ማክሰኞ 16 ኦክቶበር 2012

የጉዞ ማስታወሻ


     የጉዞ ማስታወሻ

እንደባቡር ፋርጎ ሳይነጣጠሉ እደተቀጣጠሉ መጓዝ ግድ ይላል ትልቁ ትንሹን ትንሹ ትልቁን በስተጀርባው እያስከተለ መጓዝ ግድ ይላል የቸኮለከሰንሰለተማው የጎዞ ውህደት ውስጥ ይነጠላል ደርቦ ማለፍ ለማለፍ መንሰፍሰፍ መሽሎኪያ ቀዳዳ መፈለግ የሾፌሮች ስራ ነው ተሳፋሪመጣደፉ መሳቀቅ መፀለይ የየሰዓቱ ሥራቸው ነው 12፡30 ከአ.አ መነሐሪያ የወጣው 2ኛ ደጃ አውቶብስ 2፡10 ደብረ ዘይት መንገድደረሰን መንጋቱን ማመለከቻውና የቁርስ ሰዓት ብስራቱን ለማሰማት ሁለት የመኪናው ረዳቶች ከፊት ከኋላ ፌስታለቸውን ማንኮሻኮሽ ጀመሩአፍታም ሳይቆይ አንባሻዎችን ለተሳፋሪ ማደል ጀመሩ፡፡ ቁርስ መሆኑ ነው ቁርሱን ምሳውና እና እራቱን የሰነቀው መኪና በአሽከርካሪው አማካይነት አስፋልቱን ለሁለት እየሰነጠቀ ይፈተለካል ወደ ሐረር የመቻቻልና የትብብር ከተማ፡፡
     የደብረ ዘይት (ቢሾፍቱን) እንደ ወጡ ትላልቅ ድንኳን የመሰሉ ቤቶችን ማየት ሲጀምሩ የኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆንዎን መዘንጋት የለብዎትም በአንጻሩም ያቆጠቆጡ ሰብሎችና ጥቋቁር መሬቶች የአይንዎ ማረፊያ ናቸው ጆሮዎትን ጣል ካደረጉ ፌስታል የሚል ሰው ድምጽ ይሰማሉ ሊያባላሹም ይችላሉና፡፡ ሽንቱ የመጣበት ሰው እንዲሁ ለረዳቱ ያሳውቃል ረዳቱ ለሹፌር መኪና ይቆማል ተንፍሰው ይመለሳሉ አንዳንድ ቤቱ የደረሰ ይመስለውና ወደ መኪናው በቶሎ ባለመመለስ ጉዞውን ያዘገያል የተለመነው የመኪና ረዳት እባካችሁ ግቡ በማለት ተሳፋሪውን ያስገባል፡፡ ግራ ቀኙን እየቃኙ ተፈጥሮን እያደነቁ ይሄዳሉ 2፡35 ሞጆ ከእንቅልፍ ነቅታ ተግታ ህዝቧን ለሥራ እያሰማራች ነው እኛም ወደ ጉዞአችን ሞጆ ሜዳ ላይ ደረቱን ያሰጣው ደረቅ ወደብና ተርሚናል መንጋቱ ስለሆነ ፀጥረጭ ብሏል፡፡
     በየመንገዱ ግራ ቀኝ ቅጠሎቻው ረግፈው ቅርንጫፎቻቸው የቀሩ የግራር ዛፎች የክረምቱን የምስራች ድምጽ ሰምተው ማቆጥቆጥ አንገታቸውን ቀና ማድረግ ጀምረዋል፡፡
     ከንፋስ የኤሌክትሪክ ኃይልን የሚሰጡ ተርባይን ሲመለከቱ የአዳማ መዳረሻ ምልክት እንጂ ሌላ ስራ ያለው አይመስልም እንደየዋህ ፀባዩን አሳምሮ ቆሞ ሲመለከቱት እርሱን እየተመለከቱ ሲጓዙ ኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅን ያገኙታል፡፡
     የአዳማ ውበት አባ ገዳ ህንጻ አ.አ ሳትነቃ አመልጣችው የመጣችው ተጓዦች እንኳን ደህና መጣችሁ ይህ ሥፍራ የስምጥ ሸለቆዋ እንቁ የአዳማ ከተማ ነው ይላችኋል፡፡ አሁን ከነጋ 3፡00 ሠዓት ሆኗል፡፡
     ይቺን ሞቃታማ ከተማ የኦሮሚያ ክልል ንግሥት እንደ ዋዛ የክረምት ጎም እንዳጠላበት እንደከረፈች ፈገግታዋን ሳናይ ጥለናት እብስ አልን እኛም ቅር ብሎን እርሷም ከአቅሜ በላይ ነው ጊዜው ክረምት ነው እያለች ህፃን ልጅ ከእናቱ እንዲነጠል ተነጣጠልን፡፡ ጊዜው እርሷ ዝናብን እያነባች እኛም እያዘንን እርስ በርስ ተያይዞ የቆመውን ተራራማ ምድር እየሰነጠቅን በመጓዝ ወለንጭቲን ያለፍነው ጠዋት 3፡30 ሰዓት ላይ ነበር፡፡ አሁንም ቢሆን ደፍሮ እንደሰንሰለት የተያያዙትን ተራሮች ሊለያያቸው የሚችል የለም፡፡ ለእድሜ ዘመናቸው ላይለያዩ በምድር ተማምለው ፍቅር መስርተዋልና አሁንም አብረው ናቸው፡፡ ወደ ፊትም አይለያዩም የፈጠራቸው ደግሞ እሰኪመጣ በዚህ መድር ላይ ዘር ሊዘራ ሲወጣ የግራር ዛፍ ብቻ የዘራ ይመስላል በተንጣለለው አስፋልት ግራና ቀኝ ተበትነው ሲመለከታቸው ከአብ ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ አንጥረኛው የቱ ነው እስኪሉ የኢትዮጵያ መልክዐ ምድር ማድነቅ የተለመደ ቢሆንም እኛም የአዋሽ አዋሳኝ የሆኑትን ሰንሰለታማ ኮረብቶች አሰፋፈር እያደነቅን ድፍን 4፡00 ሰዓት ሆኗል፡፡
     ግራና ቀኛችንን አልፎ አልፎ እንደ ግራር ዛፍ አጃበውን የሚጓጓዙት የከፍተኛ ኃይል የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ማማዎችን ለምስራቅ የአገራችን ክፍል ብርሃን ላመዳፈም እየገሰገሱ ይመስላሉ፡፡
     አልፎ አልፎ ጣል ጣል ብለው የሚያገኛቸው ጎጆ ቤቶች እንኳንስ የእህል ማጠራቀሚያ ጎተራ ሥንቅ መቋጠሪያ አገልግሎት ከቤት ያላቸው አይመስሉም፡፡ በየቦታው ስፍራው በረሃውን ከማድመቅ ውጭ ከአዋሽ ሃይቅ ደረቱን ስትሮ ሲመለከቱት ለጥፋት እንጂ ለልማት አለመሆኑን ሲያዩ እጅግ ያዝናሉ ዛሬም ዓባይን በደፈርንበት ዘመን አልደፈር እጄን አልሰጥ ብሎ ይልቅስ ነዋሪውን ዕንባ እያራጨ ከማፈርቀል ባሻገር አዋጅ ማን ያውቃል አንድ ቀን እንደ ባንኩ የበረሃው የልምላሜ የብልጽግና ፈር ቀያሽ ይሆንና ታሪክ ይቀየር ነገር ይገለበጥና የተሰደደው የተፈናቀለው ሁሉ መልሶ ሰፋሪ ይሆናል፡፡ ማን ያውቃል? ማንም
     አውራ ጎዳናዎቹ መኪናዎቹ ሰው ብቻ አይደለም ወደ ማቅረብም አ.አ መኪናውም መኪና ጭኖ መኪና ነዳጅ ጭኖ ላይ ታች ሲል ይታዘባሉ የአ.አ ጎዳናዎች የመኪና ማቆሚያ ሥፍራዎች በመኪና ተጨናንቀው የገባው ሥፍራ ሳያገኝ ዛሬም መኪና ተጭኖ ይሄዱለታል፡፡ የሚገርመው ግን ያ ሁሉ መኪና አ.አበባን አጨናንቆ የዚያኑ ያህል በትራንስፖርት እጥረት መሰቃየቱን ሥናይ ግራ ያጋባል፡፡ ሲባል እንደሰማሁት ጁቡቲያውያን ወደ ኢትዮጵያ የሚገባውን የመኪና ብዛት ተመልክተው በመገረም ኢትዮጵያውያን ምግብ መብላት ትተው መኪና መብላት ጀምረዋል ወይ? አሉ የተባለውን በድጋሚ ይህ መንገድ እንደገና አስታወሰኝ፡፡
     አሁንም አዋሽን በስተቀኝ እያየን እንጓዛለን 4፡20 ሠዓት ሆኗል፡፡ በስተግራ የሰንሰለታማዋን ተራራ አብይ ቅርንጫፍ እየታከክን በአዋሽ ምድር ላይ ከኤሌክትሪክ ምሶሶ በስተቀር ለመሃላም ቢሆን ሌላ ዛፍ አይመለከቱም የአዋሽን ሙቀትና ከተማ ‹‹እንግዲህ ቻው ቻው›› በማለት ጥቂት ደቂቃዎች ይቀሩታል፡፡
     የአዋሽን ሐይቅ እየታከለ የሚሄደው አውራ ጎዳና በመሰራት ላይ ስለሆነ ተለዋጩን መንገድ መጠቀም የሰውነት እንቅስቃሴ ማድረግ የግድ ነው፡፡ ምንም ክረምት ቢሆን ቦታው አዋሽ ነውና የሰውነት ሙቀትም መጨመር ግዜ ይለዋል፡-
     አሁን አዋሽን በሩቅ ማየት የለም አዋሽ በርሶ ግራ እና ቀኝ እርሶ ደግሞ አዋሽን ለሁለት ከፍሎ መጓዝ (ሰንጥቆ) መጓዝ ግድ ይላል፡፡ አዋሽን ለሁለት ተባብረው የሰነጠቁትን የመኪና መንገድና የድሮ የባቡር ሐዲድ(የግመል ሃዲድ) ከሐይቁ ጋር ውሃ ልካቸውን ሲመለከቱ ዕፁብ ድንቅ እያሉ ሐይቁን ግድብ ያስገዛ ፈጣሪ እያመሰገነ መተሐራ ከመግባት በስተቀር አማራጭ የሉትም፤ሀይቁ ቢያገሳ፣ አሻፈረኝ እምቢኝ ቢል በአንበሳው ሐይቅ ከመዋጥ የዘለለ ዕጣ ፈንታ የሉትምና፡፡ መተሐራ 4፡40 ሠዓት አዲሱ ነገር የመተሐራ ትራፊኮች መግቢያና መውጫ ላይ ሁለት ጊዜ ያስቆማሉ አለመቀናጀታቸው ሲያሻቸው የበረሃ አበል ይቀበላሉ ተብለው ይታማሉ፡፡ ትርፍ ቢኖረው ባይኖረውም ቢሳሳቱም ባይሳሳቱም ተሳፋሪው መኪናው ቆሞ ትራፊክ ሲገባ ሆዳም፣ ከርሳም፣ የሚሉ ድምጾች ይሰማሉ እኛም እንሰማለን ትራፊኩም ይሰማል፡፡
     መተሐራ ካለፉ ሰንሰለታማው ተራራ እየተበጣጠሰ በስተቀኝ ያለው እየራቀ ሥፍራውን ለተንጣለለ ሜዳ ይለቃል፡፡ ቁጥቋጦውና ግራሩ ግን የት ድረስ እንደሚሄድ አይታወቅም ይከተሎታል፡፡ ከ12ቱ ሐዋርያት ቅ/ዮሐንስ ብቻ እስከ መስቀሉ እንደ ዘለቀ ከመሐል አገር የተነሱት ዕፅዋቶች ከግራር በስተቅ በመንገድ የሚከተልዎት የለም ከከተማ ሲወጡ ይክድዋታል፡፡ ግራር ሆይ ብፅዕ ነህ ባህር ዛፍ ከከተማ ስርቅ ትከዳኛለህ፡፡
     6፡10 ሠዓት አዋሽ 7ኪሎ 3ኛው ትራፊክ 20 (ሃያ ብር) ተቀበለ፡፡ አዋሽ 7ኪሎ ሙቀቷ ከመጨመር በቀር ልማት አይታይበትም እንዲያውም በድንጋይ ካብ የታጠሩ ባዶ ስፍራዎች ይበዙበታል፡፡ ለመሃላ ከተማዋን ወጣ ብሎ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋን የመሰለ ነገር የአይን ማረፊያ አለ፡፡
     ከጁቡቲ አዲስ አበባ የሚያስመጣው የባቡር ሃዲድ  ፍተሻውን ሳይደርስ ከምድር ከፍ ያለው ድልድይ ዛሬ የጦጣ መሸጋገሪያ ኖኗል፡፡ አዋሽ አርባን እያለፉ ሲጓዙ ከተማን የሚያስታውስዎት ሁሉት ህንጻዎች ከመንገድ በስተቀኝ ቆመው ያገኛሉ፡፡
     አስቀድመው መተሐራ ላይ የከዱትና የተለዩን ስንሰለታማ ተራራዎች በስተቀኙን እንደተማረከ የጠላት ወታደር እጃቸውን ወደ ላይ ይዘረጋሉ ምህረት ጥያቃ እንከተላችሁ፣ አብረን እንሂድ በማለት። በስተ ግራ ግን ለጥ ያለው ሜዳ ላይ ከበረሃው ባቡር (ከግመል) በስተቀር ሰንሰለተማው ተራራ ላይታይ ምሏል መሰል የለም፡፡ ጊዜ ታክሲ አይደለም ቆም አይጠብቅም 5፡25 ሠዓት ለመሐላ በረሃ ውስጥ ያገኘናቸው ምሶሶዎች የበረሃውን ግለት አልቻሉም መሰል በየቦታው ወድቀዋል በቦታቸው የአርማታ ምሶሶ ቆሟል ከወደቀበት ቀና ሳያደርገው፡፡
     ቦርዳዴን ወደ ቀኝ በመተው 5፡35 ሰዓት መሆኑን ስናውቅ ወደ አሰበ ተፈሪ አመራን፡፡ 316 ኪ.ሜ መጓዝ ግድ ይላል ከተራራ ግርጌ የምትገኘዋን አሰበ ተፈሪ ለማግኘት ምሳ ሠዓት ደመቅ ሸብረቅ ሽርጉድ ትላለች እንግዶቿን ለማስተናገድ ‹‹ጥሩነሽ ምግብ ቤት›› አንዱ ነው፡፡ ‹‹እንኳን ደህና መጣችሁ›› ብለው ይቀበላችኋል ምሳዎትን ይበላሉ፡ ቡና በጀበና እዚያው ይጠጣሉ፡ አዲስ አበባ ላይ ጉሊት ሽንኩርት፣ ጎመን፣ በቆሎ ሲሸጥ እዚያው ሆቴሎች በር ላይ ጫት እንደ ጎመን ይሸጣል፡፡ ፡ምሳ ሰዓት ተጠናቀቀ፡ አሰበ ተፈሪ ደህና ሰንብች 7፡20 ሠዓት አሰበን ሻገር ካሉ ለምለሚቷን ምስራቃዊ ክፍል እየጎበኙ ሞቀታማውን በተመጣጠነ አየር ያጣጥሙታል፡፡
     ኦሮሚያ ክልል ቱሉ አረዳ ላይ ሌላ ትራፊክ 4ኛ 20 ብር ወጪ ተደርጓል ኬላ መሻገሪያ፡፡ ደበሶ 8፡00 ሠዓት ።የትራፊኮችን ጉዳይ መንግስትም ህብረተሰብም አንድ ሊላቸዉ ይገባል፡ህዝብን ሊያገለግሉ እንጂ ሊበዘብዙ አይደለምና አደራ የተጣለባቸዉ። ለመሆኑ 300 እና 400 ኪ.ሜ. ከአዲስ አበባ ሳንርቅ እንዴት እንዲህ አይነት ተግባር ሲፈፀም መንግስት ዝም ይላል? ደሞዝ አይከፈላቸዉ ይሆን?
     …ሜዳው ጨርሰን ዳገት ወተን ወደ ሂረና ለመግባት ደግሞ ቁልቁለት መውረድ ግድ ይላል፡፡ (ጠሎ ወረዳ) ከአሰበ ተፈሪ ወጥተን የሐረማያ ዮኒቨርስቲን እንዳለፉ ከአራት ሠዓታት በላይ የሚፈጀውን ዳገታማ ስፍራ ዓይንዎትን እስኪደክምዎት ግራ ቀኙን መቃኘት ነፍስ ይማርካል መቸስ የዚህ መንገድ ልምላሜ ዋነኛው ምሥጢር አልፎ አልፎ የሚታየው የበቆሎ ተክልና ከጫት ተክል ያለፈ አይደለም፡፡
     ሂረና ፣ ገለምሶ፣ ካራሚሌ፣ ቆቦ፣ ሜታወረዳን እንዳጠናቀቅን ቁልቢ 10፡25 ሠዓት ደረስን ሙስሊሙም ክርስቲያኑም ቁልቢ ከተማ አፋፍ ላይ የሚገኝን ተአምረኛውን የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መኪናው ከፍና ዝቅታ ያሳልመዋል ከሩቅ ያለ የሚመስለው ቤተክርስቲያን እንደ እኔ ለቦታው እንግዳ ከሆኑ ገና ለገና እደርስበታለሁ ሲሉ ተራራውን በስተግራ እየታከኩ ያልፉት ጳንገጐ ይገባሉ፡፡

