ሰኞ 2 ፌብሩዋሪ 2015

ከማይረባ ፍቅር የረባ ጥል ይሻላል



ነገሩ እንዲህ ነዉ ወደ ስራ ገበታችን ለመሄድ ለገሃር ባቡር ጣቢያ የከተማ አዉቶቡስ እየጠበቅን እንገኛለን፤ 36 ቁጥር ያለወትሮዋ በጣም ከማርፈድዋ የተነሳ መሰላቸትም ድካምም ይታይብናል አንድ ልጅ'ግር ከሰልፉ መካከል ደክሞኛልና አረፍ ልበል በማለት ከፊቱና ከኋላዉ ላሉት ወረፋ ጠባቂዎች አሳዉቆ እዛዉ አከባቢ ድንጋይ ላይ አረፍ አለ፡፡ ሰልፉ እጅግ እየረዘመ ከመሄዱ የተነሳ አንድ አዉቶቡስ ብቻ የሚችለዉ አይመስልም ነበር፡፡
ቀርታ አልቀረችም ተስፋ ቆርጠን ሳናበቃ መጣች፤ ሁሉም ኪሱን ፣ ቦርሳዉን ፣ …. መፈታተሸ ጀመረ ተልመጥምጦ የነበረዉ ሰልፍ ቀጥ አለ፤ ፀጥታ ነግሶበት የነበረዉ ስፍራ አዉራዉ እንደተነካ የንብ መንጋ ታወከ፡፡ ቲኬት ቆራጩ ጎልማሳ እስክርቢቶዉን ከደረት ኪሱ አዉጥቶ ጆሮግንዱ ላይ ሻጥ አድርጎ ሰልፉን እኩል ገምሶ ጀብነን ብሎ ቆመ፡፡ ሰዉ ከቅድሙ ይልቅ ደሙፈላ፣ በዉስጣቸዉ ማጉረምረም የጀመሩትን ሳንቲም አምጡ አታምጡ ላይ ንትርኩ ጨመረ፡፡ በዚህ መካከል ያ ወጣት ወደሰልፉ ተመለሰ ከኋላ ከረጅም ርቀት ላይ ከሰልፉ ሌላኛዉ ጠርዝ ላይ "ተመለስ" የሚል ጩኸት ሰልፉን ድንጋጤ ፈጠረበት፤ ሁልም ሰዉ ድምፁ ወደ ተፈጠረበት  አቅጣጫ አይኑን ላከ ሰዉየዉ እየተንደረደሩ ሲመጡ ጤነኛ አይመስሉም ነበር፡፡"ዉጣ ብዬሃለዉ ዉጣ!" ጩኸቱ በረታ፣ እስከዚህ ሰዓት የጉዳዩ ባለቤት ጉዳዩን ልብ አላለዉም እጁን ሳንቲም ካስቀመጠበት ኪሱ ከቶ እያለ ክንዱን አፈፍ አርገዉ ያዙት …. በድንጋጤ እጁን እንኳን ሳያወጣ ደርቆ ቀረ፡፡ "ዉጣ! ባለጌ! እኛ እዚህ ቆመን የማነህ ፈጣጣ ከየትም መጥተህ ዘዉ የምትለዉ?"
እኔ ነዉ?
"ከአንተ ጋር እያወራሁ እኔ ነዉ ትላለህ ? ደፋር! "
ምን አደረኩ?
" ዉጣ ሰልፉን አትረብሽ"
ለምን?
" ሰዉዬ ነግሬሃለዉ በሰላም እንሂድበት ሰልፉን አትረብሽብን"
