ሐሙስ 20 ማርች 2014

Part one “… … አጋጣሚ”

“የህዳር ሚካኤል ካለፈ አንድ ወር ሆኖታል ታህሳስ ከገባ ደግሞ 11ኛ ቀኑ ነዉ እንደከዚህ በፊቱ በፌስ ቡክ እናወራለን፣ ምሥጢሬን ሁሉ ነዉ የምነግረዉ አንድም የምደብቀዉ ነገር አልነበረኝም፤ እህቴ እቤት ዉስጥ የጤና ባለሙያ ሆና ሳለ ትንሽም ራሴን ሲያመኝ በጣምም ምቅቅ ብዬ ጨጓራዬ ሲያሰቃየኝ የማወራዉ ለሱ ነበር፡፡
በጣም እጅግ ሲበዛ በ…ጣ ም ይመክረኛል፣ ያፅናናኛል እኔም ምን እንደሆነ አላዉቅም እፅናናለሁ፣ ወዲያዉ የማላዉቀዉ ጤንነት ይሰማኛል፡፡ በነበረን ጊዜያት አንዴ ብቻ ነዉ የማደርገዉን ነገር ያልነገርኩት እሱንም አስቤዉ አልነበረም በዚያን ጊዜ ሲጠፋብኝ በጣም ቅር አለኝ፤ በነጋ ቁጥር የፀሐይ ብርሃን ሳይሆን የርሱ ድምጽ ነበር የሚናፍቀኝ፣ ስልኬን ስሰጠዉ ምንም ቅሬታ አልነበረኝም ፣ የመኖሪያ ቤቴን ሰፈር ሁሉ ስነግረዉ ደስ እያለኝ ነበር፣ አሁን ግን እነዛ ድምጾቹ የሉም ርቀዉኛል፤ የሚገርመዉ ድምፁን የምናፍቀዉ ኔትወርክ በሌለበት ስፍራ ነዉ፡፡ ተራራ ባየሁ ቁጥር ሞባይሌን እንደ አቅጣጫ መጠቆሚያ ከመዳፌ አላርቃትም ነበር፤አሁንም አሁንም ደጋግሜ አያታለሁ ቻርጅ ባየሁ ቁጥር መሰካት ነዉ ከሞባይሌ ርቄ መሄድ ጥሩ ስሜት ከማይሰሙኝ ነገሮች መካከል ዋነኛዉ ነበር፡፡ ቀናቶች እየነጎዱ ጤናዬም መለስ እያለ ስለመጣ ወደ አዲስ አበባ መመለስ ፈለኩኝ እንድመለስ ያደረገኝ የጤናዬ ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ እሱን የማግኘት ፍላጎቴ ካቅሜ በላይ ስለሆነብኝም ጭምር እንጂ ፡፡ ለነገሩ ወደዚህ ስመጣ ስራዬን ለቅቄ ነበር የመጣሁት ልቤ ግን ክፍል ለማለት ወደኃላ አልል አለኝና አስጨነቀኝ፡፡ደብረ ብርሃን ስደርስ ጭንቀቴ እየጨመረ ሄደ፣ መንገዱ ራቀብኝ፣