     ከቁልቢ (ቁልቢ በኦሮምኛ ሽንኩርት ማለት ነው) የአንድ ሰዓት መንገድ ከተጓዙ በኋላ የበረሃዋን ንግስት ድሬን በስተግራ በመተው ለሃያ ደቂቃ ከተጓዙ በኋላ የሐሮማያ ዩኒቨርስቲ ዋና ካምፓስ መቀመጫ የሆነውን አለማያን ያገኟታል ጉዞአችን በህዝብ ትራንስፖርት እንደመሆኑ መጠንና ወቅቱም ሐምሌ ስለነበር የሐሮማያ የሐረር የጅጅጋ ዮኒቨርስቲ ተማሪዎች ነበሩ የተጓዡች ቁጥርን አብላጫ የያዘውና አለማያ ላይ ለ30 ደቂቃ ያህል ቆመናል የጫኑትን ሻንጣዎች ቁሳቁሶች እስኪያወርዱ፡፡
     ከአሥር እና አስራ አምስት ደቂቃ ጉዞ በኋላ ምስራቅ ውስጥ በትክክል መድረስዎትን የምታበስራዋ አንዳንዴም የአረቡ ክፍለ ዓለም ውስጥ ነው ወይስ ቻይና ነው ያለሁት ብለው እስኪጠረጠሩ ድረስ ሰዎች በሥራ ላይ የሚያዩበትን ከተማ አወዳይን ያገኛሉ፡ ጊዜው ባይመሽና 12፡00 ሠዓት ባይሆን (ይቅርታ አወዳይ ላይ ጀንበር አትጠልቅም፡ ድካም ዝር አይልም፡ የሚዘጉ በሮች የሉም፡ ሁሉም ቀን ከሌሊት ለሥራ ይፋጠናል፡ አረንጓዴ ወርቃቸውን ወደተለያየ አቅጣጫ ለመላክ ይፋጠናሉ እንጂ፣) ጎራ ብዬ ባያት ቁጭ ብዬ ብታደማት ደስ ባለኝ ነበር እኔም ጎራ ሳልልባት እናንተንም ሳላስቃኝ ማለፌ እኔንም ቅር አሰኝቶኛል፡፡
12፡20 ሐረር የአምስት በሮች እመቤት ምሥራቃዊና ጥንታዊት ከተማ የብሔር ብሔረሰቦች መገኛ ሐረር፤
ሐረር ሲገቡ በየትኛውም አቅጣጫ ሲመጡ አምስቱም በሮች እንኳን ደህና መጡ እያሉ አቀባበል ያደርጉልዎታል፡፡ ሸዋ በር፣ ፈላና በር፣ ዱክ በር፣ኤረር በርና ሰንጋ በር ምሽት ላይ ቀዝቃዛ የምትለዋ የሐረር ከተማ ምንም አስቸጋሪ ነገር አይታይባትም ወደፈለጉት ለመጓዝ በጃጆች ሁሌ ንቁ ሁሌም ዝግጁዎች ናቸው፡፡ ታክሲዎችም እንዲሁ የምሥራቁ እመቤት ሐረር ሙስሊሙም ክርስቲያኑም በጋራ የሚኖሩበት ፍቅር የሆነች ከተማ ብትሆንም ጊዜ ያመጣውን ጊዜ እስኪፈታው እምነትን ሰበብ እያደረጉ የሚመጡ በሽታዎቸ (ግማቶች) አይታጡም በቤተክርስቲያን ላይ ድንጋይ መወርወር፣ አማራው ላይ መዛት፣ ጊሌ ይዞ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት፣ ፓሊስ ሳይቀር ከእምነት የፀዳ ተቋማዊ ግዴታን አለመወጣትና ለእምነት እያደሉ ፀጥታን ያለማስከበር መጠነኛ ድክመቶች አሉባልታ ይሁን እንጂ የሐረርን ፀጥታ ለማስከበረ መንግስት አይተኛም አያንቀላፋም ፈጣን እርምጃ ከድሬደዋ በሚመጡ ፌዴራል ፖሊስ ሁከታውን ብጥብጡን ዛቻና ማስፈራራቱን ድንጋይ ውርወራውን ፀጥ ረጭ ያደርገዋል፡፤

