በአንድም በሌላም እንናገራለን:ጆሮ ያለዉ ይስማ:ልብ ያለዉ ልብ ይበል፡፡ የታዘብነዉን የምንናገርበት፣ የምናዉቀዉን ለትምህርት እና ለእርምት የምናዉልበት ከወገንተኝነት ነፃ የሆነ መድረክ ነዉ፤ …ሁሌም ቢሆን አስተያየቶችን እና መልዕክቶችን ለመቀበል ዝግጁ ነን፡፡
ረቡዕ 22 ኖቬምበር 2017
የደረሰ ረታ እይታዎች Deresse Reta's Views : የህይወት ታላቁ ፈተና “ጠላትህን ዉደድ”
የደረሰ ረታ እይታዎች Deresse Reta's Views : የህይወት ታላቁ ፈተና “ጠላትህን ዉደድ”: ክርስቲያን ሆንን አልሆንን፣ወደድንም ጠላንም፣በየትኛዉም የእምነት አስተምህሮ ዉስጥ ብንሆንም በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርተ ወንጌል ዉስጥ ለማንኛዉም የሰዉ ልጅ ጥሩ የመሆን ፍላጎት ሊሆን ከወደ...
ረቡዕ 8 ኖቬምበር 2017
ትዳር ክፍል 3
"ሰዉ
እናቱንና አባቱን ይተዋል፤ … " ባል ከሚስቱ ሚስትም ከባሏ ጋር ይተባበራሉ ሁለቱም አንድ ስጋ ናቸዉና፡፡ በትዳር ዓለም
ዉስጥ በባህልም በሃይማኖትም የምንስተዉ ስህተት ይህ ነዉ አንድ አለመሆናችን አለመተባበራችን፡፡ ትዳር አዲስ አለም መመስረት እንደመሆኑ
መጠን ሁሉ ከአዲስ መንደር ባልተናነሰ መልኩ ብዙ መሟላት ያለባቸዉ የህይወት መሰረተ ልማቶች አሉ፡፡ እስካልተሟላ ድረስ ችግሮች
መኖራቸዉ አይቀሬ ነዉ፡፡ ወደ አንድ የሚያመጣ የፍቅር መንገድ፣ ቁጣን የሚያበርድ የትዕግስት ዉሃ፣ ብዥታን የሚያጠፋ የመተማመን
ብርሃን (መብራት)፣ አረፍተ ዘመን እስኪገታን ስንቅ የሚሆን የፍቅር ምግብ፣ አንዳችን ለአንዳችን መከታ ሆነን የምንኖርበት የተስፋ
መጠለያ፣
… ወዘተ ግድ ያስፈልጉናል፤ ይህን ጊዜ ሰዉ እናት እና አባቱን ይተዋል፡፡
ባል/ሚስት
ይህን መሰረተ ልማት (ትዳር) ሲያጡ የፍቅር ረሃብ ለማስታገስ እናታቸዉ ጋር፣ ተስፋ በማጣት መከታ ወደ ሆነ አባት መሄድ ግድ ይሆናል፡፡
ስለዚህ ለነዚህ ችግሮች መፍትሔ ሁለቱም ግዴታ አለባቸዉ፡፡ በመሰረቱ እነዚህ ጎደሉ ተብሎ የትም አይኬድም፤ ስንጀምር እንዳነሳነዉ
በባህልም በሃይማኖትም የምንስተዉ ስህተት ስለሆነ እንጂ፡፡
ብዙሃን
ኢትዮጵያዊያን ትዳር የምንመሰርተዉ እስከቤተሰቦቻችን ስለሆነ አብዝቶ ችግሩ ይስተዋላል፤ ባልም ሚስትን ቤተሰቦቼንማ አትንኪብኝ፣
ሚስትም ባልን በቤተሰቤማ አትምጣብኝ፣ ወዘተ መባባሉን ይጀምራሉ፡፡ ችግሮችን በጋራ እንደመፍታት ችግር ለመፍጠር እንደተደራጀ ቡድን
እለት እለት ጭቅጭቅ እና ንዝንዝ የበዛበት ህይወት ይመራሉ፡፡
ሐሙስ 2 ኖቬምበር 2017
የደህንነት ቀበቶ
የደህንነት ቀበቶ
በምድር