ሰዉየዉ እጅግ ትልቅ ከመሆናቸዉም የተነሳ አብዝቶ መናገርም "ባህላችን " ስላልሆነ ለረጅም ሰከንዶች ዝምታን መረጠ ሰልፉ ግን ስራዉን አላቆመም ልጁም ወደፊት ሰዉየዉም ሰልፉን እየታከኩ ፣ልጁን እየተሳደቡ እና እያመናጨቁ ወደፊት እያመሩ ነዉ፤
ከሰልፉ ኋለኛዉ ክፍል እንደገና በዕድሜ የሚቀርቧቸዉ ሰዉ " እስካሁን ሰማኖት ልጁወረፋዉ ነዉ እርሶ ወደ ቦታዎ ይመለሱ"
"ይቺ ደሞ ምን ትላለች? አንቺ ደሞ ምንሽ ተነካ?"
"ምንም አልሆንኩ! ልጅ ከሁላችን በፊት እዚህ ቆሞ ነበር ደከመዉ ከፊትለፊቱና ከኋላዉ ላሉት አሳዉቆ አረፍ አለ፤ ተራዉ ሲደርስ መጣ አንተ ምን ቤት ነህ ከኋላዉ መተህ ቡራከረዩ የምትለዉ? ዉጣ!"ልጁ ልቡ ተረጋጋ ስድቡና አላስፈላጊዉ ትችት ከርሱ ላይ ዘወር አለለት፡፡
ሰዉየዉ ግን አሁንም ሊበርዱ አልቻሉም ፤ ልጅየዉ ጎረቤቱ የሆነች ልጅ ታማ ሆስፒታል አድሮ ነዉ የመጣዉ ምንም እንኳን እንቅልፉም ድካሙም ቢኖርበት ስራ ስለነበረዉ ላለመቅረት ነበር ወደ ስራዉ ለመሄድ አዉቶቡስ እየጠበቀ የነበረዉ እና ሰልፍ ላይ ይህ ችግር የተፈጠረዉ፡፡
አባባ አላቸዉ፤ እኔኮ እያጭበረበርኩ አይደለም ተሰልፌ ነበር ሲደክመኝ  አረፍ ለማለት አስፈቅጄ ነዉ የሄድኩት እባክዎ በኔ የተነሳ አይጣሉ፡፡
"ዝም በል! አይናዉጣ!"
በቃ! እንዲያዉም ይሄ ሁሉ ፀብ እንዲህ ደክሞኝ እና እንቅልፍ ይዞኝ እያለ ስራዬን አክብሬ ወደ ስራ ገበታዬ ባልኩኝ ነዉ አይደል? ጥሩ ምክንያት ሆኑኝ በቃ አልሄድም! አያዉቁኝም አይደል?እኔም ከዛሬ በፊት አይቼዎት አላዉቅም፣ በዕድሜም ሆነ በሰፈር አንገናኝም፣ ጎረቤት ሆነን ቢሆን ኖሮ ጉድ በፈላ ነበር፤ ነገር ግን ከዛሬ ወዲህ አንገናኝም፡፡ ብዙ ፀቦች አይቼ አዉቃለሁ የእኔ እና የእርስዎ ፀብ ግን ይለያል ፀብ በደላላ የሚፈልጉ ነዉ የሚመስሉት ለነገሩ ከማይረባ ፍቅር የረባ ጥል ይሻላል፤ሰዉ እንደ እኔ እርሶ የረባ ፀብ ከተጣላ በሰፈር ሰዉ በሽማግሌ ይታረቃል አስመሳይ ፍቅር ግን ከሆነ እዉነተኛ ፍቅር ሳይፋቀሩ እንዲሁ ያልፋሉ ብሏቸዉ አመስግኖ ጥሏቸዉ ሄደ፡፡
ከማይረባ ፍቅር የረባ ጥል ይሻላል! አለቀ፡፡