     አዲስ አበባ ሆነው በመገናኛ ብዙሐን ሐረር ሲነሳ ለማዳ ጅቦች፣ የጃጎል ግንብ፣ አምስቱ የሀረር በሮች፣ የሐረር ሰንጋ…..ወዘተ የሚዘነጉና የማይጎበኙ አይደሉም። ፈጣሪ ዕድሉን ከሰጠን ጊዜው ካደረሰን አብረን እንጎበኘዋለን፡፡ ሐረር ልትተኛ ነው እኔም ድካም ተጫጭኖኛል ሰላም እደሩ ሐረር ሥትነቃ እኔም በርትቼ ስነሳ አብረን የሐረርን ጓዳ ጎድጓዳ እንቃኛለን ሐምሌ 12 ቀን 2004 ዓ.ም ፡፡
     ንጋት ሐምሌ 13 ቀን 2004 ዓ.ም የሐረር ሌሊት ለንጋት ቦታውን በመልቀቅ 12፡30 ሰዓት ሆኗል፡፡ አየሩ መጠነኛ ቅዝቃሴ ይታይበታል፡፡ አገር ለማየት ቆርጦ የመጣ ብርድ ሙቀት ዝናብ ንፋስ ብሎ መተኛት አይጠበቅበትምና በጠዋት ተነስቻለሁ ጉዞ ከሸንኮር በእግር ወደ ሐረር እምበርርት በሐረር በር አድርገን ወደ ጨለንቆ አደባባይ፤ ከጨለንቆ አደባባይ ወደ ተለያየ አቅጣጫ መጓዝ ይቻላል አንደኛ መንገድ (ወደኤራር በር)፣ ወደ ሐረር በር፣ ወደ ሸዋ በር፣ ወደ ጀጎል በር፡ሰንጋ በር(ጅቦች ወደሚታዮበት) እዛው ጨለንቆ አደባባይ ላይ አሚር አብዱላሂ አዳራሽ (የቀድሞው የራስ መኮንን አዳራሽ) ይገኛል:: ለሁሉም ጊዜ አለውና ታሪክ በታሪክ ተደምስሷል በአንደኛ መንገድ ሲጓዙ እንዲሁ የታሪክ ሹም ሽረት ጥንት ጁግለን ይባል የነበረው ጁገል ሆስፒታል በመባል ተቀይሮ ያገኙታል ሙዝየሞች የባህልና ቱሪዝም ቢሮዎች የሐረሪ ብሔረሰብ ባህላዊ ሙዝየም ሁለት መስጅዶች… ያገኛሉ፡፡ እዚሁ ወደ ጨለንቆ አዳባባይ መግቢያ ላይ ሁላችን በተለያዩ መገናኛ ሚዲያ የምናየው የሐረር በር አንድ ነገር ያመላክተናል፡፡ ‹‹ሐረር የሰላም የመቻቻልና የትብብር ከተማ›› ሐረር ጃጎል የዓለም ቅርስና የመጨረሻው የሐረር ንጉስ ፎቶ ግራፍ የአሚር አብዱላሂ ይታያል፡፡ 

   በአካባቢው ሲንቀሳቀሱ ይህቺ በ72 ነገስታት ሥትመራ ወይም ስትገዛ የኖረች ጥንታዊት ሀገር ባላት የውስጥ ለውስጥ ሽኩቻ እውን የመቻቻል አገር ናት? ብለው ጥያቄ ሊያነሱ ግድ ይልዎታል፡፡ የዛሬን አያርግና የፍቅር፡ የመቻቻል ከተማ ነበረች ነገም ተስፋ አለን ጠንካራ ህዝብ ነዉና ህዝቡ ታሪኩን ቀይሮ እንደገና ያመጣዋል።እንግዳ ኖትና አቦ ይመችዎት ወቅቱ ስለሆነ ዛሬ በሚዛን ቢሸጥም ድካሙን ያስረሳልና ማንጎ ይብሉ ተጋብዘዋል፡፡
ድሬ የምሥራቅ የበረሃዋ ንግስት የምትገኘው በ90 28.1 እና 90 49.1 በስተሰሜን ላቲቲውድ በ410 38.1 በስተምስራቅ እና በ420 19.1 ምስራቅ ሎንጊትውድ መካከል ሲሆን 505 ኪ.ሜ ከአ.አ ርቀት ላይ የምትገኝና በ1288 ኪ.ሜ ካሬ ላይ የሠፈረች፡ ደረቅና ሞቃታማ ስትሆን በ31.40Cከፍተኛ እና በ18.20C ዝቅተኛ መካከል ትገኛለች ዓመታዊ የዝናብ መጠኗ 604 ሚሊ.ሜትር እንደሆነ ይነገራል፡፡ ከባህር ጠለል በላይ ከ960-2500 ሜትር መካከል ያለች ውብ ከተማ ናት። ህዝቦቿ ተግባቢና የሥራ ፍቅር ያላቸው እንግዳ ለመቀበል የማይሰለቻቸውና በብዙ ብሔር ብሔረሰብ ስብጥርና ዕምነት ደምቃ ያለች በብዛት የውጭ ዜግነት ያላቸው ሰፈርውባት ያለች ከተማ ናት፡፡
 አስራ ስምንት ኪሎ ሜትር ወደ ታች ቁልቁል መውረድ ይጠበቅብዎታል ድሬ ከባህር ጠለል 960-2500 ሜትር የምትገኝ ሲሆን በኢትዮጵያው ውስጥ በፌዴራል ከሚመሩ ሁሉት ከተሞች ከአ.አበባ በመቀጠል የምትገኝ ሞቃታማ፣ደማቅ፣ ግርግር ቀን ከሌሊት የማይለያት፣ ሃያ አራት ሰዓት በስራ ላይ የተጠመደች፡ የተለያዩ የብሔር ብሔረሰቦች መኖሪያ፣ የእንዱስትሪ መገኛ፡ የሸቀጣ ሸቀጥ መደብር፣ የዕውቀት ምንጭ፣ የቆንጆዎች ምድር፣ መቃሚያ ቦታ፣ መጨፈሪያ መድረክ፡ መገበያያ መደብር …..በቃ ድሬን ቃላት አይገልጻትም፣ ዓይን አይቶ አይጠግባትም፣ ቢኖሩባት ቢኖሩባት አትሰለችም ሲገቡ ተንደርድረው ደስ እያለዎት ወደ ከተማዋ ይገባሉ መውጣት ምጥ ነው፣ እጅግ ይጨንቃል፡፡ ድሬ መጥተው የት አርፋለሁ ብለው አይጨነቁም እርሶ ተዘጋጅተው ይምጡ እንጂ የፀዱ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎቻቸው በራቸውን ከፍተው “እንኳን ደህና መጡ” ብለው ይቀበልዎታል፡፡ በአንዱ ሆቴል የእረፍት ጊዜውን አድርገው ገላዎትን ከተለቃለቁ በኋላ ወጣ ይበሉ የትራንስፖርት ችግር የለም አያስቡ ባጃጅ ሞልቷል ሁለት ብር ከፍለው መንሸራሸር ነው አሥር ብርማ ከከፈሉ የሚፈልጉት ቦታ ይደርሳሉ፤ ብቻ እርሶ የት መሄድ እንደሚፈልጉ፣ ምን ማየት እንደናፈቁ ዝግጁ ይሁኑ እንጂ ለዛሬ ብቻ መሄድ እንጂ ወደየት መሄድ እንዳለቦት ግራ ከገባዎት መንገድዎን ለባጃጅ ሹፌር ይስጡ እርሱ ያስጎበኝዎታል፡፡
     ደቻቱ ሠፈር፣ መጋላ ሠፈር፣ ኮኔል ድልድይ፣ ከዚራ፣ ሳብያን፣ ነምበርዋን፣ ታይዋ፣ ፖሊስ ሜዳ፣ ለገሃሬ፣  አሸዋ፣ ወዘተ… የሚጎበኙ ናቸው፡፡