ላይ ህጎች በአራቱም አቅጣጫ ይወጣሉ፤ ህግ አዉጭ፣ ህግ ተንታኝ፣ ህግ አስፈጻሚ፣ ህግ ፈፃሚ፣ ዳኛ፣ አቃቢ ህግ፣ ጠበቃ፣ከሳሽ፣ተከሳሽ፣
ምስክር፣ዋስ፣ … ወዘተ ይኖሩታል፡፡ ህጎች ከህገ ልቡና ዛሬ በየመንደሩ እና በየቤቱ በየፌስቡኩ እስከ ሚወጡት እንሰማለን እናያለን
እንተዳደርበታለን እናስተዳድርበታለን ሌሎችን እንዳኝበታለን እራሳችንም እንዳኝበታለን፡፡ከሚሻር ህግ እስከማይሻር ለዘለዓለም የሚፀና
ከኦሪት ህግ (ብሉይ ኪዳን) እስከ አዲስ ኪዳን (የወንጌል ህግ ) ድረስ ይዘልቃል፤ ከዚሁ ጋርም የህግን መሰረት ያለቀቁ ዘመናትን
ያስቆጠሩ በህብረተሰብ ዘንድ የተከበሩ ብዙ ስርዓቶችም አሉን ለምሳሌ ያህል ለመጥቀስ (የገዳ ስርዓትን የመሰለ ብዙ ሚሊዮኖች የሚተዳደሩበት
ዘመን ያስቆጠረ) በቤተሰብ ዘንድ እና በተለያዩ ማህበረሰቦች መካከልም እንዲሁ ለዘመናት ህዝቡን ከሰንሰለት በጠነከረ አስተሳስሮ
ያለ ስርዓት በሁሉም ብሄር ብሔረሰብ ዘንድ አለን ቱባ ባህልን ጨምሮ፡፡
ለዛሬ
ከዚህ ወጣ ብለን አንድ ህግን መዘን አጠር አድርገን እንወያያለን ስለ ደህንነት ቀበቶ ህግ፤ በኢትዮጵያ ህግ ወጥቶለት በመተግበርና
ባለመተግበር በመቀጣትና በማስተማር እንዲሁም ላለመማር በማስተባበል ዉስጥ የዘለቀ ህግ አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ዓለም አላት፡፡
የደህንነት ቀበቶ/ ሴፍቲ ቤልት/ ጥቅሙ በዋናነት ለባለቤቱ ሲሆን
ረቡዕ 1 ኖቬምበር 2017
ትዳር ክፍል ፪
በይደር ያቆየነዉን ጥያቄ እንመልስ ካልን እና እንደዚህ አይነት እንደምናገባ/ለወንድም ለሴትም ያገለግላል/ ቢታወቅ እግዚአብሔር
ለአዳም ከጎኑ ሔዋንን በፈጠረ ጊዜ አዳም ባላንቀላፋ ነበር፡፡ቅዱስ ጳዉሎስም ስለ ትዳር/ጋብቻ ሲናገር " ቢቻላችሁ
…" በማለት ባላቅማማ እና አግቡ ብሎ ባስተማረ እና እሱም ባገባ ነበር፤ ነገር ግን ቅዱስ ጳዉሎስ አላገባም፡፡ ከገሚሶቹም
በቀር ከሐዋርያት አላገቡም ያገቡትንም ቢሆን ከጥቂቶቹ መልካም ሚስቶች በቀር መፅሐፍ ቅዱስ ሚስቶቻቸዉን አይጠቅስም፤አልጠቀሰምም፡፡ለምን
ካሉ ልሂቃን መልስ ይስጡበት፡፡
የሰዉ ልጅ ክፉ ሆኖ እንዳልሆነ እሙን ነዉ እኔ ክፉ ነዉ ብዬ ለመናገር ያዳግተኛል፤
እንደዉ ሌላዉ ቢቀር እነዚህ ሁለት ጥንዶች እንዃን በጓደኝነት ወቅት እንቅፋት ሲመታቸዉ እኔን ብለዉ የሚንሰፈሰፉ፣ ማዕድ እንዃን
ሲቋደሱ ቀድመዉ የማይጎርሱ፣ ትን ሲላቸዉም ሆነ ምግብ ሲያንቃቸዉ ምራቃቸዉን እንዃን ለመስጠት ወደ ኋላ የማይሉ፣ ያፈለገዉን ያህል
ቀጠሮ ቢያረፍዱ በትዕግሥት የሚጠብቁ ፣ … ሁሉንም ዘርዝሮ መጨረስ ስለማይቻል በወዘተ መገላገል ሳይሻል አይቀርም፤ ስለሰዉ ልጅ