ሰኞ 26 ጃንዋሪ 2015

ሊሰራ የማይወድ አይብላ



ዳንኤል ክብረት "ቁስል ተራ " ብሎ የፃፈዉን ካነበብኩ በኋላ በልቤ ሲላወስ የነበረ ሐሳብ ስለነበር ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሜ ልተነፍስ ተነሳሁ፤ የርሱን ሐሳብ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡፡ http://www.danielkibret.com/2015/01/blog-post_20.html#comment-form ወዳጄ ዳንኤል ሥራ አልሆን ሲለን ወደ ልመና ከገባንኮ ቆይተናል፤ አንተ የአካሉን ሥትል ሰዉኮ ለመለመኛ ብሎ ልጅ መዉለድ ከጀመረ ሰነባበተኮ፡፡ በአንድ ወቅት ትራንስፖርት ዉስጥ ቁጭ ብዮ የሆነ ሰዉ ጋቢ ተከናንቦ የጉሉኮስ ዕቃ ታቅፎ አጥሚት አፉ ላይ እንደደረቀ ህፃን እየበረረ ታክሲ ዉስጥ አስጥሉኝ እያለ ገባ ከበስተጀርባዉ ስንመለከት ማንም የሚከተለዉ ሰዉ ስናጣ የባሰ አትኩሮቶቻችንን ሳበዉ …. ይህ ሰዉ ለካንስ ይህቺ ዘዴዉ የመለመኛ መንገዱ ነበረች ……. ወንበር ከመያዙ የልመና ቃላት ማዥጎድጎዱን ተያያዘዉ፤ ( ባጭሩ ታሞ ጥቁር አንበሳ ተኝቶ እንደነበረ፣ ከሁለት ወር በላይ እንደቆየ፣ ከክፍለ ሃገር እንደመጣ፣ በህመሙ ምክንያት ረጅም ጊዜ ስራ ገበታዉ ላይ ስላልተገኘ ከሥራ እንደተቀነሰ፣ በዚህ ምክንያት ቤተሰቡን ማስተዳደር ባለመቻሉ የልጆቹ እናት ጥላዉ ቤተሰቦቿ ጋር እንደሄደች፣ አሁን እንዲህ ሆኖ የተገኘበት ምክንያት ለህክናዉ የሚሆን ገንዘብ በመጨረሱና መድሐኒቱን ከወሰደ በኋላ/ በፊት የሚመገበዉ ምግብ በማጣቱ ከአልጋዉ ተነስቶ ለልመና እንደወጣ ነበር የነገረን፡፡ አስጥሉኝ ማለቱም ከሆስፒታሉ ሲወጣ ያዩት የጥበቃ ሰወችም ሆኑ ሲወጣ ያዩት የጤና ባለሙያዎችን ማለቱ ነበር፡፡) ሁላችንም ያለንን ያህል በተለመደዉ ኢትዮጵያዊ ሩህሩህ ባህሪያችን ሰጠነዉ፡፡ሰዉየዉም ለምስጋና እንኳን ጊዜ ሳያገኝ፣ ሊሄድበት የፈለገዉንም ፒያሳ ሳይደርስ እዉነት ይሁን ዉሸት ለጊዜዉ ባናዉቅም "የምበላዉ ካገኘሁ በቃ ወደ ሆስፒታል ልመለስ" ብሎ ወረደ፡፡
ከቀናት በኋላ ደግሞ ይኸዉ ሰዉ ራሱ በምሰራበት መስሪያ ቤት ጉዳይ ኖሮት ሊስተናገድ በጣም አምሮበት ጥቁር ሙሉ ልብስ በነጭ ሸሚዝ ለብሶ ጥቁር መነፅር ሰክቶ ከተፍ አለ፤ ድኖ በማየቴ ፈጣሪዬን ጤናዉን ስለመለሰለት አመሰገንኩት፡፡ ያንን ዕለት ስላደረግነዉ መልካም ነገር ደስታ እና ኩራት ተሰማኝ … … የአንድ ሰዉ ህይወት ታድገናልና፡፡ሥራ ቦታ መሆኔ ነዉ እንጂ እንኳን እግዚአብሔር ማረህ፣ እንኳን ደስ አለህ፣ … ብለዉ ደስ ይለኝ ነበር፤ ባለማለቴ እጅግ ቆጨኝ፡፡
በዚያኑ ሳምንት ቅዳሜ ዕለት አራት ኪሎ ወደ ፒያሳ ሄጄ ሲኒማ አምፔር ጋር ስወርድ ወርቅ ቤቶቹ ጋር ያደፈ ጋቢ ለብሶ ያቺ የፈረደባትን የጉሉኮስ ዕቃ ታቅፎ እያቃሰተ ወገን አድኑኝ እያለ የመጀመሪያ ቀን ያቀረበዉን ምክንያት እየደረደረ ይለምናል፤ በሱ ቦታ እኔ አፍሬ እያማተብኩ አለፍኩት የዋሁ ህዝብ ጉዳዩን አላወቀ ሳይኖረዉ ካለዉ ላይ የቀረችዉን እያነሳ ሳይሳሳ ይሰጣል፡፡ የሌለዉ ከንፈሩን በሀዘኔታ እየመጠጠ "እግዚአብሔር ይማርህ እያለ ያልፋል" የሰዉ ልጅ ለምንድነዉ ርካሽ የሆነ ባህሪ የሚመቸዉ ብዬ ታዘብኩ፤ ….
ከጊዜ ብዛት ከተማ ዉስጥ ስዘዋወር በተደጋጋሚ ሳገኘዉ ባህሪዉ መጥፎ የምንለዉ አይነት ሰዉ ነበር ( ያጨሳል፣ በጣም ይጠጣል፣ ቁማር ይጫወታል፣ … ) ከረጅም ጊዜ በኋላ ለሆነ ንግስ በዓል ነጭ በነጭ ለብሶ ከጓደኞቹ ጋር አገኘሁት የኔ ቢጤ ሲለምነዉ መርጦ አዉጥቶ 10 ሳንቲም ሲሰጥ አየሁት፤ ፈራ ተባ እያልኩ "መስጠትም ታዉቅበታለህ? " አልኩት፡፡ "ምነዉ መስመር ላይ ተገጣጥመን እናዉቃለን እንዴ ?"አለኝ፤ ….
ባጭሩ ከዚህ ሰዉ ጋር ባደረግነዉ ዉይይት የቅድሙ ታሪክ ሁሉ ዉሸት እንደሆነና ከመስራት መለመን አዋጭ እንደሆነ በድፍረት ነገረኝ፤ ሰዉ ሆይ ስራ መስራትን ጠልተን ልመናን የምንኮራበት እና የምንመርጠዉ እስከ መቼ ነዉ?ልንሰራስ የማንወደዉ ለምንድን ነዉ?
ሊሰራ የማይወድ አይብላ! ያልሰራ አይብላ አላልኩም ስራ አጥቶ ሊሆን ይችላልና፤ በየስራ ገበታዉም ያላችሁ ለታይታ የምትሰሩ፣ የአለቃን ፊት እያያችሁ የምታለምጡ፣ የሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ ለመፈረም ብቻ የምትገቡ፣ … እግዚአብሔር ልብ ይስጣችሁ፡፡