.ጐልማሳ ተረታ በጐረምሣ




31 ዓመት ፣ ሁለት መንግሥት፣ ብዙ ምኞት፣ ብዙ ጥረት ብዙ ሙከራ፣ ብዙ ሽንፈት…..ሶስት ዓሥርት ዓመታትን የዳፈነው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለራሱም የናፈቀውን ድል ለኢትዮጵያ ህዝብም ያለውን የእግር ኳስ ፍቅርና ድል ከትውልድ ወደ ትውልድ ከመንግሥት ወደ መንግሥት ሲቀያየር የነበረውን ጉጉቱን ጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. በአዲስ አበባ  እስታዲየም ከቀኑ ዓሥር ሰዓት ጀምሮ  ከሱዳን  አቻው  ጋር  ያደረገውን ትንቅንቅ በ2ለ0 90 ደቂቃውን ሲያጠናቅቅ በየቤቱና በየቦታው ድምፁን አጥፍቶ  በድጋፍና በጉጉት ሲከታተል የነበረውን የኢትዮጵያ ህዝብ ከዳር ዳር እንዲነቃነቅ አድርጐታል፡፡  ዋልያዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቶች ለኢትዮጵያ ህዝብ፣ ለአገር  ክብር፣ ለትውልድ ታሪካዊ የሆነውን ድል ለማስመዝገብ የቻሉት ከተለያየ ቡድን ተውጣጥተው በአንድ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሠልጥነው አሥራ አንድ በመሆን ተጫውተው በኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፍ በጨዋታና በግብ ብልጫ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ዋንጫ በደቡብ አፍሪካ እንድትሳተፍ አብቅተዋታል፡፡
     ብሔራዊ ቡድኑ ጐል አስገብቶ ማሸነፍ አሸናፊነትን ማሥቆጠር ብቻ  አልነበረም የሠራው:ለ31 ዓመታት የተዳፈነውን የተናፈቀውን ለአፍሪካ ዋንጫ መሳተፍ፣አንገት ደፍተንበት ተስፋ ቆርጠንበት የነበረውን የእግር ኳስ ነገር በቃ አከተመለት የተባለውን ዋልያዎቹ አባቶቻችን የፈፀሙትን በታሪክ የሠማነውን መላው ኢትዩጵያዊ የናፈቀውን እኛም ናፍቆናልና ለድል ደርሰናልና አይዞሽ አንገትሽን ደፍተሽ ካቀረቀርሽበት ቀና እናደርግሻለን፣ የጓጓሽውን እናሳይሻለን በማለት ቃል ገብተው ቃላቸውን ጠብቀው  ቃላቸውን ፈፅመው አኰሯት ህዝቧን አስደሰቱት፡፡
     በግማሽ 45 ደቂቃ ያልታየው ተስፋ የደበዘዘው ድባብ ዳግም አንገታችንን የሚያስደፋ አስመስሎት ነበር የአዳነ ግርማ ሙከራውን ለጐል አለማብቃትም ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍለንም ነበር፣ ነገር ግን ያ ከዋልያዎቹ ሲጠበቅ የነበረው የሁለት ግብ አብላጫ ድል የማታ ማታ እውን ሆኖ ወንዱን ከሴት፣ወጣቱን ከአዛውንቱ ከምሽቱ አሥራ ሁለት ሠዓት ጀምሮ ከእስታዲዮም አንሥቶ በቴሌቭዠንና በሬድዮ ሲከታተል የነበረውን ሁሉ አስፈንጥዞታል፡፡
     የአገር ኩራት የሆኑትን ዋልያዎች ለመደገፍ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ብቻ ሣይሆን ከመላ አገሪቱ  የመጡ ወጣቶችና አዛውንቶች ነበሩ፣ በዋዜማው ከምሽቱ 5 እና 6 ሰዓት ጀምሮ የእስታድየም መግቢያ ትኬት ለመግዛት ተራ ሲጠብቁ ያደሩ ጥቂት አልነበሩም፡፡  ከሃያ ሁለት ሺ የማይበልጡ ተመልካቶችን የመያዝ አቅም ያለው የአዲስ አበባ እስታድየም እስከ 30 ሺ  የሚጠጉ ተመልካቶችን ተጨናንቆ  በመያዝ  ሲያስተናግድ ከዚያ በላይ ብዙ ጊዜ እጥፍ በጉይዋ የያዘችው አዲስ አበባ ዳግም በቴሌቭዠን መስኮት ለዘጠና(101) ደቂቃ ስታስኮመኩም ነበረች፡፡  አመሻሽ ላይ ግን በውስጥም በውጭም የነበረውን ህዝብ ጮቤ አስረገጡት ዋልያዎቹ፡፡
     ዋልያዎቹ አገርን ወክለው ሲጫወቱ ሌላ ጊዜ በዚሁ አዲስ አበባ  እስታድየም እንደጠላት እየተያዩ የሚፋለሙ  የተለያየ ቡድን ተጫዋቾች ዛሬ ግን የጋራ  አገራቸውን ጉዳይ በአንድነት በመሆን ጉዳየቸው በማድረግ አንዱ ከሌላ ቦታ መጥቶ አጥቂ ፤ ሌላው ተከላካይ ፤ሌላኛው ወገን አማካይ ከአንደኛው ቡድን የመጣው ዳግም በረኛ የቀረው ደግሞ ተጠባባቂ በመሆን አገርን ለድል ህዝብን ለደስታና ለኩራት በአንድነት አደባባይ ወጥተው እንዲዘምሩና እንዲጨፍሩ አድርገዋል አንድ ሆነው ለአገር በመስራትና ውጤትን በማምጣት እምዬ ኢትዮጵያ አንገቷን ያስደፋት ለዘመናት የናፍቋት ህዝቦችን በሰቀቀን በጉጉት እንዲያልቁ ያደረጋቸው ከዛሬ ነገ ታሪክ ይቀየራል እያለ ዓመታት በተቀየረ ቁጥር የሚያስናፍቃቸው ብዙ አገር አለ ከጫፍ ጫፍ አንድ ሆነን ልንወጣበትና ድል ልናደርገው የሚገባ ጥንተ ጠላታችን ድህነት፣ ጦርነት፣ እርስበርስ መጠላላትና መከፋፋል፣ በሽታ…. እነዚህ ሁሉ እንደ እግር ኳስ ድል በአገራችን በኢትዮጵያ  ከተናፈቁ ዘመናት ተቆጥረዋል መገላጫዋ  በረሃብ ህዝቦቿ የሚረግፋ በእርስበርስ ጦርነት የምትታመስ በሽታ የሚያጠቃት፣ በመከፋፍል ያለቁ…… የሚለው መለያችን ከሆነ ሰነበቱ፡፡ ይህን ዘመናት ያስቆጠረ ታሪክ ለመቀየር፣ የናፈቀንን አንድነት ለማምጣት፣ ስማችንን ለማደስ አንገታችንን ቀና አድረገን ደርታችንን ነፍተን በዓለም አደባበይ ለመታየትና ለመናገር፣ እኛ ኢትዮጵያውያን  ነን ርሃብ ጦርነት በሽታ የትናንት ታሪካችን እንጂ የዛሬ ማንነታችን አይደለም ዛሬ እኛ ኩሩ ህዝብ ነን፣ ትናንት ተከፋፍለን እርስበርስ ብንዋጋም ዛሬ ግን እጅ ለእጅ ተያይዘን በፍቅራችን ለዓለም ምሳሌ መሆን የምንችል ነን፣ ትናንት የዓለም ቁንጮ እንዳልነበርን ዛሬ የዓለም  ጭራ ብንሆንም ነገ ግን ታሪካችን ተቀይሮ ሁላችንን ለልማት ጠንክረን በመነሳታችን የትናንቱ ቦታችን የዓለም ቁንጮነትን እንይዛለን በድህነታችን ብዙዎች ጣታቸውን እንዳልቀሰሩብን ነገ ግን ለዓለም የምንደርስና ተምሳሌት የምትሆን  ኢትዮጵያን እንፈጥራታለን ለማለት ኢትዮጵያዉያን በልባችን የሞላውን ልዩነትና ክፋት በማስወገድ ለአንድ አገራችን/ኢትዮጵያ/ዓላማ ስንል ሁሉን ወደ ጐን በመተው እንደ ኢትዮጵያ  እግር ኳስ ብሔራዊ  ቡድን ተግትን ቀሪውን አርባ አምስት ደቂቃ  ልንጫወት  ግድ ይላል ያለፈው 45 ደቂቃ አርኪ ተስፋሰጪ  አልነበረም ንጉሱ በደርግ ደርግ  በኢህአዴግ ኢህአዴግ ደግሞ በእርስበርስ መተካካት ጊዜው ባክኗል እንደ አዳነ ግርማ ሙከራን ለጐል አለማብቃተና መሳሳት ብዙ ዋጋ ሲያስከፍል እነደነበረ በደርግ ጊዜ በጦርነት በምርጫ 1997 ዓ.ም. በወጣቱ ሞት እስርና እንግልት የኢትዮጵያ ራዕይ ለማሳካት ብዙ ተከፍሏል ዛሬም እንዲሁ፣ አሁን ግን ረጋ ብለን የምናስብበት የዕረፍት ሰዓት የሚተኙበት የሚቀመጡበት ሳይሆን እርስ በርስ የሚመክሩበት  ደካማን የማያጠነክሩበት ተቀያሪ የሚቀይሩበት  ከአሰልጣኝ ምክርና ተግሣፅ  ማበረታቻ የሚያገኙበት ጊዜ ላይ ነው፡፡ ያለነው ሆኖም ጊዜው አጭር ነው፡፡
