ሐሙስ 28 ጁላይ 2022

"መጀመሪያ እንድትሸነፍ የሚያደርጉህን ምክንያትህን አሸንፍ"

 ጀግናችን አበበ ቢቂላ በባዶ እግሩ ሮጦ ጀግንነትን ከመቀዳጀቱ በፊት 35ኪሎ ሜትር እንደሮጠ ሆዱን አመመው፤ ይኽም ሕመም ሩጫውን እንዲያቋርጥ ሊያደርገው ከጫፍ የደረሰውን ውሳኔ እንዲቀይር ያደረገው ከላይ የጠቀስኩት የአለቃው ምክር ነበረ። 


የድል ምልክታችን አበበም ወደ ልቡ ተመልሶ ሕመሙን ችላ አለው። ሩጫውን ቀጠል፤ ዛሬ የምንኮራበትን ድል አስመዘገበ። አበበን ለድል ያበቃው በዓለም አደባባይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ እንዲውለበለብ ያስቻለው ሕመሙን ማሸነፉ ነው። 


እኛም እንዳናሸንፍ የሚያደርጉን፣ የሚያዋርዱን፣ ከክብር ዝቅ የሚያደርጉን፣ መለያየት ላይ እንድናተኩር የሚያደርጉን፣ ዘረኞች እንድንሆን፣ ለኔ ብቻ እንድንል ያደረጉን ሕመሞች አሉብን። 


ድል ለመቀዳጀት፣ በዓለም አደባባይ አንደኞች እንድንሆን፣ ከፈለግን መጀመሪያ እንድንሸነፍ የሚያደርጉንን ምክንያቶች እናሸንፍ። 


መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል " ጥቃቅኑን ቀበሮዎች አጥምዳችሁ ያዙ" እንዚህ ቀበሮዎች ጥቃቅን መሆናቸው ሳይሆን የሚያጠፉት ሰፊ የወይን እርሻ ነው ግምት ሊሰጠው የሚገባው። በዘመናችንም ችላ የምንላቸው ጥቃቅን የመሰሉን ለዓመታት አዕምሯችን ላይ የተሰሩ ነገሮች ዛሬ ላይ ለእርስ በርስ ጦርነት፣ ለስደት፣ ለሞት፣ ለጥላቻ፣ ለዘር እልቂት እየዳረገን ይገኛል። 


እንድንሸነፍ ከሚያደርጉን ነገሮች መካከል አንዱ ዘረኝነት ነው፤ ለማሸነፍ ከፈለግን መጀመሪያ ዘረኝነትን የተጠናወተው ማንነታችንን ማሸነፍ ይኖርብናል። 


ሌላው ጥላቻ ነው "ወንድሙን የሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው" እንዲል መጽሐፍ ጥላቻ የዕድገት/የአሸናፊነት ጸር ነው። ስለዚህ መጀመሪያ ጥላቻን እናሸንፍ። ከዚያ ወደቀደመ ክብራችን እንመለሳለን። አለበለዚያ የሶስት ሺ ዘመን ታሪካችንን እናበላሻለን። 


ሁሌም አሸናፊ ትሆን ዘንድ የሚያሸንፍህን አሸንፍ።

መልካም ጊዜ

ደረሰ ረታ 


ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...