ቅዳሜ 13 ኦክቶበር 2012

ፍቅር በFace book ክፍል ሁለት


በክፍል አንድ “ፍቅር በFace book” በሚለው እውነተኛ ታሪክ ላይ መሰረት ያደረገ ክፍል ማቅረባችንን ሳሙኤል በFace book ላይ የተዋወቃትንና ሳይስቡት ፍቅር ውስጥ ገብተው በኃላም ሕይወትን የመጀመር አዝማሚያ አሳይተው ከትውልድ ቀዬው ከአዲስ አበባ ተነስቶ የፍቅረኛው ልታገኘው እንደልፈልገች እንዳፌዘችበት፣ ደግሞ የህይወቱን ቁስል እንዳደማችበት ለጥቂት ደቂቃዎች ብቻ በብዙ ልመና ሆስፒታል በር ላይ ሰላም ብሏት እንዳተመለሰና ተስፋ ቆርጦ እንደነበር ተመልክተናል ቀጣዩ የሳሙኤል ገጠመኝ ምን ይመስላል? አብረን የምናየው ጉዳይ ይሆናል፡፡

        ‹‹ሴት ልጅን ያመነ ጉም የዘገነ አንድ ነው›› ስልህ እንዲሁ ከመሬት ተነስቼ አይደለም ወይንም ለሴቶች ጥላቻ ኖሮኝ በዚህ ተነስቼ አይደለም ወይንም ለሴቶች ጥላቻ ኖሮን በዚህ መንገድ ለመግለጽ ፈልጌ አይደለም ከሴቶች ተሽዬ ለመገኘት የጥላቻ ሰው ሳይሆን የፍቅር ሰው ሆኜ መገኘት እንዳለብኝ ከልቤ አምናለሁ ይህንን ስልህ የተቀደሱ ንዑዳን ክቡራን ናቸውና ፍቅር ይገባቸዋል እያልኩህ አይደለም፡፡ ይገርምሃል ከረጅም አመታት በፊት ለሴቶች ልዩ ክብርና ፍቅር ….ነበረኝ አሁንም ቢሆን ተረቶች ሁሉ ከብዙ ሰው ጋር ያጋጩን ነበር፡፡ ነገር ግን ሁሉም ነገር በራስህ እስካልደረሰ በስተቀር ስሜቱ አይገባህም ቁስሉ አይጠዘጥዝህም … አሁን ለአንተ የምነግርህን ነገር ለአስር ሰው ባወራላቸው በእርግጠኝነት ሁሉመን ‹‹የአንተ በምን ይለያል በሰው ከደረሰው የተለየ ምን ደረሰብህ? ይኼ ደግሞ ሰው ሆነህ ስትኖር የሚያጋጥም ነገር ነው ….›› እያሉ እንደሚያረክሱብኝ ይገባኛል፤ እኔኮ ከህመሜ ፈውሱን ተበድያለሁና ካሳ ክፈሉኝ ወይም ፍረዱልኝ እያልኩ አይደለም ቢያንስ ጭንቀቴን ስሙኝ ነው እያልኩ ያለሁት እግዚአብሔር ከዚህ ይሰውርህና አንተ ግን እየሰማኸኝ ውስጤን ተንፍሼልሃለሁ አንተም ልብ ብልህ ትማርበታልህ ከበተራታህም ሎሎችን ታስተምርበታለህ፡፡

