ዓርብ 5 ጁን 2020

ወዴት ነን?


*. ብዙዎች ስለ ዘራቸው እምነታቸውን ዘንግተዋል፣
*. ብዙዎች ስለ ፖለቲካ ሲሉ እምነታቸው ላልቷል፣
*. ብዙዎች ስለ ጥቂት ብዙ ነገር አጥተዋል፣
*. ብዙዎች የእምነት ጥንካሬያቸውን ስለ እምነት ተቋም ይዞታቸው ገብረዋል፣
*. ብዙዎቹ በየቡድናቸው ስለ መደጋገፍ እውነትን፣ እምነትን፣ ሐቅን፣ በቁሟ ቀብረዋታል፣
*. ብዙዎች ስለ እኔን ይድላኝ፣ የኔ ይቅደም፣ የኔ ይብለጥ አገርን ወደኋላ አስቀርተዋል፣
*. ብዙዎች ስለ ምድራዊው ነገር ሰማያዊ ነገራቸውን በጥቅም አስይዘዋል፣
*. ብዙ የእምነት አባቶች የምእመኖቿ መሪ ሣይሆን የምድር ርስት ጉልት ይጨነቃሉ፣
*. ብዙዎች የሚሰባሰቡት ከአንድ ሁለት ስለሚሻል ሳይሆን ከዘርህ ዘሬ፣ ከባህልህ ባህሌ፣ ከሐይማኖትህ ሐይማኖቴ፣ ከፖለቲካህ ፖለቲካዬ፣ ከድርጅትህ ድርጅቴ ይበልጣል ብለው ነው፣
*. ብዙዎች ስለውጫዊ ልዩነታቸው ውስጣዊ አንድነታቸውን ክደዋል፣
*. ብዙዎች ብዙ በጎ ነገርህን ቀብረው በጥቂቱ ስተትህ ሐዘን ተቀምጠዋል፣
*. ብዙውች ለመከባበር ቦታ ነፍገው መቻቻል አንግሰዋል፣
*. ብዙዎች በራስ መንገድ ከማሰብ በቡድን ማሰብ ተጸናውቷቸዋል፣
*. ብዙዎች እውነትን ሳይሆን ሰወችን በመከተል ዘመናቸውን ይጨርሳሉ፣
*. ብዙዎች በጋራ መውደድ እና በጋራ በመጥላት ተጠልፈዋል፣

ሥጋ በል እጽዋት


ከላይ ባለ ገጽታቸው እጽዋት መስለው እጽዋት ናቸው ብለው ነፍሳት ሲጠጓቸው/ሲቀርቧቸው በውስጣዊ ማንነታቸው ሥጋ በል እጽዋት ናቸው። 
 
ሰወችም ዘመድ እጽዋት ናቸው ሥንል ሥጋ ዘመድ፣ ልጅ፣ እህት፣ ሚስት፣ አዛውንት፣ መነኮሳት፣ የሚበሉ የሚደፍሩ ሥጋ በል እጽዋት አመንዝራና ቅንዝራም ናቸው።
 
በአለም ላይ በወረርሽኝ የተከሰተው COVID19 ባስከተለው በቤት መቀመጥ #stayhome ብዙዎች የውሻ ባህሪ ያላቸው ወንዶች ወንድም፣ አባት፣ አጎት፣ ዘመድ መስለው የዋሃን ሴቶችን ያለ እድሜ ገደብ በመድፈር ከክብር አነውረዋቸዋል።
 
ሰው ስንላቸው እንስሳ እየሆኑ ጨቅላ ሴቶችን የበሉ እንስሳ ወንዶች ተበራክተዋል፤ በየሚዲያው ከሰማናቸው ከመቶ በላይ ሴቶች በዚህ ጥቃት የስነልቦና ስብራት፣ የሞራል ውድቀት፣ የሥጋ ጉዳት ቤት ይቁጠራቸው።
 
ይህ ክስተት እየተነሳን ማውገዝ የከፋ ነገር ባይሆንም ችግሩ በዚህ ብቻ አይፈታም።ልጆቻችንን ወንድሞቻችንን በቤት ስናሳድግ ሴቶችን አክባሪ፣ ወንጀልን የሚከላከል፣ ዝሙትን የሚጸየፍ አድርገን ልንቀርጻቸው ይገባል።
 
