ታውቀኛለህ የቀድሞ ፍቅርህን ትተሃል ባለፈው በክፍል አንድ እንደፃፍኩልህ

የአጋጣሚ ነገር ….


ዛሬ ሰኞ መጋቢት 9/2005 ዓ.ም. ነዉ፤ ሰኔና ሰኞን አለመሆን እንዳለ ሆኖ ለሰራተኛና ለተማሪ ደሞ የባሰዉን ነዉ፡፡
የትራንስፖርት ችግር ደግሞ ሰኞ አያዉቅ ማክሰኞ የለ ሁሌ ችግር ነዉ ለነገሩ ለእናንተ መንገር ለቀባሪዉ አረዱት ይሆንብኛል፡፡
አሁን ስለትረንስፖርት ችግር ላወራ አይደለም፤እንዲያዉም እናቴ በአፍ ይሄዳል ትል ነበርና  … … መተዉ ሳይሻል አይቀርም፡፡
……….. ነገሩ እንዲህ ነዉ፡- በጠዋት ተነስቼ ወደ ሥራ ገበታዬ እያመራሁ ነበር ፤ መኪናዉ ጉዞዉን ጀምሯል እንሄዳለን፣ እንሄዳለን … መንገዱ አያልቅም ወይ አያስኬድም፡፡
አንዳንድ  ሰዎች የትራንስፖርት መዘጋጋቱን ምክንያት(ተገን) በማድረግ ትዉዉቅ ይጀምራሉ (በአራዳ ቋንቋ ይጀናጀናሉ!) ፡-
በተለይ የከተማ አዉቶቡስ ላይ፤

ማክሰኞ 23 ኤፕሪል 2013

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: አማርኛ ከሠላሳ ዓመት በኋላ

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: አማርኛ ከሠላሳ ዓመት በኋላ:   click here for pdf የዛሬ ሠላሳ ዓመት በ2035 ዓም በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች መካከል የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ውድድር ይደረጋል፡፡ በውድድሩም ከዚህ በታች የማቀርብላችሁ ወግ ‹እኔና ትምህር...

ቅዳሜ 20 ኤፕሪል 2013

‘’ለመጪው ትውልድ ልማትን እንጂ ልመናን አናወርስም’’

‘’ለመጪው ትውልድ ልማትን እንጂ ልመናን
አናወርስም’’

ጐበዝ ለካ ታክሲ መያዝም ይከብዳል!(ተራ አስከባሪዎች ባይኖሩና በሰልፍ ባያደርጉት እንጃ ወደየቤታችን መግባታችንን(አደራችሁን ዘይት፣ዳቦ፣ስዃር፣ መብራት፣ ዉሃ እና ኔትዎርክ በሰልፍ ይሁን እንዳትሉ ) ) እውነቴን ነው የምላችሁ እስከዛሬ በነበረኝ “ጥልቅ” ግንዛቤ የገንዘብ እንጂ “የዕውቀት” ችግር ያለ አይመስለኝም ነበር፤ (ብዙ ዩኒቨርሲቲ እና ኮሌጅ ስለተከፈተ አለማወቅ አገር ለቆ ጠፋ ብዬ ነበርና የማምነው) በመሐላ ማረጋገጥ ካለብኝ እምላለሁ፤ ደሞ ለመሐላ መርካቶ በጠቅላላ መሐላ በመሐላ አይደል እንዴ ምን ችግር አለው ሳልምል እመኑኝ፤ በታክሲ ከመሔድ በእግር መሔድ በስንት እጥፍ ይበልጣል መሰላችሁ ሲመሽማ ‘’ወክ’’ በማድረግ ዘግዘቅ ማለት ነው ወደ ሰፈር፡፡

ያኔ አዲስ ዓመት መስከረም ሳይጠባ የነበረብኝን አባዜ ጦሴን ጥንቡሳሴን ብዬ በጳጉሜ ፀበል እና ህክምና ከላዬ ልይ ጥዬ አዲሱን አመት በአዲስ ጤና ለመቀበል ወደ ሆስፒታል አመራሁ የጳጉሜ 3 ፀበል ጥሩ( ለዚያዉም የጳጉሜ 3 የሩፋኤል ዕለት ከሁሉም ይበልጣል እጣ መጣል አያስፈልገውም) ሰፈር እስከ ማወክ ቤቶች እስከ መገለባበጥ በደረሰ ዝናብ ተፀበልኩ ጐበዝ!! አትሉኝም? (ለነገሩ ወረኛ ብትሉኝ ይሻላል ወሬ ከጀመርኩ አንዱን ሳልጨርስ ወደ ሌላ እሱን ትቼ ደግሞ ወደ ሌላ እሄዳለሁና) ሐኪሜ MRI ታየው ብሎኝ ለወገቤ ህመም ‘’ቤቴል ሆስፒታል’’ ላከኝ (አላውቅም ማለት ነውር አይደል?! ቦታው የት ነው? እንኳን ሳልል ተፈትልኬ ወጣሁ) ለነገሩ ምን ላድርግ ብላችሁ ነው ሄጄ እንድታከም ሲልከኝ ማስተባበያ ቃላት ጣል አደረገልኝ ይቅርታ ማከም አቅቶኝ አይደለም እዚያ የምልክህ የተሟላ ነገር እንኳን የለንም ለዚያ ነው ታየኛለህ አይደል ‘’ጓንት’’ እንኳን ሳይኖረኝ በእጄ ሥጠቀም ለዚህ ነው ይቅርታ አለኝ፡፡

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...