        ‹‹ምን ሆኖ ነው ገና ለገና ያፈቀርኳት ልጅ ላገኝህ አልፈልግም ስላለች ወይም ስለጠላችው ወይም ስለከዳችው እንደዚህ የሚሆነው?›› ትል ይሆናል በለኝ ግዴለም እኔ ግን ያጋጠሙኝን ገጠመኞች ላጫውትህ ገና አሥራ ስምንት አመት ሳይሞላኝ አንዲት የሶስት ልጆች እናት ትዳሯን እስከ ልጆቿ በትና ጎረምሳ ተከተትላ ስትሄድና ለአስታራቂ ሽማግሌ ስታስቸግር አውቃለሁ እንዲሁ ይህ ከሆነ ከሁለት ዓመት በኋላ የመጀመሪያ ፍቅሯን አጣጥማ ሳትጨርስ አንድ ልጅ ወዳው በፍቅር ላይ ፍቅር እያስጨነቃቸው ጮቤ እየረገጡ ሳለ ምንም ሳይጎድልባት ጨዋ ቤተሰብ አሳድጓት የተማረ ሁሉ የሞላው ይህ ጉደለው የማይባል ከልቧ የምታፈቅረውን አግብታ ከሌላ ወንድ ጋር ተኝታ ተያዘች ባልም ፍቅርን እንደሻማ ያልብሳችሁ ብሎ መርቆ ፈታት በተከበረበት አገር አንገቱን አስደፋችሁ ገና ለጋ ፍቅሩን ቀነጠሰችበት የጋለውን ሥሜቱን ቀዝቃዛ ውሃ ደፋችበት ሌላናዋ ደግሞ እንዲሁ ከት/ት ቤት ጀምሮ ፍቅረኛዋ የነበረውን አገር ምድሩ እንደባልና ሚስት ሲመለከታቸው በነበረበት በትውልድ አገራቸው በክብር በስነ ሥርዓት ተጋብተው ልጅ ለመውለድ አርግዛ ሳለች ይጋጫሉ እርሱም ከርቀት ከሚሰራበት ቦታ ይቅርታ ለመጠየቅ ለዕርቅ ደከመኝ ሰለቸን ሳይል ይመጣል ይታረቃሉ ይሄዳል ደግመው ይጣላሉ ደግሞ ይመጣል ይሄዳል ተሰቃየ ጉልበቱ በመንገድ አለቀ ግን ምንም ለውጥ የላትም ከትዳር በኋላ ፍቅራቸው ያልተዳፈነ እሳት ሆነ ቢጭሩት የማይቀጣጠል በስተመጨረሻ በፍርድ ቤት ከሰሰችሁ በመሃል ልጅም ተወለደ የፍቺ ደብዳቤም ደረሰው ፍርድ ቤት ጊዜ ሰጣቸው ልጁንም እያሳደገ ተቆራጭ እያደረገ ፍቅሩን ደጅ እየጠና ቆየ ያሰበው ግን አልተሳካም ተፋቱ ልጄን ልውሰድና ላሳድግ ብሎ ሲጠይቅ ያንተ አይደለም ተባለ እናስ የማነው ተብሎ ሲጠየቅ የሁለቱም ጓደኛ የነበረ ቤተኛ የሆነ ይህን ያደረጋል ተብሎ የማይጠበቅ በጫጉላቸው ጊዜ እንኳን እንደ ወንድም እንደ ወዳጅ አብሮ ሲጫወት አብሮ ሲበላ ሲጠጣ እያደረ እየሰነበተ ትዳርን ያላመደ ባልንጃራቸው ልጅ እንዳሆነ መጨረሻም ፊርማቸውን እንኳን ሳይቀዱ አብራው መኖር ጀመረች ባለቤት ተብዬ ጓደኛዬም ልቡ ተሰበረ ሥሜቱ ተነካ ክብሩን ተነካ ይኼ የምንግርህ ጥቂቱ ነው ምናልባት አዲስ ነገር ነው ወይ? ወንዱስ ቢሆን? ልትለኝ ትችላለህ፤ ወደ እኔ እንምጣ ደግሞ የልጅነት ፍቅረኛዬ ሠንቄ ከነበረው ከሕይወት ዓላማዬ አደናቅፋ የፍቅርን ፊደል አስቆጥራ የፍቅርን ጽዋ አስጎንጭታን እያጣጣምኩት እያለሁ ልትለየኝ ልትጠላኝ ምላ ተገዝታ ያጋጠማትን የአሜሪካ ኑሮ ዕድል ተጠቅማ ከሄደች በኋላ ከወራት በኋላ የውሃ ሽታ የሆነችብኝ ምን ባደረኳት ነው? ቃሏን ለምን አጠፈች? እኔኮ የዶላር ችግር የለብኝም የፍቅር እንጂ፣ እኔኮ አሜሪካ እንድታኖረኝ አይደለም ህልሜ በልቧ እንድታኖረኝ በልቤ እንድትነግስ እንጂ ፡፡ ዛሬ ደግሞ ፍቅርን እንደምፈራ እየነገርኳት ህመም አለብኝ ቁስሌ እንዳያገረሽብኝ እያልኳት ከተማፅኖ ጭምር እያፈቀርኳት እንዲህ ማድረግ ምን ይሉታል? ምን በደልኳት? ታዲያ ‹‹ሴት ያመነ ብል ይፈረድብኛል? እስኪ ፍረደኝ! በል እስቲ ህሊናህ ያለህን ፍርድ በይንብኝ በል እባክህ ጥፋቱ ያንተ ነው ብለህ ጥፋቴን ቦታውን ጠቁመኝ እያለ ሲቃ እየተናነቀው ራሱን መቆጣጠር አቅቶት ድምጹ ሌሎችን እስኪረብሽ ድረስ ከፍ በማድረግ ትናንት ያገኘሁት ሣይሆን የጥንት ጓደኛው ያህል ስሜቱን መቆጣጠር እስኪሳነው ህመሙን ጭንቀቱን ተነፈሰልኝ፡፡

        ይኸውልህ ደረሰ ዛሬ ላይ ሆኜ ሳስብው የርሷ የባህሪ ለወጥ የጀመረው አንድ ቀን ድንገት ይሁን አስባበት አላውቅም ‹‹ታገባኛለህ? አለችኝ እውነቴን ለመናገር እርሷን ማግባት የኔ ሥራ እንጂ የርሷ ጭንቀት አልነበረም ምክንያቱም ወድጃታለሁና፡፡ ነገር ግን መዋሸት አልፈልግምና ሁሉን ነገር ዘርዝሬ ነገርኳት ደሞዜ ስንት እንደሆነ ከዚያ ላይ የተጣራ የሚደርሰኝን ለቤተሰብ የቤት ወጪ ሥንት እንደምሰጥ የዓባይ  ግድብ የቦንድ ግዢ……. ተቆራርጦ ሥንት እንደሚቀረኝ ነገርኳት ከተወሰነ ወራት በኋላ የዓባይም እንደሚያልቅ ነገሮችም ሲስተካከል እንደምንነጋገር ሆኖም  ግን የኔና የርሷ መጨረሻ አብሮ በትዳር እንደሆነና ዛሬ ግን ልዋሻት እንደማልፈልግ አጉል ቃል እንደማልገባ ነገሮችን አስተካክዬ እኔ ራሴ ልታገባኝ እንደምትፈልግ እንደምጠይቃት ነገርኳት የተወሰነ ቅሬታ አነበብኩባት ከኔ ጭንቀትና እውነት ውሸትና ቅሬታ ሽንገላ በሥሜት ‹‹አዎ አገባሻለሁ›› እንድላት ፈለገች ይሁን እንጂ የከፋ ነገር በመካከላችን አልነበረው የሆዷን እግዜር ይወቀው እንጂ እንዲያውም ብር ልላክልህ ትለኝ ሁሉ ነበር፡፡