ሴቶቻችንም እያንዳንዷ ድርጊታችሁን ዝሙትን ቀስቃሽ ከሆነ ተግባራት ልትጠበቁ፣ ልጆቻችሁን እና እህቶቻችሁን ከዚህ ተግባር ልትገድቡ ይገባል። 
 
መንግሥትም አገርንና ትውልድን አንገት የሚያስደፋ ተግባራትን በሚያከነረውኑት ላይ ከሌሎች አገራት ህግ ተሞክሮ በመውሰድ ጠንካራ ህግ በማውጣት የማያዳግም እርምጃ በመውሰድ የሴቶችን የመኖር መብት ከሥጋ በል እጽዋት ወንዶች ሥጋት ነጻ ሊያደርግ ይገባል።
 
ደፋሪዎችን አወግዛለሁ፤ ከተጎዱ ሴቶች ጉን እቆማለሁ።

ዓርብ 15 ሜይ 2020

ለምን ትኖራለህ? ወዴት ነህ? ምን ይታይሃል?


ለምን ትኖራለህ
ወዴት ነህ?
ምን ይታይሃል?
          በሳይንሱ ክፍለ ዓለም ስንጓዝ የሰው ልጅ ለመኖር ኑሮን ወይም ሕይወትን ለማሸነፍ በቂም ባይሆን አስፈላጊ የሚሆኑት ምግብ መጠለያ ልብስ ወሳኞች ናቸው ይህንን ለማሟላት ‹‹ጥራህ ግራህ›› ብላ ተብሏልና ይወጣል ይወርዳል ላቡን ያነጠፈጥፋል የሰው የበታችና የበላይ ይሆናል ለመኖር ለብቻውም በሕብረትም ይሁን ብቻ ይለፋል፡፡ ከሳይንሱ ዓለም መለስ ብለን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስንመለከትና ወደ ማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 4÷4 አካባቢ ስናነብ ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም …›› የሚል እናገኛለን በዚህም መሠረት ቅድም ከተጠቀሰው በተጨማሪ የእግዚአብሔር ቃል /ቃለ ወንጌል/ ያስፈልገናል/ ለመኖር ማለት ነው፤ ግን ለምን እንኖራለን?

ሐሙስ 14 ሜይ 2020

ዘመድኩን በቀለ: ከራየን ወንዝ ማዶ


ዛሬ ለየት ባለ መልኩ የምንመለከተዉ በልዩ አፃፃፉ እና በብዙ ተከታዮቹ የሚታወቀዉ ስለ ዘመድኩት በቀለ (ዲያቆን/መምህር) ሲሆን እንደሚታወቀዉ በተደጋጋሚ ፌስቡኩን እንደሚዘጋ የሚታወቅ ሲሆን ወደፊትም እንደሚዘጋበትና አገልግሎቱን እንደሚያቋርጥበት ይታወቃል ስለዚህ ሌላ መፍትሔ ማምጣት ግድ ሆኗል፡፡
ራሱ ዘመድኩን እንዲህ ያቀርበዋልና ስሙት፤ ተከተሉት፡፡
         ወደፊት ልንሠራቸው ያቀድናቸውን ዕቅዶች በሙሉ አስፍሬያለሁና ጦማሯን አንብቧት። ለሌሎችም #SHARE በማድረግ አጋሯት።
#ETHIOPIA | ~ እንዴት ናችሁልኝሳ ? ሀገሩ፣ መንደሩ፣ ሰፈሩ፣ ቀዬው ሰላም ነው? እኔማ አምላክ ክብር ይግባው ደህና ነኝ።
ይኸው ፌስቡክ ድራሽ አባቴን ቢያጠፋኝም እኔ ዘመዴ፣ የድንግል አሽከር የማይሰበረውን የኢትዮጵያዊነት መንፈስ እንደያዝነ፣ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ውበት አጊጠን፣ እንደ መስከረም ወር ጠሐይ ፈክተን፣ በገነት መካከል እንደ ቆመ የወይራ ዛፍ ለምልመን፣ እንደ ኃያሉ አንበሳ እያገሳን፣ እንደ ነብር፣ እንደ አቦ ሸማኔ እየፈጠንነ፣ እንደ ንስር ታድሰን እነሆ በአዲስ ጉልበት፣ በአዲስ ወኔ፣ አለን ነበረን እንል ከነበረው አቅም ላይ እጥፍ ጨምረን፣ እንደ አልማዝ እንደ ዕንቁ እያንጸባረቅን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የፌስቡክን ኳራኒትን ፈጽመን ይኸው ዳግም ተከስተናል። 
እንደተለመደው እንደ አማኝነታችን ስለ ቅድስት የኢትየጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን፣ የኢትዮጵያ ዜጋ በመሆናችን ደግሞ ስለ ውቢቷ ሃገራችን መወያየታችንንና መመካከራችንን፣ መሟገት፣ መፋጨታችንንንም አጠንክረን እንቀጥላለን። መፋታት፣ ማፈግፈግ፣ መሸሽ፣ ማምለጥና፣ ማስቀየስም የለም። ሰምና ወርቅ ፈልግ የሚል ጦማር እኔ ጋር አይሠራም። እንደ ሐረር፣ እንደ ሲዳሞ ግሩም ጣዕም ያለው ቡና አስሬ ተለክቶ እንደተለቀመ፣ ታጥቦ ተቀሽሮ፣ ተቆልቶ፣ ተወቅጦ ተፈልቶ እንደወረደ ቡና ጦማሬን ትጠጡት፣ ፉትም ትሉት ዘንድ ከሃገረ ጀርመን፣ ከራየን ወንዝ ማዶ ለእናንተ መቅረቡን ይቀጥላል።

