ዓርብ 29 ማርች 2013

* ሰሞኑን ዲ/ን ዳንኤልና ፕሮፌሰር መስፍን መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ በሚላዉ የፕሮፌሰር መጽሓፍ ላይ ሲነጋገሩ ነበር፤ ብዙዎችም አስተያየት ሰተዋል፡፡ እኔም እንዲህ ብያለሁ፡እነሆ፡-
ለኔ ሁለቱም የአገር ቅርሶቼ ናቸዉ፤ ይህን ያልኩበት የራሴ የሆነ ምናልባት ሌሎችም ሊጋሩት አልያም ላይጋሩት የሚችሉት ጉዳይ ይሆናል፡፡ ይኸዉም ሁለቱም ሰዎች በአገራችን ጉዳይ ላይ በማህበራዊ ነክ ጉዳዮች ላይ ብዙ ፅፈዋል ፣ አስተያየት ሰተዋል ተችተዋል. ጥናታዊ ፅሁፎችን አቅርበዋል፣ ወዘተ… ሆኖም ግን

* የየራሳቸዉ ደካማ ነገር የላቸዉም ማለቴ አይደለም፡ ይኖራቸዋል! ነገር ግን እነደ ጸሐፊነታቸዉ (አይከን) እንደ መሆናቸዉ መጠን በጣም ጥንቃቄ ሊያደረጉ ይገባ ነበር አሁን ሊያደርጉ ይገባል፡፡ ሊከባበሩና ሊደማመጡ ነገሮችን በጥሞና ሊከታተሉ ይገባል፣ ከመናገርና ከመጻፍ ለቆጠቡ ይገባል (ፕሮፌሰርን ማለቴ ነዉ) ዲ/ን ዳንኤል የመሰለዉን መናገር ይችላል ፕሮፌሰር ግን የጻፈዉን ነገር ተደፈርኩ በሚል ስሜት ሳይሆን በእርጋታና በጥሞና ቢያዩት፤ መልሱን የተጠቀሙበትን ቃላትም ቢፈትሹት ይሻል ነበር ይሁን ያ አልፋል፣ ያላለፈ ነገር ግን ይቅርታ ብሎ በጠረጴዛ ዙርያ ታሪክን መፈተሽ ይቻላል፡፡

* ህብረተሰቡን መወረፍም፣ ሌላ ስም መስጠትም አግባብ አይደለም እንዲያዉም እንበል ከተባለ የታሪክ መክሸፍ ሳይሆን የግለሰብን ማንነት መክሸፍና መዉረድ (መዝቀጥ) አይተንበጣል፤ ተሳዳቢነትና ንቀት የምንም ምልክት አይደለምና፡፡ ለዚህ ትዉልድ ምንም እንኳን ያደረግንለት ጥቂት ነገር (የምናቀዉን ነገር የሰጠነዉ ) ቢኖርም ከዚህ ህዝብ የተሰወረና እኛ ጋር ብቻ ያለ ነገር የለም! ያገኘነዉ ከህዝብ ነዉና ህብረተሰቡም ከኛየተሻለ ነገር አለ፡ አልፃፈዉም እንጂ፤ እዉቀቱን ገበያ ላይ አላዋለዉም እንጂ፡፡ ስለዚህ አንዱን ጥሎ ሎላዉ አንጠልጥሎ ጉዞ አይቻልምና ያለተገነዘቡአቸዉን ነገሮች ወደ ኋላቸዉ ተመልሰዉ ይመልከቱ!!!!!! መልዕክቶ ነዉ፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...