        የኔ ፍቅር ከቀን ወደቀን እየጨመረ ሲመጣ በመካከላችንም የነበረው እንቅፋት የፍቅር ችግር ሳይሆን በኢኮኖሚ ራስን አለመቻል ስለነበር ወደያው አንድ ነገር ወሰንኩ ስራ ማፈላለግና የተሻለ ደመወዝ ተከፋይ መሆን እንዳለብኝ ምክንያቱም ጥሩ የስራ ልምደና የት/ት ደረጃ አለኝና የሚገርመው በወራት ውስጥ የምፈልገውን ሥራ ከእጥፍ በላይ በሆነ ወርኃዊ ደመወዝ ተቀጠርኩ ወደ ድሬደዋ የፍቅር አገር የመጣሁት ስራ ከመጀመሬ በፊት ይህንን የምስራች ለፍቅሬ ልነግራት ታገቢኛለሽ ወይ ብዬም የትዳር ጥያቄ ላቀርብላት፣ እመጣለሁ ብዬ ቃል የገባሁትንም ቃልኪዳኔን ለመፈጸም ለድርብ ድርብርብ ደስታ ነበር ጉዞዬ ከአ.አበባ ድሬደዋ ነገር ግን በድሬደዋ ሙቀት ውስ ፍቅራችን ለፍሬ እንደ ደረሰ ሰብል ታጭዶ ተወቅቶ ወደ ጎተራ ሳይገባ ውርጭ መታውና ልቤን ደግሞ የፍቅር ጦር አደማው ላይሻለኝ ላይጠገን ልቤ ተሰበረ ‹‹ ጉም ጨበጥኩልህ ሥቅሥቅ  ብሎ አለቀሰ፡፡ ግራ መጋባት በሚታይብኝ ሁኔታ ‹‹አይዞህ›› እያልኩ ለማጽናናት እንዳያለቅስም ‹‹አታልቅስ›› በማለት አባበልኩት፡፡

        ደረሰ ተወኝ እባክህ ለምን አላላቅስ ለምንስ አላነባ ምን ቀረኝ ፣ጌታዬኮ አብሬያት እንድኖር ከግራ ጎኔ አጥንት ከፍሎ የሰጠኝ ሴትን ነው፡ ታዲያ ሴቶች እንዲዘህ እንደጉም አልጨበጥ ካሉ  ወንድ ላግባ እንዴ?! ምን ለማለት ነው አታልቅስ የምትለኝ እያፅናናኽኝ እያበረታኸኝ ነው? ወይስ በቁስሌ  ላይ እንጨት እየቆሰቆስክበት ነው?

        እምባ ተናነቀኝ የወንድ ልጅ ሐዘን እና ጉዳት አሳዘነኝ እኔም የራሱን ጥያቄ መልሼ ራሴን ግን ለምን? አልኩት፤ታዲያ አሁን ምን እያደረክ ነው? በማት በጥያቄ መልክ ጨዋታ ለመቀየር ሞከርኩ ከሐዘኑ የማስወጣበትን መንገድ እየፈለኩ፡፡

        ‹‹አሁን ምን አደርጋለሁ እቅዴን ምኞቴን ተስፋዬን ውሃ ባለው መነሻዬን ራስ ሆቴል አድርጌ ዳቻቱ ሰፈር፣ መጋላ፣ ኮኔል ድልድይ፣ ከዚራ፣ ለገሃር፣ ሃምበር ዋን፣ ሃራር መውጫ፣ ታይዋን፣ ሳቢያን፣...ወዘተ እያልኩ ላይ ታች ሥል ውዬ ዛሬ ደግሞ ራስ ሆቴል አርፋለሁ፤ የከፋው (ግራ የገባው) ቱሪስቱ ታውቃለህ እንደዚያ ሆኛለሁ፡፡

        አይዞህ ታሪክ ይቀየራል ራስህን አትጉዳ በትዕግስት ነገሮችን በሙሉ መርምራቸው ደግ ሴቶች በሙሉ አንድ አይደለሙ ወላድ በድባብ ትሂድ እዛው አዲስ አበባ የአገርህን ልጅ ታፈቅራለህ አይዞህ!

        “ምን አልክ ፍቅር?! ፍቅር እንደገና ! ሴት ልጅን እንደገና ላምናት? ይገርምሃል አንድ ጓደኛዬ በሆነ ወቅት ስለ ሴት ልጅ ያለውን መጥፎ አመለካከት ተመልክቼ እንዲራራ መልካም አመለካከት እንዲኖረው ብዙ ጥረት አደርግ ነበርና ስለሴት እናትነት፡ እህትነት፡ሚስትነት፡ ወዘተ እያነሳሁ ብዙ ብዙ ነገር እለው ነበር ዛሬም አንተ ለምን እንደዚህ እንደምትለኝ ይገባኛል፡፡ አዎ የምትለውን በሙሉ ነች አምናለሁ ነገር ግን ያ! ጓደኛዬ እንዳለኝ ሴቶች የሚመቻቸው ከርህራሄ ይል ጭካኔ፣ ከፍቅር ይልቅ ጥላቻ፣ ከመግባባት ይልቅ ፀብና ክርክር፣ አብሮ ከመኖር መለያየት ይመቻቸዋል።ይኸም የመጣዉ ከጥቅም ፈላጊነታቸውና ራሳቸውን አብዝተው ከመውደዳቸው የሚመነጭ ይመስለኛል። ዛሬ ዛሬ እንደውም ከወንድ በተቃራኒ በሆኑ ቁጥር የሚወደዱና የሚፈለጉ እየመሰላቸው ሲሞላቀቁ ይታያል፡ እውነታው ግን ይህ አይደለም በተቃራኒው ነው ስለዚህ አያስፈልጉኝም፡፡››

        ‹‹እስኪ የመለያየታችሁ፡ ይቅርታ የመቀያየማችሁ ዓብይ ጉዳይ ምንድን ነው ብለህ ታስባለህ?