ጥሩነት ለመግለፅ በቂ ናቸዉና (ለማያምን ግን ሺም ቢዘረዘር አያሳምነዉም)፡፡ ከትዳር ማግስት ግን እነዚያ ሃሜትም ምክርም የማይሰሙ
ጥንዶች ጆሮአቸዉ በኦዙን የሳሳ ይመስል ሽንቁር ይሆናል፡፡ ሆድ ይብሰዋል፣ ቶሎ ይከፋዋል፣ ቂም ይቋጥራል፣ ወሬ ይሰማል፣ ነገር
ይጠመዝዛል፣ በአጠቃላይ ማንነቱ ላይ የሆነ ነገር ዞር ይለበታል፡፡ አጋሩን/ሚስቱን እንቅፋት ሲመታት እያየሽ አትሄጂም ምን ወሬ
ታያለሽ፣ምግብ ሲያንቃት ቀስ ብለሽ አትበይም ምን ያጣድፍሻል ዉድድር የለብሽ እያለ ይነቅፋታል፣እሷም አባወራን የሚያህል ነገር ከዉጭ
ቀርቶ ሲያመሽ ስለጤንነቱ ሳይሆን ቅናት ፀጉሯን አቁሞት ሰላም አመሸህ እንደማለት የት አመሸህ ብላ በነገር ትቀበለዋለች፣ ከመነጋገር
በግል መወሰን ይጀምራሉ ይህ ነገራቸዉ ለብቻ ወስኖ እስከማርገዝ አልፎተርፎም ለብቻ የህክምና ክትትል ይጀመራል በአጋጣሚ ሃኪም ባለቤትሽስ
ሲላት አልሰማም ለምን ከተባለች አርግዤ አምጬ የምወልደዉ እኔ እሱ ምን አገባዉ ድረስ ይዘልቃል፤ ….
ሳምንቱ ከምኔዉ አልቆ/ዕለቱ ከምኔዉ መሽቶ
ዓርብ 20 ኦክቶበር 2017
ትዳር ክፍል ፩
ሰላም ወዳጆቼ እየደጋገመ/እየተመላለሰ ወደ አዕምሮዬ
እየመጣ የሚያስቸግረኝ በየአጋጣሚዉም የተለያዩ ጓደኞቼም ሲያነሱት የምሰማዉ ሲነሳም አጨቃጫቂነቱ ሰላም የሚነሳ ጉዳይ ዛሬ ልተነፍሰዉ
ፈለኩ፤ "ትዳር" በመፈላሰፍም/መንፈሳዊ በመሆንም/በመዘመንም … ዉስጥ ሆነን እናየዋለን አንባቢ እንደመሰለዉ ሊያቀናዉ
ሊያጣምመዉ ሊተቸዉ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
ትዳር
የሚለዉን ቃል የከሣቴ ብርሃን ተሰማ የአማርኛ መዝገበ ቃላት " ሰዉ ሁሉ በንብረቱ የሚተዳደርበት የቤት ስራ ፣ ባለ ጠጋም ሆነ ድሃ እንደተሰጠዉ መተዳደር" ብሎ ይፈታዋል፤
የትዳር ዉስጥ ድራማዎች
በመሰረቱ ድራማ እንደሚታወቀዉ በመድረክ የሚተወን፣ በተለያዩ ሚዲያዎች የሚተላለፍ እና
የአጭር ጊዜና የረጅም ጊዜ ድራማዎች አሉ፡፡ እነዚህ በአጭርና በረጅም ጊዜ ተመጥነዉ የሚሰሩ ድራማዎች በባህሪያቸዉ
ü
ኮሜዲ (አስቂኝ )ወይም አዝናኝ
ü
ትራጀዲ
ü
ሆረር ( አስፈሪ) ከማዝናናት
ከማስተማር ባለፈ በአስፈሪነታቸዉ የሚታወቁ፤ ነገር ግን ምንም አስፈሪ ቢሆኑ መልዕክት ከማስተላለፍ ወደ ኋላ የማይሉ ናቸዉ፡፡
ልክ ከዚሁ ጋር ተመሳሳይነት ያለዉ ትዳርም በምድራችን ሁለት ነጠላ ሰወች " ትዳርን " ሲመሰርቱ የሚተዉኑት የህይወት ድራማ ይሆናል፡፡ እነዚህም፡-
ü
የማስመሰል ( በአንድ ቤት
መኖር ብቻ ህይወት አልባ ዓላማ የለሽ )
ü
እዉን የሆነና ህይወት ህይወት