ለቀሪው 45 ደቂቃ ተግትን ለመሥራት ታሪክ ለመቀየር የጠፊውን የኢትዮጵያ ህዝብ ጥም በአንድነት የምናረካበት ለአገር የምንሰራበት ልዩነትን አጥብበና ወደጐን በመተው ለአገር ክብርና ጥቅም ሲባል አንድነትን በመፍጠር አንተ የእገሌ ነህ አንተ የእንቶኔ ነህ ውጤት ልመባባሉን ትተን መድረክ ቅንጅት አንድነት ፣ኢህአዴግ፣ኦነግ፣ ኦብነግ….. ወዘተ የሚባሉት ድርጅታዊ ስሞች ትተን ኢትዮጵያዊነትን ይዘን ለአንዱ አገራችን ለሠፊው ህዝባችን ቅድምያ በመሥጠት ልንሥራ ናስመዘግብ ይገባል እንደ ከዚህ ቀደሙ ሆድ የሚነፋ ተስፋ ህበረተበቡ አያሻውም አገርም አያስፈልገውም፡፡
      የኢትዮጵያን ህዝብ እንደምናየው ለአትሌቱም፡ ለእግር ኳሱም፡ ለአባይም….. ድጋፉን በነቂስ ያሳያል ባለሀብቱም ለድጋፍ እጁን ይዘረጋል፡ቃል ይገባል፡ከዚህ ቀደም እንዳስለመዱት ለተጫዎችቹ የተለያዩ ስጦታዎችን ለማበርክት ቃል የገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡  ታዲያ የፓለቲካ መሪዎቻችን፣ የሃይማኖት አባቶቻችን መከፋፈሉን ትተው እርሰ በርስ መነቋቆሩን አቁመው በአንድነት እጅ ለእጅ ተያይዘው በአንድ አላማ ለአንዲት አገራቸው ለሠፊው ህዝባቸው ቢተጉ እውን ኢትዮጵያ ሥሟ በርሃብና በእርስበርስ ጦርነት ይነሳ ነበር በፍፁም  ሃያ እና ሰላሳ አባላት  የያዘ አንድ ቡድን የደገፈና ለድል ያበቃ ህዝብ፣ ቡድኑን በመምራትና በማሰልጠን ለድል ያበቃ አንድ አሰልጣኝ  ሰ31 ዓመታት በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ካቀደጀና ለአፍሪካ ዋንጫ ካበቃ አንድ የአገር መሪ ደግሞ ከሚኒስተሮችና በተለያየ ደረጃ ላይ በመሆን የሚሰሩትን ባለስልጣናት በመያዝ 80 ሚሊዮን የሚሆነውን የኢትዮጵያ ህዝብ ከጐኑ በማሰለፍ ኢትዮጵያን  መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ማሰለፍ ፣ ህዝቦቿን ደግሞ እስር በርስ የሚፋቀሩ አገርን ለማልማት ጠንክረው የሚሰሩ ዜጐች ማድረግ ይችላል፡፡  የፓለቲካ ልዩነትን ወደ ጐን በመተው አገርንና ህዘብን  በማሰብ መከፋፈል  ያሳደጋት አገር፣ እርስ በርስ ጦርነት ያለማት አገር የለችም ስለዚህ ትናንት  አልፋል በትናንት በሬም ያረሰ የለም ዛሬ ደግሞ 45 ደቂቃ ግማሹ ዘመናችን ተጋምሷል በቀሪው ጊዜአችን አመርቂ ውጤት ለማምጣት የጐሪጥ መተያየቱን ትተን ተናበን ወደ ድል ለማምራት አንዱ እንሁን ህዝቡን ለጦርነት ሣይሆን ለልማት እንጠቀምበት በድጋሜ ዛሬ ላይ ሆነን የምንሥተው ሥተት እንደትናንቱ በቸልታ የሚታለፍ ሣይሆን ትልቅ ዋጋ የሚያስከፍለን ከተለወጥን ዳግም ከድህነት ታሪክ ወደ መካከለኛ ገቢ የምንሸጋገርበት አለበለዚያ ግን ባለንበት የምንረግጥ ባስ ካለም እጅግ ወደታች የምንዘግጥበት ሰዓት ነው፡፡
    በአገራችን ላይ የተንሰራፋው ችግር የጐልማሳ ዕድሜ የያዘው በተተኪው ትውልድ በጐረምሣው ታሪክ ሆኖ ሊቀር ጊዜው  አሁን ነው የመተካካቱ ጅማሬ  አኩሪ  በሆነ መልኩ ሊቀጥል ግድ ይላል አሰልጣኝ ሠውነት ቢሻው በጥንካሬ ቡድናቸውን በታክቲክ  በቴክኒክ በሞራል በአካል ብቃት  በአሰላለፍ…… ወዘተ ብቁ በማድረግ ከድል እንደበቁት ሁሉ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ብሔራዊ የአገር ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን፣ ክቡራት ሚኒስተሮችን አምባሳደሮችን፣… ወዘት ለልማቱ ለዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ብቁና ትጉህ ቀና ቡድን ሊያበቁ የሚገባበት ሰዓት አሁን ሉ፡፡  ለአገር ዕድገት የተናጠል ሣይሆን የጋራ /የቡድን/ ሥራ የሚሠራበት ሠዓት ላይ እንደሚገኙ ልብ ሊሉት ይገባል፡፡
     አሁን ጊዜው የፓለቲካ ልዩነት ወደጐን የሚባልበት የአገር አንድነትንና ልማትን አንግበን የምንነሣበት ሰዓት ላይ ነው ያለነው እገሌም እንቶኔም ማንመ ይሁን ምንም በጥላቻ መፈራረጅ አቁመን በፍቅርና በአንድነት መንፈስ ለአንዲት ኢትዮጵያ  ለሠፊው ህዝብ ጥቅም ሲባል መሥራትና ማልማት ብቻ በግብ ብልጫ ለድል መብቃት እገሌ የሚባል ድርጅት አባል ግብ አስቆጠረ መሆኑ ቀርቶ ኢትዮጵያ አሸነፈች የሚለው ሊቀድም ይገባል፡፡  የባከነ ሰዓት ላይ ነውና ያለነው ጠላትን በመከላከል ክፍተትን በመሸፈን አስተማማኝ ውጤትነ ለማምጣት መከላከልን መሠረት ያደረገ ጥቃት በድህነት  ላይ በጦርነትና በረሃብ ላይ በድንቁርና እና በበሽታ ጥቃት መፈፀም ግዴታ ነው ፡፡
     ብሔራዊ ቡድናችን ለዚህ ድለ እስከሚበቃበት በብሔራዋ ቡድኑ ብዙ አጥቂዎች ተከላካዮች አማካዮች ነበሩት ይበልጡኑ ደግሞ ግብ በማግባት የሚታወቁ ነገር ግን በጉዳት በተለዩበት ሰዓት እነርሱን ሳናሳልፍ እንዴት ብሔራዊ ቡድኑን ለጨዎታ እናሰልፋለን ብሎ ህዘቡ ሲጨነቅ ቡድኑ ግን አጥቂያችን ቢጐዳ አንበላችን መካከላችን ባይኖር እኛም ግብ ማስቆጠር እንችላለን አምበልም ከመካከላችን ማፍራትና መተካት እንችላለን፣ የቡናው ባይኖር የጊዮርጊሱ ከዚያም ቢጠፋ የደደቢቱ ወይም የስኳር ፋብሪካው አለ በማለት በልብሙሉነት  የአገራቸው ታሪክ እንደቀየሩና የ31 ዓመቱን ክብሯን መልሰው ለማምጣት እንደበቁ መላው ኢትዮጵያዊ በክቡር ጠቅለይ ሚኒስትሩ እና በብፁዕ ፓትራያሪኩ ድንገተኛ ህልፈት ህይወት ቢደናገጥና ተስፋ ቢቆርጥ የተያዘው ልማት እንደማይደናቀፍ እኛም አለን በማለት ከየድርጅቱ የጐደለውን አሟልተውና የተሻለ ቡድን በመፍጠር የአገርን ሥምና ታረክ መጠበቅ ግድ ይላል ኢትዮጵያዊነት የሚለካበት ጊዜው አሁራ ነውና እነዚህ  ሠዎች ቢኖሩ መልካም ነበር  ባይኖርም ግን እንሰራለን እንለወጣለን የአንድ ሠው አስፈላጊነት አለ የማይባል ቢሆንም አገር ግን በአንድ ሠው ራዕይና ግብ የትም አትደርስም በህብረትና በአንድነት እንጂ እነዚሀ ሠዎች ለአገር ያላሠለሰ ጥረት ቢያደርጉም ዛሬ የሉም እነርሱ የሉምና አገር እጃን አጣጥፋ ትቀመጣለች ማለት አይደለም ተጫዋቶቹ የብሔራዊ ቡድኑ አባል ናቸው እንጁ ብሔራዋ ቡድኑ የነርሱ /የግለሰቦች/ ነው ማለት እንዳልሆነ እንዲሁ እነዚህ መሪዎች የአገርና የህዝብ ሀብት ናቸው እንጂ አገር የነርሱ የግል ጥቅም የነርሱ የአዕምሮ ውጤት ናት ማለት አይደለም ምናልባት የላቀ አስተዋፅኦ አድርገው ይሆናል አድርገዋልም ነገር ገን በነርሱ ህልፈተ ህይወት የአገር ጉዳይ ተዳፈነ ማለት አይደለም ጥቂቶች ቢያልፋ በብዙሃን ይተካልና፡፡
