በክፍል
ሁለት ትዝታችን ነቢዩ ዳንኤልን የሥራ ባልደረቦቹ የሆኑ ሹማምንት በስልጣን ጥማት እና በሹመት ቅናት ከንጉሡ ጋር መክረዉ ህግ አዉጥተዉ
ለርሱ ለመገዛት ወስነዉ ነገር ሸረቡ ዳንኤልም እንደጠበቁት ከወጥመዳቸዉ ገባላቸዉ፤ እዉን ንጉሥ ዳርዮስ እና ንግስተቱ ዳንኤልን
እንደተባለዉ ወደ አንበሶች ጉድጓድ ይከቱት ይሆን? አናብስቱስ ይበሉት ይሆንን?
‘’
ንጉሡም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ በጣም አዘነ ያድነዉም ዘንድ ልቡን ወደ ዳንኤል አደረገ፤ ሊያድነዉም ፀሐይ እስኪገባ ድረስ ደከመ፡፡
‘’ ዳንኤል 6÷14
ዳርዮስ
ያስብ እንጂ አልተሳካለትም፤ አጣብቂኝ ዉስጥ አስገብተዉታልና፡፡
ዳንኤል
ወደ አንበሶች ጉድጓድ ተጣለ፡፡
በስተመጨረሻ
ንጉሡም ዳንኤልን የሚያመልከዉ አምላኩ እንደሚያድነዉ ያምናልና
‘’ሁል
ጊዜ የምታመልከዉ አምላክህ እርሱ ያድንህ አለዉ’’
ሹማምንቱም
ጉድጓዱን እንዳይከፈት የሚቻላቸዉን ሁሉ አደረጉ፤ ንጉሡም እያዘነ ወደ ቤቱ ሄደ እራትም ሳይበላ እንቅልፍም በአይኑ ሳይዞር አደረ፡፡