        ‹‹ግልፅ ነውኮ ያኔ ነገሮች ባልተስተካከሉበት ወቅት ለርሷ ወቅታዊ ላልሆነ አጣዳፊ ጥያቄ አገባሻለሁ የሚል የውሸት ተስፋ ስላልሰጠኋት ነው፤ እስኪ ተመልከታት ይህቺን ሴት እኔ ያኔ ብዋሻት ዛሬ ድረስ ከኔ ጋር ነች፡ አሁን ሥመጣ በደስታ ትቀበለኛለች አዲስ አበባም ትመጣ ነበር ያፈለገንንም ነገር እናደርጋለን ደግሞ ስለ መጋባት አናነሳም በቃ! ምናልባት ‹ቆይተን መቼ ነው ታዲያ የሰርጋችን ቀን?› ትለኝ ይሆናል፡፡››

        እሷም ጥያቄዋ ስህተት ያለበት አይመስለኝም እውነትዋን ነው የማታገባት ከሆነ ለምን ጊዜዋን ታባክናለች?

        ‹‹እኔስ ምንድን ነኝ ዝም ብዬ ጊዜዬን የማባክነው የወንድ ልጅ ዕድሜ እና የዕባብ ዕድሜ አንድ ነው ያለው ማን ነው? የኛም ዕድሜ ይሄዳልኮ እንደ ሴቶቹ ባይሆንም፤ እኔ ደግሞ ራሴን እፈልገዋለሁ ዝም ብዬ አልንዘላዘልም፡፡ የማላገባትን የእኔ ያልሆነችዋን ሴት አልፈልጋትም ወንድ አዳሪ አይደለሁምኮ፡፡

ቀጣይ ጊዜህን ታድያ እንዴት ታሳልፋለህ ያለሴት መኖር ይከብዳል፡ ለምን አላስታርቃችሁም?

አመስግናልሁ፡ግን አሁን የማሰቢያ ጊዜ ነዉ የምፈልገዉ ዳግም የምሳሳትበት ጊዜ አልፈልግም፡፡…ለወንዱም ለሴቱም መልካም ዘመን እና ጣፋጭ የፍቅር ጊዜ እመኝላቸዋለሁ። እነሆ ላንተም መልካም መዝናኛ፡፡

አሜን ብዬ ምርቃት ከተቀበልኩ በሁላ ይጠቅም ይሄናል በማለት እንዲህ አስፍራለሁ፡፡

(ገጠመን የምትሉትን ፍቅር በfacebook ላኩልኝ እኔም እንዲህ ለሰፊዉ ህዝብ ጥቅም በምስጢር አቀርበዋለሁ።)

ክፍል 3 በእኛዉ ገጠመኝ እና ታሪክ ፈጣሪ ካደረሰን እናንተም ከላካችሁልኝ እንገናኛለን፡ቸር ይግጠመን።

ማክሰኞ 9 ኦክቶበር 2012

ቅዱሣት መካናት በፎቶግራፍ

  ቁልቢ ገብርኤል
                                                                        ሀረር መድኃኒዓለም
አዲስዓለም ማርያም
 

ቅዳሜ 29 ሴፕቴምበር 2012

መልካም በዓል


በመላዉ ዓለም ለምትገኙ ኢትዮጵያን እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ  በሰላም አደረሳችሁ፡፡በጦማሩ ላይ ስለ ጦማሪው ያላችሁን አስተያየት በ e-mail:-lovelydere@gmail.com መላክ ወይም በፖስታ ቁጥር 25476 አዲስ አበባ ደረሰ ረታ በማለት መላክ ይቻላል፡፡አመሰግናለሁ፡፡ለተጨማሪ ንባብ
www.deressereta.blogspot.com ይጠቀሙ፡፡


ዓርብ 28 ሴፕቴምበር 2012

“የምናብ ለውጥ”


ይሕ ፅሑፍ ጳጉሜ 3/2004 ዓ.ም. የተጻፈ በመሆኑ የተፈጠሩ ስሕተቶች ግምት ዉስጥ ይግባልኝ!
የምናብ ለውጥ
ክቡር የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ በተጠባባቂነት  የሚሰሩበትን የጠቅላይ  ሚኒስተርነት በትረ ሥልጣን በቃለ መሐላ ሙሉ በሙሉ ሲረከቡ ያደርጉታል ተብሎ ከሚጠበቀው ንግግር መካከል አንዱ፡-
ክቡር የኢፌዴሪ መንግሥት ኘሬዜዳንት አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ክቡር የኤፌዴሪ መንግሥት የተወካዮች ምከር ቤት አፈ ጉባኤ  አቶ አባዱላ ገመዳ ክቡራት ሚኒስተሮችና አምባሰደሮች እንዲሁም የተወካዮች  ምክር ቤት አባላት ክቡራን  ጥሪ የተደረገላችሁ የውጭ አገር አምባሳደሮች ኮር ዲኘሎማቶች የሐይማኖት   መሪዎች የአገር ሽማግሌዎች የተቃዎሚ ፓርቲ  ተወካዮች ከሁሉም በላይ እጅግ የማከብርህና  የምወድህ  ልታዘዝህና ላገለግልህ በዛሬዋ ዕለት በቃለ መሐላ አረጋግጨ በትረ ሥልጣኑን የተረከብኩህ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፡፡
በየአላችሁበት  የእግዜአብሔር ሠላም ይብዛላችሁ፡ ጌታ እግዚአብሔር ይባርካችሁ፡ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና እኛ  ህዝቦቿን ይባርከን!

