ዓርብ 14 ዲሴምበር 2012

ኑሮ በአሜሪካ


ኑሮ በአሜሪካ
        «ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባ» ይባላል ድሮ ድሮ በተረት አባቶች፡ ነገሩ ከተረትነት ወደ እውነትነት ተቀየረና አንድ ለእኛ አገር ለእውነትም የሚከብድ ለተራትነትም የማይመጥን ወሬ ቅዥት ያርገውና ከወደ አሜሪካ ነው የመጣው ተብሎ ሲወራ ጆሮዬን ጣል አድርጌ ማዳመጥ፡- «ልጅየው ከሞትና ከአሜሪካ አይቀርም ከተባለባት ምድረ አሜሪካ ሰሞኑን ሥሰማ አፍሪካዊ ስለገዛት ነው መሰለኝ ገነትም ማለት ጀምረዋል መቸስ አሉ ነው እኔ አልሰማሁም፡ ገነትም ስትሆን አላየሁም፤ ብቻ ይህ ሰው ከሄደ ዓመታት ተቆጥረዋል። ያው! እንደሚባለው የአሜሪካ  ሰው ከሄደ ዓመታት ተቆጥረዋል። ያው! እንደሚባለው የአሜሪካ ሰው ምንም አይመቸውም ጊዜም የለውም ፀበል ፀዲቅ፣ክርስትና፣ ልደት፣ለቅሶ፣40 እና 80 የሚባል ነገር እንደተለመደው መድረስ እንኳን ሊደረግ አይታሰብም። አገር ቤትም መጥቶ ቤተሰብ ለመጠየቅ የሚያደርሰው ለዚያውም እግዚአብሔር ፈቅዶ ሳይሆን የአሜሪካ መንግስትና ኑሮ ከፈቀዱ እግዜርም ለዓይነ ሥጋ ተገናኙ ሲላቸው ወላጅን ሳይሆን የልጅ ልጅን ያገናኛቸዋል። ይህ የተባለው ሰው ግን ብልጥ ነበርና ዘዴ ዘይዶ አባቱን እዚያው ከወደ አሜሪካ ይወስዳቸውና በዓይነ ሥጋ ለመገናኘት ይበቃሉ። ሰውና እንጨት ተሰባሪ ናቸውና ሰውየው ቀናቸው ደርሶ ወይም በሽታቸው ፀንቶ አሊያም አሜሪካ የምትባል አገር አልመች ብላቸው ብቻ የሆነውን እንጀላቸው ሞቱ፤ ... ልጅ እርሙን አወጣ፣ ጉረቤትም ደረሱ ጓደኞችም ግማሹ e-mail ልከውለት፣ አንዳንዶቹም ሥልክ ደወለው ለቅሶ ደረሱ አራት ነጥብ በቃ ለቅሶ አለቀ ቀብር ቀረ፤ ልጅ ሆዬ አባቱን እንዴት መቅበር እንዳለበት ለጥቂት ዳቂቆች አሰብ ካደረገ በኃላ ለቀብር ተዘጋጀ እንዳአሜሪካ በዚህ መሀል ድሮ ከአገር ቤት ሳይወጣ የሚያውቃቸው ጓደኞቹ የአባቱን መሞት ሲሰሙ ለቅሶ ሊደርሱ እርማቸውን ሊያወጡ በዚያውም የቀብር ቀንና ሰዓት ጠይቀው የቀብር ቦታውን ለይተው ሊመለሱ በድንገት ይደርሳሉ። ለቅሶ ተጀመረ «አልሰማሁም ነበረ... እኔን ያስቀድመኝ ...አባዬ አባዬ...»ልጅየው ትንሽ ታገሣቸው ከሩቅ ቦታ ስለመጡ በማለት ሠዓቱን እየተመለከተ እነርሱም በአገርኛ አልቅሰው ከጨረሱ በኃላ ሴቷ ወደ ጓዳ ገባች ሀዘንተኞች ከቀብር መልስ የሚቀመሱትን ንፍሮ ለመቀቀል፣ አንደኛው ምን ሆነው ነዉ የሞቱት እያለ ይጠይቃል ሌላው እስክርቢቶ አውጥቶ የህይወት ታሪካቸውን ይፅፋል ከቀብር በኃላ ለታዳሚዎች ለማንበብ ...እንዲህ ሁሉ በሥራ በተጠመደበት እርሱ መቸኮሉን ይነግራቸዋል ወደ ሥራ ለመሄድ እነርሱም አባቱን ሊቀብሩ እንደመጡ ምናምን ሲያጫውቱት «...