ማክሰኞ 24 ማርች 2015

ፍቅር!



ፍቅር
ስለፍቅር እናዉራ ካልን እጅግ ተቀድመናል፣ ብዙዎች ባማረ ስንኝ በተዋበ ዜማ አወድሰዉታል አብጠልጥለዉታልም፤ የልብ ብሔራዊ ዜማ እስኪሆን እያነባንና እየደማን የልብን ሰንደቅ እየሰቀልን እና እያወረድን እያከበርንና እየተዋረድን ብዙ አዚመናል፡፡ እንደያቅማችን እኛም ቢሆን በጊዜዉ ስንኝ ቋጥረናል፤ እንዲህ እያልን
                                    ኤድያ! ፍቅር
አበድን ….
        ከነፍን ….
 አለኝ
        አልበላ
አላት
       አልጠጣ
አቅበጠበጠን
      አንዘፈዘፈን
ግሞ ተጋግሞ
 … ተቀጣጥሎ መተንፈሻ
አሳጥቶን
ጣን
   ዓይን ገባን
ከዓይን ያዉጣችሁ
    ያዝልቃችሁ
       አሉን
" አሜን" ሳንል
ከአንደበታቸዉ ሳይጨርሱት
            መርቀዉን
            እንደተገናኘን
አፍታም ሳንቆይ ወዲያዉ ተለያየን፡፡
(ደረሰ ረታ)
ቋጠሮ ቋጥረን እምባችንን አብሰን መሃላችንን አፍርሰን ዳግም እንደገና ለፍቅር ስንል በፍቅር ጦር ሜዳ እንሰለፋለን ሌላ ምንም አይደለም በቃ ፍቅር ስለሆነ ብቻ!
ደግሞ ትንሽ እንቆይና
ሌላ የስንኝ ቋጠሮ ይገመዳል፤
……
እንሰነባብትና ምሬታችንን መለኪያ ቋጠሮ …. በየጎዳናዉ እንቀባጥራለን፤
" ይህቺ ሴት "
ያቺም ኋሜተኛ ይቺም ስሞተኛ
ላላማት ላታማኝ
ከማን ተነጥዬ
ከየትኛዋ ልተኛ?
እኔንስ ጨነቀኝ እኔንስ ጠበበኝ
ከጎኔ የሳባት አጥንት እየወጋችኝ
ሥሄድ ተከትላኝ ስመጣ እየገፋችኝ
መቆሚያ መቀመጫ
መሞቻ አሳጣችኝ፡፡
እስኪ ስለፍቅር እንቀኝለት ቅኔ!
(ደረሰ ረታ)
ያለፍቅር እንደማይሆን ስናዉቀዉ በተደበላለቀ ስሜት ለእርግማንና ለፀፀት እንዲህ ስንኛችንን እንቋጥራለን
መከራዬ ትንገስ
ችግሬም ትወደስ
እስከ ዘለዓለም ትሁን የኔ ቅርስ
በድዬ ከሆነ ፍቅሬን ገፍቼ
አርክሼም ከሆነ ክብሩን ረስቼ
…. … አልያ ግን  …. አልያ ግን
በዳዮቼን ሁሉ ገፊዎቼን ሁሉ
ይገፉ አልልም!
ይከፉም አልልም!
… … ግን … …
ይማሩ … ተበዳይን ይካሱ፣
ፍቅርን ከል ጥቀርሻ ስላለበሱ
… … ፍቅር ሆይ …
መስክሪኝ! ፍረጂኝ!
ይህን ክፉ በደል
ክፈይኝ ወረታዉን
የፍቅር ምላሹን፡፡
(ደረሰ ረታ)
ደግሞ ስናገኝ ጮቤ እንረግጣለን፤ ስንጎዳ እናለቅሳለን፡፡ ነገር ግን ሁላችንም ልብ የማንለዉ ነገር መበደላችንን፡፡
እናቅርብ ዉዳሴ ሲያሰኘን ወቀሳ
ለትንታኔዉ በካህሊል ጊብራን ድርሰት እንዲህ እያልን እንነሳ
ፍቅር!
መንገዶቹ አስቸጋሪ አቀበት ቢሆኑም ፍቅር ሲጠቅሳችሁ ተከተሉት፡፡ በላባዎች መካከል የተደበቀዉ ሰይፍ ሲያቆስላችሁ ክንፎቹም ሲያቅፋችሁ ተሰጡት፡፡
