ማክሰኞ 31 ዲሴምበር 2019

"ዳንኤልን" እንኳን ሰው ሠይጣንም ይፈራዋል ( ክፍል አንድ )

"ዳንኤልን" እንኳን ሰው ሠይጣንም ይፈራዋል
12 ምእራፍ እያንዳንዳቸው ትንሹ 13 ቁጥር ሲኖረው ትልቁ 49 ቁጥር አለው። በአማካይ አንድ ምእራፍ 30 ቁጥር ይኖረዋል።
የመጽሐፉ ክፍል "የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአቄም በነገሠ በሶስተኛው አመት የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ከበባት።" ብሎ ይጀምርና። " አንተ ግን እስከ ፍጻሜው ድረስ ሂድ አንተም ታርፋለህ: በቀኑም መጨረሻ በእጣ ክፍልህ ትቆማለህ።" በማለት ይዘጋዋል።
የሥሙ ትርጓሜ " እግዚአብሔር ፈራጅ ነው " ማለት ሲሆን የተረጎማቸው ሕልሞችና ያያቸውን ራእዮች ብዙ ምሥጢር ያለባቸው ከመሆኑ የተነሣ ብዙዎች አይስማሙበትም።
አላማው እኔ ልግነን፣ ልታወቅ፣ ብዙ ተከታዮች ይኑሩኝ፣ አድናቆትን ላትርፍ፣ ወዘተ ... አይደለም። እግዚአብሔር እና ሕዝቡ እንደሚያሸንፍ ለመግለጥ እንጂ።
የመጽሐፉ ክፍሎች በአሥር የተከፈሉ ሲሆኑ በአብዛኛው የሚያወሩት ስለ ምርኮ፣ ሕልም፣ ትርጉም፣ አራት መንግሥት፣ ጦርነት፣ ስለ እግዚአብሔርም ሕዝብ መከራ ... ወዘተ ነው።
"ዳንኤልን" እንኳን ሰው ሠይጣንም ይፈራዋል::
በይፋ ተጀመረ።
ይቆየን።

ከትናንት እስከ ዛሬ …

በነገራችን ላይ   ከ ፈረንጆቹ Thursday, March 22, 2012 እስከ ዛሬይቱ ቀን ድረስ ………. 


https://deressereta.blogspot.com/

የደረሰ ረታ እይታዎች የፀሐፊዉ ያላሰለሰ ስንፍና እንዳለ ሆኖ በአገራት ኢትዮጵያና አሜሪካ እንደ ቅደም ተከተላቸዉ ብዙ አንባቢያን ያሉበት ሲሆን በመቀጠል ኬንያ፣ ሩሲያ እና ኢንዶኔዥያ ከ1 እስከ 3 ያለዉን ተራ ይይዛሉ፡፡
ከሚለጠፉት ፅሑፎች ደግሞ ትልቁን የቀዳሚነት ድርሻ የያዘዉ ፍቅር በፌስቡክ ክፍል ሁለት ሲሆን አጋጣሚ ክፍል አራት እና ለመጪዉ ትዉልድ ልማትን እንጂ ልመናን አናወርስም የሚሉት ሁለተኛ እና ሶስተኝነትን ይይዛሉ፤ እኔን በስነ ፅሑፍ ዘመኔ እጅግ ዋጋ ያስከፈለኝ እና በወቅቱ ከ1500 በላይ ኢ-ሜይል የተቀበልኩበት እና አንባቢ ያገኘዉ ብዙ ጊዜም ሲመራ የቆየዉ ዋጋ የሚያስከፍሉ ጥፋቶች

ሰኞ 16 ዲሴምበር 2019

የጊዜ አጠቃቀም


የጊዜ አጠቃቀም


መግቢያ

ስኬታማ የጊዜ አጠቃቀም ያዳበረ ሰራተኛም ሆነ ግለሰብ ጊዜዉን በመርሃግብር እና በዕቅድ ይመራል፤ ይህ ሰዉ ህይወቱን የሚመራዉ በዕድል ሳይሆን ራሱ ነዉ፡፡ ስለዚህ ይህንን ዶክመንት ማዘጋጀት ግድ ሆኗል፡፡

ጊዜ -

በቀን 24 ሰዓት

በሳምንት 7 ቀን

በወር 30 ቀን

በዓመት 52 ሳምንት/ 365 ቀናት/ ብለን የምንጠራዉ ማለት ነዉ፤

ጊዜ ከሁሉ ነገር በላይ እጅግ የሚያስፈልገን ነገር ሆኖ ሳለ ከሁሉ ነገር በላይ በተበላሸ ሁኔታ የምንጠቀምበት ነገር ነዉ፤

ዊሊያም ፔን

                                    ዓላማ -

v የተቋማትን ፣አልያም የአገራችንን፣ ከዚያም አልፎ የየራሳችንን፣ ወዘተ … “የተለጠጠእቅድ ለማሳካት ዋነኛ ሃብት ጊዜ በመሆኑ ጊዜያችንን በመጠቀም ዉጤትን እንድናመጣ ግብን እንድናሳካ ግንዛቤ ለመፍጠር ነዉ፡፡


 የጊዜ አስፈላጊነት (ጥቅም)


Ø  ለመዉጣት ለመግባታችን የምንጠቀምበት

Ø  በመዉጣት በመግባታችን ዉስጥ የምናከናዉናቸዉን ነገሮች የምንፈፅምበት መሣሪያ

የአንድ ዓመት ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ክፍሉን የደገመን ተማሪ ጠይቀዉ

 የአንድን ሰዓት ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ለመገናኘት የተቀጣጠሩ ትኩስ ፍቅረኞችን ጠይቃቸዉ

የአንድን ደቂቃ ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ አዉቶቡስ ለትንሽ ያመለጠዉን ሰዉ ጠይቀዉ

v  ያለ በቂ ምክንያት፣ ከአቅማችን በታች በሆነ ጉዳይ ከሥራ ላይ የቀረንባቸዉ ቀናት ምን ያህል ግባችን ላይ ተፅዕኖ እንደፈጠሩ እንመልከት፤

የአንድን ሰከንድ ዋጋ ለማወቅ ከፈለግህ ከአደጋ ለጥቂት ያመለጠን ሰዉ ጠይቀዉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...