ረቡዕ 24 ጃንዋሪ 2024

"ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ"

 

"ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ" ገላትያ 6÷14

ይህን መልእክት የጻፈልን ከሐዋርያት ጋር ለሐዋርያነት ያልተመረጠው ይልቁን ሐዋርያትን በማሳደድ የሚተባበረው ከሐዋርያት መካከል እንደ አንዱ የሚቆጠረው ቅዱስ ጳውሎስ ነው።

መልዕክቱ የተጻፈው በገላትያ ቤተክርስቲያን ለሚገኙ ምዕመናን ነው። ገላትያ፦ ቱርክ ውስጥ የምትገኝ አንድ አውራጃ ነች።

ቱርክ ቅዱስ ጳውሎስ ለወንጌል አገልግሎት ሲሰማራ ካገኛቸው ከተሞች አንዷ ነች።

በገላትያ የሚገኙ አብያተክርስቲያናት በቅዱስ ጳውሎስ የተመሰረቱ ናቸው።

የገላትያ ሰዎች ቅዱስ ጳውሎስ አስተምሯቸው ከሄደ በኋላ ካስተማራቸው ትምህርት ቢያፈገፍጉም (ስለግርዘት ተምረው ነበረ ያፈገፈጉት) በመጨረሻም ተጸጽተው ተመልሰዋል።

ይህ መልዕክት የመጀመሪያው የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት እንዳልሆነ ይነገራል። መልዕክቱ ጠጠር ያለ እና ከበድ ያለ መልእክት ነው።

የመነሻ ቃላችን ሙሉው እንዲህ ይላል።

 

ቃና ዘገሊላ

 ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ በጥምቀት በዓል ማግስት(ጥር 12) ቀን የቃና ዘገሊላ በዓል ይከበራል፡፡ ይህ በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ ያለው በዓል ነው፡፡ በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው፡፡



የቃና ዘገሊላ ጥንተ ነገሩ ወይም ታሪኩ የተፈፀመው የካቲት 23 ቀን ነው፡፡ ነገር ግን አባቶቻችን የውኃን በዓል ከውኃ በዓል ጋር ለማክበር ብለው የየካቲቱን በዓል ወደ ጥር 12 አምጥተውታል፡፡ ይህም ውኃ ወደ ወይን የተለወጠበትን በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ለማስተሣሠር ለማስኬድ ነው፡፡ በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር 12 ቀን ይከበራል፡፡

በቃና ዘገሊላ ምን ተፈፀመ?

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...