Yes We Can Change!
Yes we can!
Yes we need change !

“ የኢትዮጵያ ህዝብ  ሆይ አዎ መለወጥ እንችላለን! መለወጥ ያስፈልገናል፡፡”
 የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ለብዙ ዘመን ለረጅም  ወራት ሥትረገጥ ሥትጨቆን  ብትኖርም ኢህአዴግ የድልን ካባ ከተጐናፀፈ ማግሥት ሥትናፍቅ  የኖረከውን ያንን ነፃነት፣ ዕድገት ፣ ብልፅግና  ሰላም……..ለማምጣት ድፍን  ሁለት ዓሥርት ዓመታት  አልፈውታል፡፡  ይህንንም ግሥጋሴ በፅናትና በትጋት ሲመሩት የነበሩት  ክቡር ጠቅላይ  ሚንስትራችንን በሞት ቢለዩንም ይኸውና ዛሬ በህይወት ዘመናቸው የቀረፁኝ የመንፈስ ልጃቸው ተተክቼ በትረ ሥልጣኑን ተረክቤአለሁ ፣ ቃል የምገባልህ የተጀመረውን ማስቀጠል  እንደምንችልና ለውጥ ማምጣት እንደምንችል ነው፡፡
     ክብራትና ክቡራን ሚኒሰተሮች፣ የፓርላማ አባላት  በየደረጃችሁ  የመንግሥት ባለሥልጣናት  ጥያቄ አለን የመለወጥ ዓላማ አለን ወይስ ዓላማችን ምንድን  ነው  መለወጥ መለወጥ  ሥላችሁ /አንዴ ለ ን አጥብቃችሁ እንዴ አላልታችሁ  ይሁንልኝ/ መቀየር /ማሳደግ/ ቀ ን አጥብቋት መቀየር /ማደግ/ / ቀ ን ላላ አድርጓት /ያለብን ይመስልኛል ይመስለኛል አይሰራም  መቀየር ወይም መቀየር አለብን፡፡
ዓለማችን መለወጥ ማስተካከል ወይም ማስተካከለ ካልሆነ  የእኔ  የለውጥ ሂደት በእናንተ የመለወጥና/ የመለወጥ አስተሳሰብ ካልታጀበ የእኔ  ዕቅድ የእናንተም የጋራችን ካልሆነ  የእኔ የለውጥ ሂደት ጎምዛዛ እና ደብዛዛ  ይሆናል፡፡ ለዘመናት  የእኛን ለውጥ ሲጠብቅ የኖረው መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተስፋ መና ይሆናል የእኛም ዕጣ ፈንታ በታሪክ ተወቃሾች መሆን ነው፡፡
ክብራት ሚንስተሮች ክቡራን የፓርላማ አባላት ለውጥን  ለማምጣት የምንችለው  ሰውን  በማምጣት ሰውን በመቀያየር ብቻ አይደለም ፓሊሲዎቻችን  አፈፃፀምቻችንንም መፈተሽና መቀየር ግድ ይላል የማንቀይረው ሰው የማንቀይረው ፓሊሲ የለም ሁሉም ይቀየራለ አስፈላጊ  ሆኖ ከተገኘ እኔም እቀየራለሁ  መንግሥታችንም ይቀየራል፡፡  የሄድንበት መንገድ ትክክል አይደለም አያዋጣም ከእንግዲህ የኢትዮጵያ ህዝብ ተቃዋሚ ፓርቲዎች  ሣይቀሩ በሚያመጡት መልካም ኃሳብ ፈትሸንና አስተካክለን  እንጓዛለን ማለት አለብን፡፡
እንደ እህአዴግም የተጓዝንበት መንግድ ትክክለ ነወይ እንደ መንግሥትስ የቀየስነው ዓላማ ጠንካራ ነው አፈፃፀማችንስ እንዴት ነው ብለን ራሳችንን እስከ ታችኛይቱ የቀበሌ እና የጎጥ ጽ/ቤት ድረስ ልንፈትሽ አገራዊና ህብረተሰበአዊ ግዴታችን ነው ደካማ ጐናችንን ማመኑ ጥፋታችንን መረዳቱ የለውጥ ሂደታችን አንዱ አካል ነውና፡፡ ግትርንት አይሰራመ ለአገራችን ለኢትዮጵያ  እኔ ብቻ አውቅለታለሁ የምንልበት ዘመን አብቅቷል የበረሃ  ታጋይነት ብቻ በቂ አይደለም ከፈቃደ ሥጋችንና ከያዝነው የዛፍ ላይ እንቅልፍ ሥልጣናችን  ጋር ልንታገል ግድ ነው፡፡
የማከብራችሁ የመንግሥት  ባለሥልጣናትና የምወዳችሁ የኢትዮጵያ ህዝቦች ሆይ እኔ ዛሬ ከፊታችሁ ቆ ሜ ቃለ መሐላ የፈፀምኩር ኩራት አይደለም የሚሰማኝ ሥጋት እንጂ ይህን ሥጋቴን ዳግመ ወደኩራት መለወጥ የምችለው ከፊታችን ባስቀመጥንው ሶስት ዓመታት ውስጥ በሥራ እና በለውጥ ነውና እናንተን ከእኔ ጋር በመሆን አብረን ከእርሱ ጋር እየሠራን እንየው እንለወጥ ልትሉ ይገባል፡፡