ማክሰኞ 13 ጃንዋሪ 2015

Ethiopia Zone9: " ህልም አንደሆነ አይታሰርም " ጦማሪ አቤል ዋበላ

Ethiopia Zone9: " ህልም አንደሆነ አይታሰርም " ጦማሪ አቤል ዋበላ: ‹‹ ስሜ አቤል ዋበላ ነው፡፡ አዲሱ አመት ሲጠባ በአዲስ መንፈስ አዲስ ህልም ለአገሬ ማለም የነበረኝንም ማጠናከር እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያችን የብሄር፣ የሃይማኖት፣ የሀብት፣ የትምህርት፣ የፖለቲካ አመለካከት እና ሌሎች...

እሑድ 4 ጃንዋሪ 2015

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: የትልቁ ዋርካ ትልቁ ቅርንጫፍ

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: የትልቁ ዋርካ ትልቁ ቅርንጫፍ:   click here for pdf ታኅሣሥ 19 ቀን 2007 ዓም በቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታወቁት ሊቃውንት መካከል አንዱን አጥተናል፡፡ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየን፡፡ ስለ ሥርዓተ ...

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: እንደ ሰው ወይስ እንደ እንስሳ

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: እንደ ሰው ወይስ እንደ እንስሳ: click here for pdf   The Indian Folktales በተሰኝ ከዛሬ 100 ዓመት በፊት በ1919 እኤአ በታተመ መጽሐፍ ላይ እንዲህ ይላል፡፡ አንድ የሕንድ ጠቢብ ደቀ መዝሙሮቹን ሥራ እንዲሠሩ አዘ...