     በብሔራዊ ቡድኑ ውስጥ አጥቂው በጉዳት ከሜዳ ስለወጣ አለበለዚያም በቅያሬ ከሜዳ ስለወጣ ተከላካዩ መከላከሉን በረኛው ግብ መጠበቁን አማካዩ አቀብሎ ተተኪው ግብ አያስቆጥርም ማለት እንዳልሆነ እንዲሁ የተያዘውን መርኃ ግብር ልማት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ለማሳካት የቀድሞዎቹ ባለድርሻ አካላት አዲሶቹም ተሻሚዎች ነባሮችን ተክተው ዕቅዱን አያስፈፅሙም ማለት  አይደለም፡፡  በእግር ኳስ ሜዳ አጥቂው ሲወጣ ሌላ አጥቂ ይመጣል እንጂ የማጥቃት  ሞያውን ለብሔራዊ ቡድኑ ይዞ የግድ የአጥቂውን የማልያ ቁጥር ይዘህ ካልመጣህ  ሥምህን ካላስቀየርክ እንደማይባል እንዲሁ የጠቅላይ ሚንስትሩን ሥም ብሔር አስተሳሰብ እምነት አቋም፣ ቋንቋ፣…… ይዘው መምጣት አይጥበቅባቸውም ዋናው አላማቸው  ግብና ውጤት እንጂ፣ ተቀያሪው ሲመጡ ያሰሩትን  ሊፈቱ፣ የነፈጉትን ሊሰጡ፣ የሾሙትን ሊሽሩ፣ ያጥላሉትን ሊወዱ፣ ያራቁት ሊያቀርቡ፣ የሠቀሉትን ሊያወርዱ… ህጉ ይፈቅድላቸዋል የርሳቸው ለምድ ለብሰው ሊመጡ አይገደዱም ተተኩ ሳይሆን የሚባለው በምትሃተዊ መንፈስ ተቀየሩ እንጂ ስለዚህ ብሔራዊ ቡድን ጨወታ ላይ የቡድን ውጤት አሳምሮ አገርን ለድል ለማብቃት የመተካካቱን ሥራ በጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል ምናልባት እንደብሔራዊ ቡድናችን ተጫዎቻችን በጉዳት አለበለዚያም በቀይ ካርድ ከሜዳ ስናጣ ባለሙያውን በረኛ መቀየር አቅቶን ተጫዎች ውጤቶን ለማስጠበቅ  ለቁጥር ያህል ብቻ ሲባል ሙያው ያልሆነውን ተጫዎች በመተካት ታሪክ ሊያበላሽ የሚችል ዋጋ ልንከፍል እንችላለንና ብሔራዊ ቡድኑም ፓርላማውም ይህን ልብ ይበሉት፡፡ 
     ወደ ማጠቃለያው ማንሳት የምሻው ዐብይ ጉዳይ የብሔራዊ ቡድናችንን ደስታ የህዝባችንን ተሰፋ ታሪክን እንደነበር ሊያስቀጥልና የአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ ህልማችንን ሊያደበዝዝ የነበረው የመጨረሻ የሱዳን አቻችን ሙከራ ግብ መሆን ነበር ሴኔጋላዊዉ ዳኛ የጫወታውን ፍፃሜ ማብሰሪያ ፊሽካ ባይነፋ ኖሮ ይህ የሚያመለክተው አሁንም  በእግር ኳሳችን ላይ ምንም አንኳን ድልን መጐናፀፍ ብንችል ጠንክረን ያልስራነውና ያልደፈነው ክፍተት እንዳለ ያሳየናል  ስለዚህ የብሔራዊ ቡድኑ ዛሬም ለደቡብ አፍሪካው የዋንጫ ትንቅንት የበለጠ ሊራ ህዝቡም ከሜዳ ውጭም ሊያበረታቸውና ሊደግፋቸው ሊመክራቸውና ሊገስፃቸው ለድል ሊያበቃቸው የሚገባውን ሁሉ ሊያደርግ ይገባል፡፡  ልብ ብለን ልናጤነው የሚገባው ይህ ትውልድ ሊቀይረው ያልቻለውን ጉዳይ ዋጋ እንከፍልበት ነበር  የተዘናጋንባት የመጨረሻ ግብ ታሪክ ታዝባ፣ ደስታን ታጨልም፣ ሌሎች ችግሮችንም ታመጣ ነበር፡፡
      እንዲሁ ደግሞ የአገራችንን ልማት፣የድህነት ቅነሣ የበሸታን ማስወገድ፣ የጦርነትን በሰላም መተካት…… ሁሉ ትናንት መልካም ጅማሬ ሊኖረው ይችላል፣ ይህ ግን አስተማማኝ አይደለም በአገር ጉዳይ ተዘናግተን ሌላ ነገር ላይ አትኩሮታችን ከተሰረቀ በግለሰብ ጉዳይ ላይ ከደረግን አርን ወደኃላ ልናስቀራት የትናንት ታሪካችንን ልንደግም የህዝቡን የረጅም ዘመን ናፎቆት ተስፋ ልናጨልምበት ነው ማለት ነው ይህን ድህነት ጐልማሣውን በጐረምሣው ጥረታችን ታሪክ እናድርገው እስኪ ጠቅለል አናድርገው የአይናለምንና የአዲስህንፃን የበረኛነት እኔ ነኝ  እኔ ነኝ የአገርን ድል ለማስጠበቅ የነበረ ትንቅንቅ መቃኘት ይቻላል፡፡  በረኛችን ደማል ተጐድቶ ከሜዳ መውጣት እንዳለበት አሠልጣኝ ሠውነት ቢሻው እንደሰማ ዓይናለም በረኛ መሆኑን ከዚህ ቀደም በነበረው ታሪኩ ያውቀው ስለነበር ጓንት አጥልቆ ማልያ ቀይሮ ካጠናቀቀ በኃላ አዲስ ህንፃ በልበ ሙሉነት በመምጣት እኔኮ በበረኛነት አሪፍ ነኝ በመለት ክፍተቱን ሊሞላ ዝግጁ መሆኑን ለሠውነት ይነግረዋል፣ ሠውነትም በቃ አንዴ መድቤአለሁ አላለም ተነጋገሩበት ብሎ አድሉን ለተጫዎቶቹ ሠጠ ዓይናለም ከእኔ አዲስ ይበልጣል በማለት ማልያውን አወለቀ ተጫዎቶቹን አዲስን ደገፋ ጨዋታውን ቀጠሉ በድል ተጠናቀቀ፡፡
    ይህ አጋጣሚ በአሜሪካ የኘሬዘዳንታዊ ምርጫ በ2001 ዓ.ም. ሲካሄድ የነበረውን ቅስቀሳ ለኘሬዘዳንትነት ዕጩ የነበሩት ማኬ ከእኔ ባራክ ኦባማ ይበልጣል በማለት ከግል ሥልጣን ይልቅ አሜሪካንን አስቀድመው ነበር፡፡  ዓይናለምም ከእኔ አዲስህንፃ ይበልጣል በማለት ታሪክ ደገመ፡፡  ኢትዮጵያን በመጪው ዘመን ታሪኳን ለመቀየር ዉጤታማ ለማድረግ ፍቅር እንጂ ፀብ አይጠቅማትም አንተ ትብስ አንች ትብስ ከኔ አንተ ትሻለለህ አንተ ትክክል ነህ መባባል አንጂ መናቆር የጐሪጥ መተያየት የትም አያደርሳትም እንደ ዓይናለም ያ ተጫዎች፣ መሪ፣ የፓለቲካ አራማጅ፣ የሃይማኖች ሰባኪ፣ የለውጥ አርበኛ፣ ኢንቨስተር፣የመንግሥት ሠራተኛ፣ አባወራና እማወራ …..ወዘተ ነው የሚያስፈልጋት የግል ክብር ማድመቂያ ማለያችንን አውልቀን፣ የሥልጣን ዘመናችንን በቃ ብለን፣ ከተቆናጠጥነው መድረክ ወርደን ማይኩን ለሌላ በማቀበል ከአኔ ወንድሜ/እህቴ ይሻላል ትሻላለች፣ ከዚህኛው የፓሊተካ ፖርቲ ይኸኛው ይልቃል ከዚህኛው ያኛው ይሻላል እርሱ ስልጣኑን ይረከብ እኛ ደግሞ በመደገፍ አብረን እንስራ ልንል ይገባል፡፡ የህዝብን ድጋፍ ሳይዙ ሥልጣን ለመቆናጠጥ መጣር፣ በራስ መተማመንን ሣይዙ ለሥልጣን መደናበር በቃ ህዝቡን የልማት ሠራዊቱን በተለያዩ ነገሮች ማደናቀፍና ማሸማቀቅ ጣልቃ ገብነት ይቁም እንደ ሠውነት ቢሻው ራስን ዝቅ በማድረግ እናንተ በፍቅር አድርጉት ከእኔ አናንት ትሻላላችሁና፣ ጉዳዩ የጋራችን ነውና በማለት ድሉን በፍቅር የሚያደምቅ መር፣ ባለሥልጣን፣ የሥራ ኃዥለፊ፣ የቡድን መሪ ያሻናል፡፡ ከእንግዲህ ኢትዮጵያን በጦርነት በአንባገነንነት እኔ ብቻ አውቅለተለሁ በሚል መንፈስ መምራት ሊያከትም  በፍቅርና በህብረት የምንመራበት የምናስተዳድርበት ሰዓት ነው ይህን የሚደግፍ ማልያውን አውልቆ ለሚሻለው ብቁ ለሆነው  ይስጥ፡፡
ጆሮ ያለው ይስማ ልብ ያለው ልብ  ይበል ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ! ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!፡፡