እንዴ! አባቴን ለመቅበር ነው የመጣችሁት? ጊዜ አላችሁ? እንግዲያውስ በቃ እናንተ አባቴን ሄዳችሁ ቅበሩልኝ እኔ ወደ ሥራ ልሂድ ይላቸዋል፤ ...» መቸስ ትስቁ ይሆናል አታፍሩም አይሳቅም ነገሩም አያስቅም እንግዲህ እዚያ አገር አሜሪካ እንዲህ ነው አሉ እንዲያውም ሲባል እንደሰማሁት መቸስ አሉ ነው፤ ያንን የአሜሪካ ፕሬዘዳንት ኦባማን እንዲመረጥ ካስደረጉት ውሥጥ አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያኖች ናቸው ይባላል። ምክንያቱ ደግሞ አፍሪካዊ ሥለሆነ አፍሪካ ደግሞ ለአሜሪካ ሳይሆን ለኢትዮጵያ ነውና የምትቀርበው ባህላችንን ይጠብቅልናል የሐዘን ፈቃድ ይሰጠናል እዚህጋ እንዲያውም እንደሚባለው ያኔ ድሬደዋን ጎርፍ ያጥለቀለቃት ጊዜ መጥቶ ሐዘናችንን በዓይኑ ስላየ ይራራልናል በማለት ነበር። የምርጫዉ ቅስቀሳ ላይ እርሱ እንዲመረጥ ላይታች ሲሉ የነበሩት አሁን እንዲያውም ስሰማ ይህንንና ሌሎች ተስፋ ያደረግናቸውን የአፍሪካን ይልቁንም የኢትዮጵያን ጉዳይ ችላ ብሏል ብለው ቂም ይዘውበታል፣ አንዳንዶችም ዋ! እያሉ ይዝቱበታል አሉ። ለዚህ ያበቃቸው ምን እንደሆነ ባላውቅም ይህን ድፍረታቸውን ግን አልወደድኩላቸውም የሰማ ቀን ግን በአመጽ መንግሥት ለመገልበጥ ጥረት አድርጋችል በማለት እንዳያስገባቸው ኦባማ ማለቴ ነው። በቅስቀሳ ወቅትም አጉል እዩኝ እዩኝ በማለት የኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ እያሉ ማሽቃበጡን ትተው የሄዱበትን ጉዳይ ሥራቸውን ብቻ ቢሰሩ ይሻላቸዋል ባይ ነኝ ፌዴራል ፖሊስ ጠራርጎ እንዳይወስዳቸው (ፌሬራል ፖሊስ ለመሆኑ አለ አንዴ አሚሪካ?) እንጃ እንግዲህ!
          መቸስ ዘመድ ባይኖረኝ የማውቀው ሰው አይጠፋ ብዬ ሰጋሁና እንዴት ነው ነገሩ እነዚህ ኢትዮጵያውያን እንደዚህ ያስጠገባቸው ዓለም በአጠቃላይ ያልደፈራትን አሜሪካንን  መሪዋን ኦባማን የተዳፈሩት አርፈው አይቀመጡምወይ ብዬ የጭንቀቴን ባማክረው የኔን ጭንቀት ከቁብም ሳይቆጥረው ምን  ይሆናሉ ብሎኝ እርፍ። እንግዲህ ዘመድ ባይኖረው ካልሆነም የሚያውቀው ነገር ይኖረዋል ብዬ እንዴት? አልኩት። እንዴት ምንም አይሆኑም ኢራቅን የመሰለች አገር ደብድባ የሳዳም ሁሴንን ክብር ያቀለለች አገር እዚሁ ፊታችን ዓለምን ሲያስጨንቁ የነበሩ የሱማልያ አሸባሪዎች ዶግ አመድ ያደረገች አሜሪካ በመሪዋ ሲመጡ እነዚህን ጭብጥ የማይሞላ ኢትዮጵያውያን እንዴት ምንም እያደረጓቸውም ?? ብዬ ቱግ አልኩላችሁ ሰውየው የባስ እግሩን አንስቶ ቢስቅ ምን ትሉታላችሁ? በአንድም በኩል ትዕግሥቴ በዝቶ በሌላ በኩልም ፍርሃቴ ፀንቶ ነው እንጂ ዘልየ ጉሮሮውን ባንቀው ደስ ባለኝ። ሳቁን አፍኖ «እድሜ ለዲሞክራሲ» ብሎኝ እርፍ «ዲሞክራሲኮ ነው ምን አስፈራቸው እንዲያውም በዚህ ሰዓት ባለቀ ሰዓት እርሱ ነው ሊፈራቸው የሚገባው የምርጫ ካርድኮ በነርሱ እጅ ናት! በምርጫ ካርዳቸው ልኩን ያሳዩታል» በማለት ወደኔ አፈጠጠ፤ «አሁንስ ገባህ?! አለኝ ተረጋግቶ እየተቀመጠ።
          ገባኝ «ገባኝ አሁን ገና» ነው ያለው ዘፋኙ? አፍሪካ አገር ውስጥ ዲሞክራሲ ሥራውን የሚጀምረው ከስንት ዓመት በላ ነዉ የምርጫ ካርዳችንስ መቼ ይሆን ዋጋ የሚኖረው? አፍሪካዊስ መች ይሆን ደፋር የሚሆነው?...