ማክሰኞ 18 ማርች 2014

ጊዜና ዘመን

ጊዜ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ይታሰባል ይከወናል ትናንት ዛሬን እየሆነ ይቆጠራል፤ ትናንትናና ዛሬ ተደማምሮ ሳምንት ሳምንታትና ቀናት ተደማምረው ወራትና ዓመታትን /ሦስት መቶ ስልሳ አምስት ቀናትን/ ይሰጣሉ፡፡ ከአዳም ጀምሮ ዓመት ይቆጠራል፡፡ የዓመታት ጥርቅም ዘመን ተብሎ ይጠራል ዘመን ረጅም ጊዜ ነው ወይም አንድ አይነት አገዛዝ አምልኮ ሌላም የተደረገበት ጊዜ መጠሪያ ነው፡፡
       ዘመን የተፈጠርንበት /የተወለድንበት/ ትምህርት የጀመርንበት፣ ሥራ የያዝንበት፣ መከራን ያየንበት፣ ከውድቀታችን የተነሳንበት፣ የተማመንበት፣ የተፈወስንበትወቅት ማስታወሻ /መጠሪያ/ ሊሆን ይችላል፡፡
       ወደ ፍሬ ነገሩ ልምጣና ከብዙ ሰዎች አንደበት ስሰማና ከብዕራቸው የዕምባ ጠብቃ ሳነብ ብዙዎች ዘመንና ጊዜን ሲደግፉ በከንቱ ስሙን ሲያጠፉ ሲኮንኑ አዳምጣለሁ አነባለሁ ‹‹አይ ዘመን፣ አይ ጊዜ›› ‹‹ጊዜው ነው፣ ዘመኑ ነው›› ሲሉ ነገር ግን ጊዜና ዘመን ምን አደረገ ምንስ በደለ ጊዜና ዘመን በራሱ ምን ያመጣው ለውጥ ምንስ ያደረሰው ተፅዕኖ አለ? አንዳንድ ፀሐፍት እንደሚሉት ዘመንና አህያ አንድ ነው ይላሉ አህያ እንዳሸከሟትና የጫኑባትን ይዛ እንደምትገኝ ዘመንም

‹‹ቅዳሴ›› ክፍል -2-

አይነጋ የለ ነጋ ጊዜው 1130 ሰዓት ነው የሞላኋት የግድግዳ ሰዓቴ ድምፅ አሰማች እኔም ከእንቅልፌ ነቃሁ ሲረፍድብኝ እንዳላደርኩ ሳይረፍድብኝ ወደ ቅዳሴ ሄድኩ የቀን መዘውሩ ተገባዶ ሌሊቱ ለንጋት ስፍራውን መልቀቁን የተገነዘበ ሕዝበ አዳም ታጥቆ ተነስቷል ፀሐይ የንጋት ብርሃኗን ለመፈንጠቅ ሰማዩን አድርጋዋለች ነጭ ነጠላ የለበሱ ምዕመን መንገዱን ሞልቶታል አብያተ ክርስቲያናት የጥሪ ደውላቸውን (ድምፃቸውን) እያሰሙ ነው ሱቆችም የአሁኗን ንጋት በጥዋፍና ሻማ ዕጣን ሽያጭ ጀምረዋል ነዳያን ቤተክርስቲያን ጌጥ መስለው ከደጇ በረድፍ ተቀምጠዋል አስቀዳሹ እኔም አላረፈድኩም በሚል ስሜት በርጋታ እየተራመድኩ የደጃፉን በር ተሳልሜ ከግቢው ከመግባቴ ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ …›› የሚለውን የካህኑ ድምፅ በዜማ ተሰማኝ ተፈጥሮ ካስዋበው ከቤተክርስቲያኑ አጸድ ሥር ተጠንቅቄ በመቆም እጆቼን ከላይ ሆኖ ወደሚያየኝ አምላክ በማንጋጠጥ ዘረጋሁ ዙሪያው ጭር ያለው ግቢ በምዕመናን እየተጨናነቀ መጣ የቅዳሴውየተሰጥኦዜማ ሥፍራውን የመላዕክት ከተማ ኢዮር፣ ኤረር፣ ራማን አስመስሎታል የዕጣን የሽታ መአዛ ግቢውን አውዶታል ነፍሳችን እጅግ ተደስታለች ቅዳሴውን የሰማይ አዕዋፍ በድምፃቸው አብረው ሲያጅቡት የበለጠውን ውበት ሰጥተውታል የዕጣን ጢስ ወደላይ ማረግ የተመለከተ ልቡናችን አብሮ ከመንበረ ፀባኦት ደርሷል

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...