ቅዳሜ 13 ኦክቶበር 2012

ፍቅር በFace book ክፍል ሁለት


በክፍል አንድ “ፍቅር በFace book” በሚለው እውነተኛ ታሪክ ላይ መሰረት ያደረገ ክፍል ማቅረባችንን ሳሙኤል በFace book ላይ የተዋወቃትንና ሳይስቡት ፍቅር ውስጥ ገብተው በኃላም ሕይወትን የመጀመር አዝማሚያ አሳይተው ከትውልድ ቀዬው ከአዲስ አበባ ተነስቶ የፍቅረኛው ልታገኘው እንደልፈልገች እንዳፌዘችበት፣ ደግሞ የህይወቱን ቁስል እንዳደማችበት ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ በብዙ ልመና ሆስፒታል በር ላይ ሰላም ብሏት እንዳተመለሰና ተስፋ ቆርጦ እንደነበር ተመልክተናል ቀጣዩ የሳሙኤል ገጠመኝ ምን ይመስላል? አብረን የምናየው ጉዳይ ይሆናል፡፡

        ‹‹ሴት ልጅን ያመነ ጉም የዘገነ አንድ ነው›› ስልህ እንዲሁ ከመሬት ተነስቼ አይደለም ወይንም ለሴቶች ጥላቻ ኖሮኝ በዚህ ተነስቼ አይደለም ወይንም ለሴቶች ጥላቻ ኖሮን በዚህ መንገድ ለመግለጽ ፈልጌ አይደለም ከሴቶች ተሽዬ ለመገኘት የጥላቻ ሰው ሳይሆን የፍቅር ሰው ሆኜ መገኘት እንዳለብኝ ከልቤ አምናለሁ ይህንን ስልህ የተቀደሱ ንዑዳን ክቡራን ናቸውና ፍቅር ይገባቸዋል እያልኩህ አይደለም፡፡ ይገርምሃል ከረጅም አመታት በፊት ለሴቶች ልዩ ክብርና ፍቅር ….ነበረኝ አሁንም ቢሆን ተረቶች ሁሉ ከብዙ ሰው ጋር ያጋጩን ነበር፡፡ ነገር ግን ሁሉም ነገር በራስህ እስካልደረሰ በስተቀር ስሜቱ አይገባህም ቁስሉ አይጠዘጥዝህም … አሁን ለአንተ የምነግርህን ነገር ለአስር ሰው ባወራላቸው በእርግጠኝነት ሁሉመን ‹‹የአንተ በምን ይለያል በሰው ከደረሰው የተለየ ምን ደረሰብህ? ይኼ ደግሞ ሰው ሆነህ ስትኖር የሚያጋጥም ነገር ነው ….›› እያሉ እንደሚያረክሱብኝ ይገባኛል፤ እኔኮ ከህመሜ ፈውሱን ተበድያለሁና ካሳ ክፈሉኝ ወይም ፍረዱልኝ እያልኩ አይደለም ቢያንስ ጭንቀቴን ስሙኝ ነው እያልኩ ያለሁት እግዚአብሔር ከዚህ ይሰውርህና አንተ ግን እየሰማኸኝ ውስጤን ተንፍሼልሃለሁ አንተም ልብ ብልህ ትማርበታልህ ከበተራታህም ሎሎችን ታስተምርበታለህ፡፡

        ‹‹ምን ሆኖ ነው ገና ለገና ያፈቀርኳት ልጅ ላገኝህ አልፈልግም ስላለች ወይም ስለጠላችው ወይም ስለከዳችው እንደዚህ የሚሆነው?›› ትል ይሆናል በለኝ ግዴለም እኔ ግን ያጋጠሙኝን ገጠመኞች ላጫውትህ ገና አሥራ ስምንት አመት ሳይሞላኝ አንዲት የሶስት ልጆች እናት ትዳሯን እስከ ልጆቿ በትና ጎረምሳ ተከተትላ ስትሄድና ለአስታራቂ ሽማግሌ ስታስቸግር አውቃለሁ እንዲሁ ይህ ከሆነ ከሁለት ዓመት በኋላ የመጀመሪያ ፍቅሯን አጣጥማ ሳትጨርስ አንድ ልጅ ወዳው በፍቅር ላይ ፍቅር እያስጨነቃቸው ጮቤ እየረገጡ ሳለ ምንም ሳይጎድልባት ጨዋ ቤተሰብ አሳድጓት የተማረ ሁሉ የሞላው ይህ ጉደለው የማይባል ከልቧ የምታፈቅረውን አግብታ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ ተያዘች ባልም ፍቅርን እንደሻማ ያልብሳችሁ ብሎ መርቆ ፈታት በተከበረበት አገር አንገቱን አስደፋችሁ ገና ለጋ ፍቅሩን ቀነጠሰችበት የጋለውን ሥሜቱን ቀዝቃዛ ውሃ ደፋችበት ሌላናዋ ደግሞ እንዲሁ ከት/ት ቤት ጀምሮ ፍቅረኛዋ የነበረውን አገር ምድሩ እንደባልና ሚስት ሲመለከታቸው በነበረበት በትውልድ አገራቸው በክብር በስነ ሥርዓት ተጋብተው ልጅ ለመውለድ አርግዛ ሳለች ይጋጫሉ እርሱም ከርቀት ከሚሰራበት ቦታ ይቅርታ ለመጠየቅ ለዕርቅ ደከመኝ ሰለቸን ሳይል ይመጣል ይታረቃሉ ይሄዳል ደግመው ይጣላሉ ደግሞ ይመጣል ይሄዳል ተሰቃየ ጉልበቱ በመንገድ አለቀ ግን ምንም ለውጥ የላትም ከትዳር በኋላ ፍቅራቸው ያልተዳፈነ እሳት ሆነ ቢጭሩት የማይቀጣጠል በስተመጨረሻ በፍርድ ቤት ከሰሰችሁ በመሃል ልጅም ተወለደ የፍቺ ደብዳቤም ደረሰው ፍርድ ቤት ጊዜ ሰጣቸው ልጁንም እያሳደገ ተቆራጭ እያደረገ ፍቅሩን ደጅ እየጠና ቆየ ያሰበው ግን አልተሳካም ተፋቱ ልጄን ልውሰድና ላሳድግ ብሎ ሲጠይቅ ያንተ አይደለም ተባለ እናስ የማነው ተብሎ ሲጠየቅ የሁለቱም ጓደኛ የነበረ ቤተኛ የሆነ ይህን ያደረጋል ተብሎ የማይጠበቅ በጫጉላቸው ጊዜ እንኳን እንደ ወንድም እንደ ወዳጅ አብሮ ሲጫወት አብሮ ሲበላ ሲጠጣ እያደረ እየሰነበተ ትዳርን ያላመደ ባልንጃራቸው ልጅ እንዳሆነ መጨረሻም ፊርማቸውን እንኳን ሳይቀዱ አብራው መኖር ጀመረች ባለቤት ተብዬ ጓደኛዬም ልቡ ተሰበረ ሥሜቱ ተነካ ክብሩን ተነካ ይኼ የምንግርህ ጥቂቱ ነው ምናልባት አዲስ ነገር ነው ወይ? ወንዱስ ቢሆን? ልትለኝ ትችላለህ፤ ወደ እኔ እንምጣ ደግሞ የልጅነት ፍቅረኛዬ ሠንቄ ከነበረው ከሕይወት ዓላማዬ አደናቅፋ የፍቅርን ፊደል አስቆጥራ የፍቅርን ጽዋ አስጎንጭታን እያጣጣምኩት እያለሁ ልትለየኝ ልትጠላኝ ምላ ተገዝታ ያጋጠማትን የአሜሪካ ኑሮ ዕድል ተጠቅማ ከሄደች በኋላ ከወራት በኋላ የውሃ ሽታ የሆነችብኝ ምን ባደረኳት ነው? ቃሏን ለምን አጠፈች? እኔኮ የዶላር ችግር የለብኝም የፍቅር እንጂ፣ እኔኮ አሜሪካ እንድታኖረኝ አይደለም ህልሜ በልቧ እንድታኖረኝ በልቤ እንድትነግስ እንጂ ፡፡ ዛሬ ደግሞ ፍቅርን እንደምፈራ እየነገርኳት ህመም አለብኝ ቁስሌ እንዳያገረሽብኝ እያልኳት ከተማፅኖ ጭምር እያፈቀርኳት እንዲህ ማድረግ ምን ይሉታል? ምን በደልኳት? ታዲያ ‹‹ሴት ያመነ ብል ይፈረድብኛል? እስኪ ፍረደኝ! በል እስቲ ህሊናህ ያለህን ፍርድ በይንብኝ በል እባክህ ጥፋቱ ያንተ ነው ብለህ ጥፋቴን ቦታውን ጠቁመኝ እያለ ሲቃ እየተናነቀው ራሱን መቆጣጠር አቅቶት ድምጹ ሌሎችን እስኪረብሽ ድረስ ከፍ በማድረግ ትናንት ያገኘሁት ሣይሆን የጥንት ጓደኛው ያህል ስሜቱን መቆጣጠር እስኪሳነው ህመሙን ጭንቀቱን ተነፈሰልኝ፡፡