ያለቸገረኝን?
በሉ ወደ ጀመርነው ጉዳይ፤
          በዲቪውም ይሁን አጥር ዘለን የምንሄድበት (በህገ ወጥነት) አሜሪካ ይሰሩበታል እንጂ ቁጭ ብለው አይቡሉባትም አሉ። አንድ ወዳጄ አጥር ሰበሮ ከደቡብ አፍሪካ አሜሪካ ከገባ በኃላ ኑሮ በአሜሪካ እንዴት ነው? ብዬ ብጠይቀው ምን ብሎ አወጋኝ መሰለቻችሁ ሰርቶ ለማግኘት ቤተሰብም ለመርዳት እምዬ ደቡብ አፍሪካ  ለጉራ (ልጄ፣ ወንድሜ፣ እህቴ አሜሪካ አለ ለማለት) ደግሞ አሜሪካ ይሻላል ብሎኝ አያርፈውም ይቺን ይወዳል ገነት አሜሪካ!
          ጊዜ ገንዘብ ነው ይላሉ 16 እና ከዚያ በላይ ሠዓት ሰርቶ አደሮች (አበዶች አላልኩም) በአሜሪካ፡፡ በቅርቡ ከአሜሪካ የመጣ አንድ የጉደኛዬ ወንድም እንደሰማሁት ከሆነ ለፈሱ ጊዜ የለዉም አሉ አሜሪካ ከሄደ ጀምሮ ይሰራል ይሰራል ይሰራል... ግን ኖሮ አያውቅም ሰዎች (አሜሪካ ያላችሁ) እናንተ አገር 24 ካራት ወርቅ ነው የምትበሉት ወይስ ውሏችሁ አሜሪካ አዳራችሁን ፕላኔት ላይ ነው? እንደዚህ የምትሰሩት ለሥራ ተከፍሏችሁ ለመኖር የሚያስከፍሏችሁ ከሆነ እባካችሁ ተመልሳችሁ ኑ! ምድራችን ሠፊ ናት አየር መንገዳችንም ቀጥታ በራራ ከጀመረ ሰንብቷልና (መረጃ ከሌላችሁ)። አልሰማችሁ እንደሆነ ልንገራችሁ ዓለም የሰማውን እናንተ በሥራ ተጠምዳችሁ ካልሰማችሁ የአቡኑን እና የመሪዎቻችንን ETV «ደማቅ» ያለውን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ለዚያም አባቱን በጓዸኞቹ ላስቀብረውም ንገሩት ቀብር ክብር እንዳለው እናንተ ለግማሽ ቀን በዛ አንድ ቀን ሰልስት ለሌላው ለቅሷችሁ እኛ 15 ቀን ሙሉ አስክሬን አስቀምጠን ሥራ ፈተን እንደምንቀብር፣ ለሟች ክብርና ፍቅር እንዳለን። አሁን ታዲያ እናንተ ተመልሳችሁ ኢትዮጵያዊ ትሆናለችሁ? እንጃ! ለነገሩ እንኳን የሚያዝን ልብና የምታነቡት እንባ ጊዜም አይኖራችሁ፤ ተውት! እኛ እንዳተፈጠረን እናዝናለን። እንዴት ሰው ለወለደው አባቱ ቀብር ጊዜ የለኝም ይላል! ነው ወይስ ዘመናዊነት እንዲህ ሆኖ ቀረ ወይስ ጉድ ሳትሰሙ መስከረም አይጥባ ብሎ ፈጣሪ ፈርዶብን ነው።???
ለነገሩ ለቅሶን አነሳን እንጂ ኑሮስ መች ተመቻቸዉ? አንዴ ሄደናል ብለዉ እፍረት ተሰምቸዉ እንጂ ለነገሩ ኑሮ ካሉት መቃብርም ይሞቃል ብለዋል ቾች፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...