መንግሥት መሥርተን በጋራ የምንሠራ በተለያየ የድርጅት አባልነት ያለን አለን በአጋር ድርጅትም ታቅፍችሁ ያላችሁ ሳስገነዘባችሁ የምፈልገው አንድ ጥብቅ ጉዳይ አለ፡፡  ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚናገሩትን ከእንግዲህ ልንሠማ ቦታም ልንሠጣቸው ግድ ይለናል ልንለውጣት ለቆምንላት አገራችን ኢትዮጵያ  እንርሱም እንደዜጋም ይሁን እንደተቃዋሚ የለው  አጋሮቸችን  ቻውና፡፡ ወሀትመ ለአገር ለውጥና እድገት ለሠዎች ልጆች ሠላምና እኩልነት የሚሠጕ የካበተ ልምድ  ካላቸወ ተለውጠው ከመጡ የደርግ ባለሥልጣናት ሣይቀር  በህይት ካሉ በንጉውም ዘመን ያሉ ካሉ እንቀበላለን”፡ ያቋቋምነው ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ምህደሩ እዚህ ድረስ ሠፈና ጥልቅ ነው፡፡
የተከበራችሁ የምክር ቤት አባላት ባለፋት የሁለት ዓመት የዚህ የምክር ቤት የሥራ ዘመናችን የኢትዮጵያ  ህዝብ እና ሚዲያዎች በሥራችን ላይ ምስጋና ነው ወይስ ወቀሳ ነው የሚያቀርቡት ክስ ነው ወይስ እርካታ ነው ያላቸው ምንድን ነው እየተሰማ ያለው ሰማንያ ሚሊዮን የኢትዮጵያን ህዝብ እንደመወከላችን መንግሥታችን ዲሞክራሲያዊ እንደ መሆኑ መጣን ምን መረጃ አለን እኛስ ምን መስራታችንን ነኁወ የምናውቀው እንደ አንደ ግለሰብ እንደ አንድ ኢትዮጵያዋና የምክር ቤት አባልነቴ ምን አስተዋፅኦ አድርጌአለሁ ብለን ራሳችንን ፈትሸናል ይህ ቀን ግን ራሳችንን ቆም ብለን የምንፈትቨበት ቀን ነው፡፡ ይቅርታ አድርጉልኝና የምክር ፀበት አባላት በሙሉ አንድ ግዜ ከመቀመጫችሁ ብድግ በሉልኝ አመሰግናለሁ በዚያው እስኪ  እጃችሁን ወደ ኪሶቻችሁና ወደ ገንዘብ ቦርሳችሁ ከታችሁ
ተመልከቷቸው /ጠቅላይ ሚኒስትሩም እጃቸውን ወደ ኪሳቸወ ከተቱ የገንዘብ በርሳቸውንም  ፈተሹ የማን ገንዘብ ነው ኪሶቻችን ውስጥ ያሉት  መልስልኝ ጉርምርምታ ነገሰ በአዳራሹ  ጓዳች  ፀጠታ መልሰን እኔ እመለሰዋለሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው የኢትዮጵያ  ሃብት ነው ለመሆነ ምን ያህል ሰርተን ነው ይህን ያህል የተከፈለን የፀዳ የላባችን ውጤት ብቻ ነው ኪሳችን ውስጥ ያለው በየግለ ሥማችን የተፃፋ የገንዘብ ማዘዥ ቼኮች የሉም በኪሳችንና በቤታችን  ጐበዝ በቃ አካሄዳችንን እንገምግም ችግር ካለብን በቃኝ ተነቅቶብኛል የጀመርኩር መንገድ አያስቀጠልኝም በማለት የለውጡን ጉዳና  ለመቀላቀል የኢትዮጵያ  ህዝብ ይቅርታ እንጠይቅ በአገሪቷ ላይም እርቀ ሰላም እናውርድ፡፡
ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ የፓለቲካ ድርጅቶች የሃይማኖት ተቋማት፣………ወዘተ ሁላችሁመ አንድ የጥሪ መልዕክት አለን እንደማመጥ መስማት ወይመ ማዳመጥ ለሰው ልጅ ከሚያስፈልጉት መሠረታዊ ነገሮች ውስጥ አንድ ነውና፡፡መደማመጥ ለመንግሥታችን ፋይዳው  ከዚህ በላይ ነው ለለውጥ የተነሳ ትውልድ አዳማጭ ካጣ ልፋቱ  በጠቅላላ ዋጋ ቢስ ይሆናል ስለዚህ ለዚህ ለውጥ  መሳካት መዳመጥም ሆነ ማዳመጥ ትልቁን  ሥፍራ ይይዛልና እንደማመጥ  ሰዎች በየእመነታቸው ወደ ፈጠረን በፀሎት የምንጨኸው የፈጠርን ይሰማናል ያዳምጠናል መልስም ይሰጠናል ያሰብነውን ያለምነውን ያቀድነውን ያሳካልናል ብለንኮ ነዉ ታዲያ ትልቅ ራዕይ ሰንቀን ረጅሙን ጐዳና ከፈታችን አስቀምጠን ሳንደማመጥ እንዴት ይሆናል፡፡