ረቡዕ 10 ሴፕቴምበር 2014

መልካም አዲስ ዓመት፡

ራስን ሁልጊዜ በአሸናፊነት ዙፋን ላይ …
ይህ ዓለም የዉድድር ዓለም እንደመሆኑ መጠን ይበልጡኑ የሰዉ ልጅ ትልቁን ዉድድር በተሳታፊነት እና በበላይነት ሚናዉን ይወጣል፡፡ ይሁን እንጂ በዉድድሩ ሁሉም በመንፈሰ ጠንካራነትም ሆነ አልሸነፍ ባይነት መንፈስ መሸነፍን አይወድም፡፡ ሁሌም እርሱ አሸናፊ ቢሆን እና በድል ቢያጠናቅቅ ደስ ይለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ዉድድሩ በአንድ ሰዉ የበላይነት ( አንደኝነት ) መጠናቀቁ ግድ ይላል፡፡   ሆኖም ሁሉም ሰዉ በአንደኝነት ሊጨርስ ይቻለዋል፤ ጨርሻለሁ ብሎ ማመንም ማሳመንም ይችላል፡፡ እንዴት?
ሁሉም ሰዉ የሥራ ድርሻ እንዳለዉ የታመነ ነዉ፤ ሁሉም ወደ ዉድድሩ የሚገባዉና የአሸናፊነት አክሊሉን ሊደፋ የሚችለዉ እየሰራ ባለዉና በሚሰራዉ መስክ ነዉ፡፡ ማንም ሰዉ አንተ እየሰራህ ያለዉን ሥራ አንተ በምትሰራዉ መንገድ አይሠራም፣ አልሠራምም፤ ስለዚህ ይህንን ሥራ በምታጠናቅቅበት ሠዓት አሸናፊዉ አንተ ነህና፡፡ ተወዳዳሪህን ባታሸንፈዉ ሥራህን አሸንፈሃልና፡፡የሰዉ ልጅ በአሸናፊነት ዙፋን ላይ ለመቀመጥ ሁል ጊዜ ሥራዉን ማሸነፍ አለበት፡፡ በተገቢዉ ሁኔታ ተጀምሮ እስኪያልቅ ሥራዉን ካወቀ፣ ከሰራ፣ ካጠናቀቀ፣ እሱ ሰዉ ባለድል ነዉ፡፡

ሁላችንም ከፊታችን በሚመጣዉ አዲስ ዓመት ራሳችንን ሁል ጊዜ በአሸናፊነት ዙፋን ላይ ማስቀመጥ የሚችል ልዩ ሞራል ባለቤት እንድንሆን መልካም ምኞቴን ገልፃለሁ፤ መልካም አዲስ ዓመት፡፡

ሰኞ 18 ኦገስት 2014

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነዉ፤"



ደብረ ታቦር ከገሊላ ባህር በምዕራብ ደቡብ በኩል አስር ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ተራራ ሲሆን ከባህር ጠለል በላይ ከፍታዉ 572 ሜትር ነዉ፡፡
ደብረ ታቦር፡-
1.     ባራቅ ሲሳራን ያሸነፈበት ተራራ ነዉ፡፡ መሳፍንት 4፡6-14
2.    ሳኦል እንደ ሳሙኤል ትንቢት ከሶስት ሰዎች ጋር የተነጋገረበት ነዉ፡፡ 1ኛ ሳሙኤል 10፡3
3.    ደብረ ታቦር በዛብሎን ዕጣ ያለ ለጨራራ ልጆች የተሰጠ ቦታ ነዉ፡፡ 1ኛ ዜና መዋዕል 6፡77
4.    ጌታችን ክብረ መለኮቱን የገለጠበት ቦታ ነዉ፡፡ ማቴዎስ 17፡1-8
ጌታ በማንኛዉም ቦታ ክብረ መለኮቱን መግለፁን ትቶ ደብረ ታቦርን ለምን መረጠ?
አንድም ትንቢቱ ይፈፀም ዘንድ
" ሰማያት ያንተ ናቸዉ ምድርም የአንተ ናት አለምንና ሞላዋን አንተ መሰረትክ ሰሜንና ደቡብን አንተ ፈጠርክ ታቦርና አርሞን በስምህ ደስ ይላቸዋል፡፡" መዝሙር 88፡11-12 የተባለዉ ይፈፀም ዘንድ ነዉ፡፡ ከሌሎች ተራሮች ሁሉ ደብረ ታቦርን የመረጠዉ ሌላዉም ተራራ ከመሬት እንዲርቅ የመለኮትም ምሥጢር ከሰዉ የራቀ የጠለቀ መሆኑን ለማጠየቅ ነዉ፡፡
ሌላዉ፡-

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...