ማክሰኞ 7 ኤፕሪል 2020

ስኬታማ ተቋም ለመፍጠር Part Three


1. ሰው መምረጥ


*በብቃቱ፣ በክህሎቱ፣ በተሠጥኦው፣ በትምህርት ዝግጅቱ፣ ወዘተ ከአላማችን ጋር የሚቀራረብ ግባችን ለማሳካት የሚያስችል ሰው መምረጥ አስፈላጊ ነው።
ተቋማት የሥራ እድልን ከመፍጠር ጎን ለጎን ተቋምን ሊያሳድጉ ስኬትን ሊያስመዘግቡ የሚችሉ እና የአገርን ሥም በአለም መድረክ ጭምር ሊያስጠሩ የሚችሉ ሠራተኞችን ከጅምሩ ከላይ በተዘረዘሩት መሥፈርቶች መመልመል ይኖርባቸዋል።

ይህ ሠው ታድያ ግላዊ ጉዳዩን ወደ ጎን ያደረገ የአገር ፍቅር ለወገን ክብር ያለውና ሥራውን እሴት ጨምሮ የሚሰራ ተደርጎ መሠራት አለበት።

የማይረካ፣ የመማር፣ የመሥራት፣ ሁሌም ጀማሪ የሆነ፣ ሁሌም ለአዲስ ነገር ጉጉ የሆነ፣ ዘወትር ለውጥን አሻግሮ የሚያይ፣ ሁሌም ለሥራ የሚሮጥ፣ ጥማት ያለበት ሰው መምረጥ ይኖርብናል።

ሰዉ በመምረጥ ሂደት ዉስጥ መዘንጋት የሌለብን ነገር ምናልባት ከቦታዉ ጋር የሚሄድ ካልሆነ በቀር አለበለዚያም የትምህርት ዝግጅቱ ከመለያየቱ በቀር ‹‹የማይረባ›› የሚባል ሰዉ እንደሌለ ልብ ልንል ይገባል፡፡

ሐሙስ 12 ማርች 2020

ስኬታማ ተቋም ለመፍጠር Part Two


በክፍል አንድ እንዴት ስኬታማ ተቋም መፍጠር እንደሚቻል በጥቂቱ መዳሰስ ጀምረን በይደር ማቆየታችን ይታወቃል ክፍል ሁለትን እነሆ፡-



ሰዉን እንዴት መፍጠር ይቻላል?
ሰዉ በእግዚአብሔር በአርአያዉ እና በምሳሌዉ የተፈጠረ ሆኖ እንዴት ድጋሜ መፍጠር ይቻላል? የሚሉ ጥያቄዎች ሊነሱ ይችላሉ፡፡ አዎ! ጥያቄዉ ጤናማ ነዉ፡፡
ሰዉ በፆታ ወንድ እና ሴት ተብሎ በሁለት እንደተከፈለ ሁሉ ሰዉ ሆኖ በእኩልነት አንድ ሆኖ ሊያስቀጥለዉ የሚችለዉን ማንነት መፍጠር ይቻላል፡፡ እንዴት?
ሰዉን መፍጠር የሚቻለዉ በሶስት ነገር ነዉ፤