የሰሜኑ የነፋስ የአትክልት ስፍራን እንደሚያወድም፣
ድምፁ ህልሞቻችሁን ቢበትንም፣
ሲያናግራችሁ እመኑት፡፡ ፍቅር እንደሚያነግሳችሁ ሁሉ ይሰቅላችኋልና፡፡ለዕድገታችሁ እንደሆነዉም ሁሉ ለምልመላችሁ ነዉና፡፡
ወደ ጫፋችሁ ወጥቶ በፀሐይ ዉስጥ የሚያርገደግዱትን እጅግ ለስላሶች ቅርንጫፎቻችሁን በፍቅር እንደሚዳብሰዉ ሁሉ፣ እንዲሁም ወደ ሥሮቻችሁ ወርዶ በመሬት ዉስጥ በይዞታችሁ ይነቀንቃችኋል፡፡
እንደ ስንዴ ነዶ ወደ ራሱ ይሰበስባችኋል፡፡
እርቃን ሊያደርጋችሁ ይወቃችኋል፡፡
በገለባዎቻችሁ እንድትለዩ ያነፍሳችኋል፡፡
ለንጣት ይፈጫችኋል፡፡
እስክትለስልሱ ያቦካችኋል፡፡
ለእግዚአብሔር ቅዱስ ግብዣም ቅዱስ እንጀራ እንድትሆኑ ከዚህ በኋላ ለቅዱስ እሳቱ ይዳርጋችኋል፤
የልባችሁን ምሥጢሮች እንድታዉቁና በዚህ ዕዉቀት የልብ ሕይወት መአዛ እንድትሆኑ ፍቅር እነዚህን ነገሮች ሁሉ ያደርግባችኋል፡፡
ነገር ግን ከፍርሃታችሁ የተነሳ የፍቅርን ደስታ ብቻ ብትፈልጉ እርቃናችሁን ሸፍናችሁ ከፍቅር አዉድማ ገለል ብትሉ ይሻላችኋል፡፡ … ፍቅር ራሱን እንጂ ምንም አይሰጥም፡፡ ከራሱም በቀር ምንም አይቀበልም፡፡
ፍቅር ማንንም ገንዘቡ አያደርግም፡፡ለማንም ገንዘብ አይሆንም፤ፍቅር ለራሱ በቂ ነዉና፡፡
ስታፈቅር " እግዚአብሔር በልቤ ዉስጥ ነዉ " አትበል፤ ይልቁን ግን " እኔ በእግዚአብሔር  ልብ ዉስጥ ነኝ " በል እንጂ፡፡
የበቃህ ሆነህ ካገኘህ ፍቅር ጎዳናህን ይመራልና የፍቅርን ጎዳና መምራት የምትችል አይምሰልህ፡፡ ራሱን ከመሙላት በቀር ለፍቅር ሌላ ምኞት የለዉም፡፡
ነገር ግን ካፈቀራችሁና ምኞቶች እንዲኖራችሁ ከፈለጋችሁ ምኞቶቻችሁ እነዚህ ይሁኑ፤
ቀልጦ ቃናዉን ለሌሊት እንደሚያዜም ጅረት መሆን፤ 
የርህራኄን ብዛት ህመም ማወቅ (መቅመስ)፤
 በጋዛ ራሳችሁ የፍቅር ማስተዋል መቁሰል በፈቃደኝነትና በደስታም መድማት፤
ክንፍ ባለዉ ልብ በጎህ ተነስቶ ስለሌላዉ የፍቅር ቀን ምስጋና ማቅረብ ፡፡
በቀትር ሰዓት አርፎ የፍቅርን በረከት ማሰላሰል፤
ማታም በምስጋና ወደ ቤት መመለስ፡፡
ከዚያ በኋላ በልባችሁ ዉስጥ ለተወዳጆቻችሁ ፀሎት በከንፈሮቻችሁ ላይ በዉዳሴ ዜማ መተኛት፡፡   
ፍቅር ወደድንም ጠላንም እዉነቱ ይህ ነዉ፤ 
እዉነትም የፍቅር ትርጉሙ ያልገባን ገብቶንም እንዲህ መኖር ያልፈለግን ከፍቅር አዉድማ ገለል እንበል፡፡ ቅዱሱን ስፍራ በረከሰ ማንነታችን አናርክሰዉ፡፡ ወልደ አምላክ የደም ዋጋ የከፈለበት ነዉና፡፡

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...