        ይኸውልህ ደረሰ ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስብው የርሷ የባህሪ ለወጥ የጀመረው አንድ ቀን ድንገት ይሁን አስባበት አላውቅም ‹‹ታገባኛለህ? አለችኝ እውነቴን ለመናገር እርሷን ማግባት የኔ ሥራ እንጂ የርሷ ጭንቀት አልነበረም ምክንያቱም ወድጃታለሁና፡፡ ነገር ግን መዋሸት አልፈልግምና ሁሉን ነገር ዘርዝሬ ነገርኳት ደሞዜ ስንት እንደሆነ ከዚያ ላይ የተጣራ የሚደርሰኝን ለቤተሰብ የቤት ወጪ ሥንት እንደምሰጥ የዓባይ  ግድብ የቦንድ ግዢ……. ተቆራርጦ ሥንት እንደሚቀረኝ ነገርኳት ከተወሰነ ወራት በኋላ የዓባይም እንደሚያልቅ ነገሮችም ሲስተካከል እንደምንነጋገር ሆኖም  ግን የኔና የርሷ መጨረሻ አብሮ በትዳር እንደሆነና ዛሬ ግን ልዋሻት እንደማልፈልግ አጉል ቃል እንደማልገባ ነገሮችን አስተካክዬ እኔ ራሴ ልታገባኝ እንደምትፈልግ እንደምጠይቃት ነገርኳት የተወሰነ ቅሬታ አነበብኩባት ከኔ ጭንቀትና እውነት ውሸትና ቅሬታ ሽንገላ በሥሜት ‹‹አዎ አገባሻለሁ›› እንድላት ፈለገች ይሁን እንጂ የከፋ ነገር በመካከላችን አልነበረው የሆዷን እግዜር ይወቀው እንጂ እንዲያውም ብር ልላክልህ ትለኝ ሁሉ ነበር፡፡

        የኔ ፍቅር ከቀን ወደቀን እየጨመረ ሲመጣ በመካከላችንም የነበረው እንቅፋት የፍቅር ችግር ሳይሆን በኢኮኖሚ ራስን አለመቻል ስለነበር ወደያው አንድ ነገር ወሰንኩ ስራ ማፈላለግና የተሻለ ደመወዝ ተከፋይ መሆን እንዳለብኝ ምክንያቱም ጥሩ የስራ ልምደና የት/ት ደረጃ አለኝና የሚገርመው በወራት ውስጥ የምፈልገውን ሥራ ከእጥፍ በላይ በሆነ ወርኃዊ ደመወዝ ተቀጠርኩ ወደ ድሬደዋ የፍቅር አገር የመጣሁት ስራ ከመጀመሬ በፊት ይህንን የምስራች ለፍቅሬ ልነግራት ታገቢኛለሽ ወይ ብዬም የትዳር ጥያቄ ላቀርብላት፣ እመጣለሁ ብዬ ቃል የገባሁትንም ቃልኪዳኔን ለመፈጸም ለድርብ ድርብርብ ደስታ ነበር ጉዞዬ ከአ.አበባ ድሬደዋ ነገር ግን በድሬደዋ ሙቀት ውስ ፍቅራችን ለፍሬ እንደ ደረሰ ሰብል ታጭዶ ተወቅቶ ወደ ጎተራ ሳይገባ ውርጭ መታውና ልቤን ደግሞ የፍቅር ጦር አደማው ላይሻለኝ ላይጠገን ልቤ ተሰበረ ‹‹ ጉም ጨበጥኩልህ ሥቅሥቅ  ብሎ አለቀሰ፡፡ ግራ መጋባት በሚታይብኝ ሁኔታ ‹‹አይዞህ›› እያልኩ ለማጽናናት እንዳያለቅስም ‹‹አታልቅስ›› በማለት አባበልኩት፡፡

        ደረሰ ተወኝ እባክህ ለምን አላላቅስ ለምንስ አላነባ ምን ቀረኝ ፣ጌታዬኮ አብሬያት እንድኖር ከግራ ጎኔ አጥንት ከፍሎ የሰጠኝ ሴትን ነው፡ ታዲያ ሴቶች እንዲዘህ እንደጉም አልጨበጥ ካሉ  ወንድ ላግባ እንዴ?! ምን ለማለት ነው አታልቅስ የምትለኝ እያፅናናኽኝ እያበረታኸኝ ነው? ወይስ በቁስሌ  ላይ እንጨት እየቆሰቆስክበት ነው?

        እምባ ተናነቀኝ የወንድ ልጅ ሐዘን እና ጉዳት አሳዘነኝ እኔም የራሱን ጥያቄ መልሼ ራሴን ግን ለምን? አልኩት፤ታዲያ አሁን ምን እያደረክ ነው? በማት በጥያቄ መልክ ጨዋታ ለመቀየር ሞከርኩ ከሐዘኑ የማስወጣበትን መንገድ እየፈለኩ፡፡

        ‹‹አሁን ምን አደርጋለሁ እቅዴን ምኞቴን ተስፋዬን ውሃ ባለው መነሻዬን ራስ ሆቴል አድርጌ ዳቻቱ ሰፈር፣ መጋላ፣ ኮኔል ድልድይ፣ ከዚራ፣ ለገሃር፣ ሃምበር ዋን፣ ሃራር መውጫ፣ ታይዋን፣ ሳቢያን፣...ወዘተ እያልኩ ላይ ታች ሥል ውዬ ዛሬ ደግሞ ራስ ሆቴል አርፋለሁ፤ የከፋው (ግራ የገባው) ቱሪስቱ ታውቃለህ እንደዚያ ሆኛለሁ፡፡

        አይዞህ ታሪክ ይቀየራል ራስህን አትጉዳ በትዕግስት ነገሮችን በሙሉ መርምራቸው ደግ ሴቶች በሙሉ አንድ አይደለሙ ወላድ በድባብ ትሂድ እዛው አዲስ አበባ የአገርህን ልጅ ታፈቅራለህ አይዞህ!

        “ምን አልክ ፍቅር?! ፍቅር እንደገና ! ሴት ልጅን እንደገና ላምናት? ይገርምሃል አንድ ጓደኛዬ በሆነ ወቅት ስለ ሴት ልጅ ያለውን መጥፎ አመለካከት ተመልክቼ እንዲራራ መልካም አመለካከት እንዲኖረው ብዙ ጥረት አደርግ ነበርና ስለሴት እናትነት፡ እህትነት፡ሚስትነት፡ ወዘተ እያነሳሁ ብዙ ብዙ ነገር እለው ነበር ዛሬም አንተ ለምን እንደዚህ እንደምትለኝ ይገባኛል፡፡ አዎ የምትለውን በሙሉ ነች አምናለሁ ነገር ግን ያ! ጓደኛዬ እንዳለኝ ሴቶች የሚመቻቸው ከርህራሄ ይል ጭካኔ፣ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ፣ ከመግባባት ይልቅ ፀብና ክርክር፣ አብሮ ከመኖር መለያየት ይመቻቸዋል።ይኸም የመጣዉ ከጥቅም ፈላጊነታቸውና ራሳቸውን አብዝተው ከመውደዳቸው የሚመነጭ ይመስለኛል። ዛሬ ዛሬ እንደውም ከወንድ በተቃራኒ በሆኑ ቁጥር የሚወደዱና የሚፈለጉ እየመሰላቸው ሲሞላቀቁ ይታያል፡ እውነታው ግን ይህ አይደለም በተቃራኒው ነው ስለዚህ አያስፈልጉኝም፡፡››

        ‹‹እስኪ የመለያየታችሁ፡ ይቅርታ የመቀያየማችሁ ዓብይ ጉዳይ ምንድን ነው ብለህ ታስባለህ?

        ‹‹ግልፅ ነውኮ ያኔ ነገሮች ባልተስተካከሉበት ወቅት ለርሷ ወቅታዊ ላልሆነ አጣዳፊ ጥያቄ አገባሻለሁ የሚል የውሸት ተስፋ ስላልሰጠኋት ነው፤ እስኪ ተመልከታት ይህቺን ሴት እኔ ያኔ ብዋሻት ዛሬ ድረስ ከኔ ጋር ነች፡ አሁን ሥመጣ በደስታ ትቀበለኛለች አዲስ አበባም ትመጣ ነበር ያፈለገንንም ነገር እናደርጋለን ደግሞ ስለ መጋባት አናነሳም በቃ! ምናልባት ‹ቆይተን መቼ ነው ታዲያ የሰርጋችን ቀን?› ትለኝ ይሆናል፡፡››

        እሷም ጥያቄዋ ስህተት ያለበት አይመስለኝም እውነትዋን ነው የማታገባት ከሆነ ለምን ጊዜዋን ታባክናለች?

        ‹‹እኔስ ምንድን ነኝ ዝም ብዬ ጊዜዬን የማባክነው የወንድ ልጅ ዕድሜ እና የዕባብ ዕድሜ አንድ ነው ያለው ማን ነው? የኛም ዕድሜ ይሄዳልኮ እንደ ሴቶቹ ባይሆንም፤ እኔ ደግሞ ራሴን እፈልገዋለሁ ዝም ብዬ አልንዘላዘልም፡፡ የማላገባትን የእኔ ያልሆነችዋን ሴት አልፈልጋትም ወንድ አዳሪ አይደለሁምኮ፡፡

ቀጣይ ጊዜህን ታድያ እንዴት ታሳልፋለህ ያለሴት መኖር ይከብዳል፡ ለምን አላስታርቃችሁም?

አመስግናልሁ፡ግን አሁን የማሰቢያ ጊዜ ነዉ የምፈልገዉ ዳግም የምሳሳትበት ጊዜ አልፈልግም፡፡…ለወንዱም ለሴቱም መልካም ዘመን እና ጣፋጭ የፍቅር ጊዜ እመኝላቸዋለሁ። እነሆ ላንተም መልካም መዝናኛ፡፡

አሜን ብዬ ምርቃት ከተቀበልኩ በሁላ ይጠቅም ይሄናል በማለት እንዲህ አስፍራለሁ፡፡

(ገጠመን የምትሉትን ፍቅር በfacebook ላኩልኝ እኔም እንዲህ ለሰፊዉ ህዝብ ጥቅም በምስጢር አቀርበዋለሁ።)

ክፍል 3 በእኛዉ ገጠመኝ እና ታሪክ ፈጣሪ ካደረሰን እናንተም ከላካችሁልኝ እንገናኛለን፡ቸር ይግጠመን።

ማክሰኞ 9 ኦክቶበር 2012

ቅዱሣት መካናት በፎቶግራፍ

  ቁልቢ ገብርኤል
                                                                        ሀረር መድኃኒዓለም
አዲስዓለም ማርያም
 

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...