ምንም እንኳን ለውጣቸው እስከዚህም ቢሆን የድሮ ነገሥታት (መሪዎች) የህዝባቸው የልብ ትርታ ለማዳመጥ ‘’እረኛው ምን ይላል’’ እሰከ ማለት ታች ድረስ  ወረደው ያዳምጡ ነበር፡፡  ታዲያ መደማመጥ ክፉ ነገር ከሌለው ለዚያውም በመረጃ መራብ  ዓለም አንድ መንደር በሆነችበት ዘመን ለምን አንደማመጥም? መዳማመጥ አለብን፡፡ አለቃ ምን ይላል? ብቻ ሣይሆን ወደታች በመውረድ ሠራተኛው፣ ህዝቡ፣ ደጋፊው፣ ተቃዎሚው ምን ይላል? ማለት ይገባል፡፡ ህዝቡ ዝም ካለ አደጋ ላይ ነንና ባለፋት ሥርዓት እንዲሁም በኛም  ዘመን የሚናገሩ ብዙዎች  የሚያዳምጡ ጥቂቶች በመሆኑ መፍትሔ እና   ለውጥ ሣይመጣ ቀርቷል፡ ዛሬ ግን ያ ዘመን  ይብቃ! መስማት (ማዳመጥ) የመፍትሔው ዋነኛ ቁልፍ ነውና የተከበራችሁ ሚኒስተሮች ማዳመጥ ከማይችሉ መሪዎች ጋር የሠራ ሠራተኛ የመደማመጥን ባህል ማዳበር አይችልምና መደማመጥን ባህላችን  እናድርግ ብዙ ሥናዳምጥ ብዙ መረጃ  ይኖረናልና፡፡
     የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ህዝቦችና የመንግሥት ባለሥልጣናት በእርግጠኝነት የምነግራችሁ ይብዛም ይነስም ይህቺን አገር በድለናታል፣ ተበዳይ ደግሞ ካሣ  ያስፈልገዋልና ይህ ጊዜ ምንም አጭር ቢሆንም ባለን አጭር ጊዜ  አገራችንንና ህዝባችንን  የምንክስበት እንጂ የምንከስበት ሰዓት ላይ አይደለም ያለነው ምን ያህል ነው ያጠፋሁት ሣይሆን  ጥፋቱ መኖሩን ማመን የጥፋቱ ምክንያት እኛው መሆናችንን ማመን በራሱ አንድ የለውጥ መጀመሪያ ነው ሌላው ዓብይ ጉዳይ የሚያጠፋትን ሠዎች ለመቅጣት ሥንል የምንዘረጋቸው መንግዶች በአገራችን ላይ ቂም እና በቀልን እንዳያሠፍኑ የተቀጣው ሠው ተምሮ ወደ ማኀበረሰቡ ተቀላቅሎ  ልማትን እና የዕድገቱን ለውጥ የሚያፈጥንበትን መንገድ ልንቀይስ   ይገባል፡፡ በዘመናችን ሠዎች የሚቀጡበት የእስር ቤት ግንባታዎችን ከማስፋፋትና የሌለንን የሠው ኃይል ለዓመታት  በአንድ ቦታ  ያለ ጥቅም ከማዋል  አስቀድመን ሠዎችን ከጥፋት ማራቁ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው ስለዚህ በዚህ የሶስት ዓመት የሥራ ዘመናችን እንዚህ እስር ቤቶች  የልማት ሀይሎች መፍለቂያ ማድረግ አንዱና ዋነኛ ሥራችን ይሆናል ሌላው አገራችን በፓለቲካ ፓርቲ መሪዎች ብቻ የምትመራ ሣትሆን በፍቅር በዕድገት እና  በለውጥ ጐዳና የምንመራት ኢትዮጵያ መሆን አለባት፡፡
     ወገኔ የኢትዮጵያ  ህዝብ ሆይ ተከፋፍሎና ተቃቅሮ መኖር ከዚህ ቀደም በቅርበት ያየናቸው የአፍሪካ ህዝቦች ታሪክ  ብዙ ነገር ያስተምረናል ብዬ አስባለሁ የተደረጉት ክፋ ድርጊትና ብቀላዎች  አህጉሪቷን ለልማት  አላነሳሳትም ከጥፋትና  ከረኃብ፣ ከበሽታና ፣ ከእርሰ ብርስ  ጦርነትና ኃላቀርንት፣ ከትውልድ እልቂትና ከመበታተን / ከስደት/ አልታደጋትምና ከዚህ ክፋ  አጋጣሚዎች የመለያየትንና የክፋትን ነገር ልንማርበት ይገባል፡፡ ከቂም እና ከበቀል ይልቅ  ታሪካችንን በዕርቅ የምንቀይር ታሪክ ሠሪዎች  እንሁን፡፡  ትናንት  የተሠራውን ጥፋት እና መጥፎ ታሪክ እየዘረዘርን  የአጥፊውን ወገን በክፋ ዓይን ማየት ይቅር መካሰስ የትኛውን አገር ገነባ? የየትኛውን አገር ኢኮኖሚ  አሳደገ?
     ትናንትናን  መለወጥ ባይቻል ከትናንት መማር ግን ይቻላል  አይደል የሚባለው ከተስማማንና በግልጽ ከተነጋገርን በአንድነት እና  በቁርጠኝነት ለእምዬ ኢትዮጵያና ህዝቧ ለህዝቧ ታሪክ ለመሥራት ዝግጁ ከሆንን   ነገሮችን ሁሉ እንደምንፈልገው ማድረግ እንችላለን ታሪክ ለመቀየር ክፋ ነገሮችን  ወደ በጐ ለመገልበጥ የተነሳን ከሆንን ህዝባችንና የኢትዮጵያ  አምላክ እግዚአብሔር ከጐናችን ሆኖ  ብርታትና ሞገስ ይሆነናል፡፡  በትናንት መጥፎ ታሪካችን  ላይ  ሥንጣላ ሥንጨቃጨቅ ጥሩው ቀን ዛሬ ግን እንዳያልፍብን ጥሬዬን አቀርባለሁ፡፡
      ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝቦችን  ብሔር  ብሔረሰቦች ዛሬ የምንተራረምበትና  ጥሩ ሥራ ለመሥራት  የምንመካከርበት ቆርጠን የምንነሳበትና ቃል  የምንገባበት የለውጥ ብሥራት ዕለታችን ናት ፣ ከመላው የእትዮጵያ ህዝቦች ብሔር ብሔረሰቦች ልቡና ልትጠፋ  የማትችል ተከባብረንና ተዋደን  ልንኖርበት ቃል የምንገባበት  የደስታ ቀን ናት ተራርመን ጥሩ ሥራ መሥራት የማንችል ዜጐች ካልሆንን  እንደ ህዝብ ብዛታችን እና ብዙ  የብሔር ብሔረሰብ ሥብጥር ውጤት እንደመሆናችንን  መጠን ትናንት የነበሩት  ካጠፋት፣ ሌሎችም የአፍሪካ አገራት ላይ ከጠፋው ጥፋትና ከደረሰው  ውድቀት  የከፋ  ነገር ያጋጥመናል የበለጠ ነገርም ልናጠፋ እንችላለን፡፡ በውኑ የትናንትናዎቹን በምንወቅሳቸው ሚዛን ብንመዘን እኛ  ምን የተሻለ  ሥራ  ሠርተናል እነርሱን ያጋጣማቸው ነገሮች ቢያጋጥሙን እነርሱ ካጠፋት የተሻለ  ሥራ እንደምንሠራ ምን ማረጋገጫ አለን በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ሥናጠፋ ታግሶን ስናለማ አጋራችን በመሆን ከጐናችን ላልተለየ ህዝባችን ምስጋናዬና አክብሮቴ ላቅ ያለ ነው፡፡
    በመጨረሻም የተከበሩ የኢፌዴሪ ኘሬዘዳንት፣ የተከበሩ የምክር ቤቱ አፈ-ጉባኤ እና የተከበራችሁ የምክር ቤት አባላትና የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ ባለፋት ሁለት ዓመታት የተጀመሩትን የልማት ሥራዎች ማስቀጠል  እንዳለብንና ሌሎችንም ሥራዎች ማቀድና መተግበር እንዳለብን ላሳስብ እወዳለሁ፡፡  ይልቁንም ታላቁ የህዳሴ ግድብ ከዳር ማድረስ እንዳለብን በአጽንኦት  አሳስባለሁ፡፡  ከዚህ ጋር ተያይዞ ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ እምቅ እውቀቱን ይዞ  በተለያየ አጋጣሚ ጉልበቱን ጭምር  ይዞ እንደ ዓባይ ለሌላው ዓለም ሲሳይ  የሚሆነውን ህዝባችንን ልንታደገው እንደሚገባና እንደ ወንዛችን ዓባይ ሁሉ ከአባይ ወንዝ በላይ ጥቅም ያለውን ህዝባችንን በአንድነት ልንገድበው ይገባል፡፡  የዓባይ ወንዝ በገንዘብና በጉልበት ሊገደብ  ይችላል ህብረተሰብ ግን በጉልበት አይገደብም በጥበብ እና በፍቅር እንጂ  ስለዚህ አደራ የምለው በጥበብና በፍቅር በመከባበርና በመተባበር በስደት ላይ ያለውን በመሰደድ  ላይ ያለውን እምቅ ሐብት  ህዝባችንን ለእምዬ ኢትዮጵያ እናውለው እንገድበው!!!
በእኔ በኩል የሥደት ምክንያት የሆነውን በነፃነት የመኖር መሠረታዊ  ነገሮችን፣ የሚዲያ እና የነፃ ኘሬስ ነፃነትን፣ የመንግሥትን በሀይማኖቶች ጣልቃ  ገብነት ገለልተኛ መሆንና እና ሌሎችን በራሴና ከምክር ቤቱ አባላት ጋር ታምኜ ልሰራ እና ላገለግላችሁ  እንድትሰሩ ላመቻችላችሁ ቃለ እገባለሁ ፡፡(ንግግሬን እዚህ ላይ አበቃለሁ በክብር ለህዝብ ጥቅም  ከድል በኃላ ለተሰውት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን መለስ ዜናዊ ከመቀመጫችን ተነስትን  በድጋሚ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት እናድርግ፣ አመሠግናለሁ፡፡)

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !
ኢትዮጵያለዘለዓለምትኑር!
ክቡር ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለ እንን ለዚህ አበቃዎት!

 

ሐሙስ 20 ሴፕቴምበር 2012

አንጥፋ



          ሁላችንም ወደዛዉ ነን!
        በጉብዝናችን ሰአት ከቤቱ አንጥፋ፡፡
God bless Ethiopia!

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...