የሚል
ü
ማስፈራሪያና ዛቻ የሞላበት
ከፍቅር ይልቅ ፀብ ጭቅጭቅ የነገሰበት
ü
የሚፈልገዉን (የምትፈልገዉን
) በማድረግ ብቻ (በማሟላት ብቻ) ፕሮዲዉሰር(አዘጋጅ ) መሆን ( እንደቤት ሠራተኛ) በማገልገል ድራማዉን የሚሰሩ ወዘተ
ታድያ ትዳርም ህይወት አልባ እንደሆነና ሌላን
ሠዉ መስለዉ የሚተዉኑበት ከሆነና የማይኖሩት ሁለቱ ነጠላ (ሲንግል) ሠወች በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነዉ
እንደ አንድ ልብ አሣቢ ሆነዉ የማይኖሩት በድን አሻንጉሊት ከሆነ የሠዉ ልጅ ለምን ይጋባል? ለምንስ ትዳር ይመሰርታል? የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል፡፡
መቀጠሉ አይቀርም፤ እንቀጥላለን
ማሳሰቢያ ፡- የምንቀጥለዉ ግን በዉስጥም በዉጭም ባለዉ አስተያየታችሁ ላይ ተንተርሰን ነዉ፡፡
እሑድ 13 ኦገስት 2017
የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ›
የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ›: ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ ከገዛም ይጥፋበት› ይላሉ የምንዳዬ እናት አባዬ፡፡ ‹ምነው አባዬ ድኻ በመከራ የገዛውን ወርቅ እንዴት ይጥፋበት ይላሉ› ብለን ሞገትናቸው፡፡ ‹እይውልህ እኛ ሠፈር አራት ኪሎ አዲሴ የሚሏት አንዲ...
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)
ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!
መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡
ትቶ እና ችሎ
ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...
-
የጊዜ አጠቃቀም መግቢያ ስኬታማ የጊዜ አጠቃቀም ያዳበረ ሰራተኛም ሆነ ግለሰብ ጊዜዉን በመርሃግብር እና በዕቅድ ይመራል፤ ይህ ሰዉ ህይወቱን የሚመራዉ በዕድል ሳይሆን ...
-
ሰሞኑን በዚች በምድራችን ‹‹ጫካው ለዛፎች ብቻ›› በሚል ዛፎች ተሰባስበው በዱር አራዊቶች እና አዕዋፎች ላይ የአቋም መግለጫ አወጡ አሉ፤ ከመግለጫው ሥር እንደ አብይ ርዕሰ ጉዳይ ያደረጉት ጫካው ለእኛ ለዛፎች ብ...
-
በክፍል አንድ “ፍቅር በFace book ” በሚለው እውነተኛ ታሪክ ላይ መሰረት ያደረገ ክፍል ማቅረባችንን ሳሙኤል በFace book ላይ የተዋወቃትንና ሳይስቡት ፍቅር ውስጥ ገብተው በኃላም ሕይወትን የመጀመር አዝማሚያ...