እሑድ 8 ማርች 2020

ሴቶች ተቋምን ለመፍጠር ያላቸዉ ብቃት March 8

ሴቶች ይችላሉ።

ከዚህ ቀደም ስለ ተቋም ስኬት እየተነጋገርን እንደነበረ ይታወሳል ለዛሬ ከዚያው ቀጣይ ክፍል የተቀነጨበ ስለሴት ልጅ ችሎታ የሚያረጋግጥልን ጽሑፉ መታሰቢያነቱ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ላሉ ሴቶች እና ህልማቸውን እንዳያሳኩ በማይረቡ ጭንጋፍ ወንዶች የተሳናከለባቸው የታገቱ እህት ተማሪዎች ይሁንልኝ።

$$$$$$$$$$$$$$$$$

2. ሰው መሥራት

የአንድ ሰው ዋጋ እጅግ ውድ እና በምንም የመገበያያ ገንዘብ ሊተመን የማይችል ነው፤ በአንድ ተቋም ውስጥ ከሰው የሚበልጥ ነገር የለም።
ስለዚህ የሰራተኛን አመለካከት፣ የሰራተኛን ችሎታ፣ የሰራተኛውን አቅም ማሳደግ ከሁሉ ነገር መቅደም ይገባዋል።
ለውጤታማነቱ ተከታታይነት ያለው ክትትል በጥንቃቄ ሊተገበር ይገባል።
እርስ በርስ ፍሬያማ የሆነ ውድድር እንዲኖር አዎንታዊ የእርስ በርስ ተቋማዊ ውድድር እንዲኖር ማድረግ አንዱ ሰው የምንሰራበት መሣሪያ ነው።
ሰው በዚህ መልኩ በጥሩ ሁኔታ ከተገነባ ጠንካራ የሰው ሃይል ስኬታማ ተቋምንም ሆነ አገርን መገንባት ይቻላል።
አገርንም ሆነ ተቋምን በጠንካራ መሠረት ላይ ለመመስረት የሴቶች ተሳትፎ ትልቅ ድርሻ አለው፤ ሴቶች ትውልድን በመቅረጽ ላይ ትልቁን ሚና ስለሚጫወቱ።
አገራትም ሆኑ ተቋማት የሴቶችን ቁጥር በመጨመር ለዘላቂ ስኬት መትጋት ይኖርባቸዋል።
በምሳሌ ላስረዳ:- ሴት ከሁሉም የሰው ፍጥረት ጋር ቀዳሚ እና ዘላቂ ቁርኝነት ስላላት ሚናዋ ከፍ ያለ ነው። ምክንያቱም ሴት ልጅ የወንድ ልጅ የተፈጥሮ አጋር ከመሆኗ ባሻገር እናት ነች፣ (ልጇን በስነምግባር አንጻ ለስኬት ብቁ አድርጋ መቅረጽ ትችልበታለች) ሞግዚት ናት፣ (ጤናማ እና በአካል የዳበረ ለትምህርት እና ለሥራ ዝግጁ የሆነ ዜጋ መፍጠር ትችላለች)፣ የሥራ ሃላፊ ነች፣( በቅርበት በእናትነት እና በእህትነት ጸጋ የሥራ ባልደረቦቿን የተጣመመውን አቃንታ የተበላሸውን አስተካክላ ለመጓዝ የሚያክላት እና ከርሷ የተሻለ ልምድ ያለው የለም)፣ ሚስት ናት፣( ባለቤቷን ለተሳካ ውሎ በደስታ እና በተነቃቃ መንፈስ ከቤት መሸኘት የምትችል በውሎው ደስተኛና ስኬታማ እንዲሆን የምታስችል መግነጢሳዊ ጸጋ የተላበሰች ነች) እህት ናት፣( ትንሽ ሆና ትልቅ በእድሜ አንሳ አስተሳሰቧ ትልቅና ሐላፊነትን መሸከም የሚችል ነው።)
ይህ ሁሉ ሴትን ልጅ የዚህ አለም ማጣፈጫ ጨው ናት ብንል ማጋነን አይሆንብንም ሰው መሥራት ትችላለችና።

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...