ሐሙስ 14 ፌብሩዋሪ 2013

ቅዱስ ቫላንታይን


ቅዱስ ቫላንታይን
በየአመቱ በፈረንጆች feb 14 ቀን በአሜሪካና በቀሪዉ ክፍለ ዓለማት የተለያዩ አበባዎችን፣ ሻማዎችን፣ ስጦታዎችን፣ ፍቅረኛሞች በመለዋወጥ ቅዱስ  ቫላንታይንን በማሰብ ያሳልፋሉ፡፡በአገራችንም ብዙ ወጣቶች በዓሉን በድምቀት ያከብሩታል፡፡በዓልን ማክበር ምንም የከፋ ነገር ባይኖረዉም ለምን እናከብራለን ? ፋይዳዉ ምንድን ነዉ? የምታከብረዉ አገር የበዓሉ መከበር ዜጋዋን ምን ጥቅም ይሰጠዋል? የሚሉት ነገሮች ሊነሱ ይገባቸዋል፡፡
ዛሬ ወጣቱ የቄስ ቫላንታይንን ቀን እያከበረ ባለበት ሰዓት የበዓሉን ድምቀት እንዳላደበዝዘዉ ብፈራም ወደፈት ግን በአገራችን የሚከበሩትን መጤ በዓላት እናዳስሳለን፤በጎ ጎናቸዉንና መጠፎ ጎናቸዉን እናያለን፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ የኮራ የደራ የደመቀ እጅግ በጣም ብዙ በዓላት ሲኖሯት ገሚሶቹ እንዲሁ እንደቫላንታይን ቀን መጤዎች ናቸዉ፡፡ የመጤ በዓላት የአገራችንን ባህል ቅይጥ እንዲሆኑና የባለቤትነት መብት ላይ አጨቃጫቂ ሆነዋል፡፡ የ3000 ዘመን ታሪክ ያላት ኢትዮጵያ በንግስተ ሳባ በኩል ከኢየሩሳሌም ያመጣቻቸዉ ባህል፣ ሃይማኖት፣ ስልጣኔ … ወዘተ ጠቀሜታም ጉዳትም ሲኖረዉ ንግስተ ሳባ ከንጉስ ሰሎሞን ጋር ያላት ግንኙነት እዉን ንግስተ ሳባ ኦትዮጵያዊ ነች ወይ? የሚል ጥያቄን አስነስቷል፤እንኳንስ የመጡት ባህሎችና በዓላት ይቅርና ማለት ነዉ፡፡
ከዚህ ጊዜ አንስቶ (እስራኤላዉያን የንጉስ ሰሎሞንን ልጅ ምኒልክን ተከትለዉ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ ጊዜ አንስቶ) ዛሬ በብዙ ድካም ልንከላከለዉና ልናስቀረዉ የምንለፋዉ ብዙ በጀት የምንመድብበት የግርዛት ጣጣ አስቀድሞ የኛ አልነበረም፡፡ እንዲሁ በየግል ት/ቤትና በየመንግስት ት/ቤቶች ይልቁንም በየዩኒቨርችቲዎች ሳይቀር የሚከበሩት የከለር ቀን፡የእብደት ቀን ፡የከረባት ቀን፡ … ወዘተ ከባዕዳን አገራት ያመጣናቸዉ በዓላት ናቸዉ::
የኢትዮጵያ እንግዳ ተቀባይነት ወደ መጤ ባህሎች ተቀባይነት ተቀይሮ ዛሬ እነኝህንና ሎሎችን ባህሎች በዓላት በቀላሉ ተቀባይ ለመሆን መቻሉ ዛሬ በዓለም ላይ አነጋጋሪ እየሆነ የመጣዉን በሃይማኖትም ሆነ በባህል የተወገዘዉን የሌዝብያን (የሴት ለሴት መዳራትና መጋባት)፤ የጌዎች (የወንዶች ለወንዶች መዳራትና መጋባት) ሰዶማዊ ግብር በአገራችን ከ14000 በላይ አባላት እንዳሉት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ለዚህ እንዲበቃ ያደረገን ደግሞ ከልካይ ማጣታችንና ባለን ያለመርካት  ክፋና ደጉን ለመለየት የአዕምሮ ብስለት ማጣት ሳይሆን አዕምሮዎቻችንን በአግባቡ ያለመጠቀም አባዜ ነዉ፡፡
ትናንት ለእድገት ፀር ሆነ፡ ወደ ኋላ አስቀረን ልማትን አደናቀፈ እየተባለ ሲወቅስ የነበረዉ የኢ/ኦ/ተዋህዶ ቤተክርስትያን እግዚአብሔርንና ቅዱሳኗን የምታስብበትንና ለምዕመናኗ በረከትን የምታሰጥበት (ዓለም የሰማዕታት ቀን ብላ እንድታከብር ማለት ነዉ) ክብረ በዓላት በአንድ ልደታ፡ በሶስት በዓታ ፡ በአምስት አቦ፡ በሰባት ስላሴ፡ … እያለች ህዝቡን አሳነፈች ተብላ ቅድስት ቤተክርስትያኗ ያለሃጢያቷ ስትብጠለጠል ነበር፡፡አገርንም ሆነ ህብረተሰብን የሚጎዳ ነገር አልነበራትም፤ አክብሩ ብላም አላስገደደችም፡፡ ነገር ግን ት/ቤቶች እየተዘጉ ፣የትምህርት ሰዓት እየተቋረጠ፣ ወጣቱ ወዳልተፈለገ ስነ-ምግባርና የህይወት አቅጣጫ ሲያዘነብል ፣አንድም ሰዉ ሊያወግዝ አለመነሳቱ የሚያስተዛዝብና ቀጣይ ዕጣ ፈንታችን ስጋት ላይ የወደቀ ጉዳይ እንደሆነ ያመላክታል፡፡
በእያንዳንዱ መጤ በዓላት ቀን ወጣቶች በተለያየ ስፍራ አልባሌ በሆነ ሁኔታ ጊዜአቸዉንና ህይወታቸዉን በከንቱ ማባከን እየተለመደ መጥቷል፤ በነዚህ በዓለት አማካይነት ወጣቶች ለመጠጥ ቤት፡ለጭፈራ ቤት፡ ለሽሻ እና ለሲጋራ ማጤሻ፡ ለጫትመቃምና ለተለያዩ ሱሶች መጋለጥ፡ አልፎ ተርፎም ለወሲብ ጥቃት(ለፆታዊ ትንኮሳ)መጋለጥ አብይ መንገድ እየሆነ ይገኛል፡፡እነዚህ አላስፈላጊ ባህሎች፡ በዓላት፡ ቀናት … ጥቅማቸዉንና ጉዳታቸዉን በመለየት ትዉልዱን ለማስተማርና ለመቅረፅ የራሳቸዉን ባህሎች ሊያዳብሩና ሊኮሩበት እንዲችሉ ለማስቻል ወላጆች፡ የሚመለከታቸዉ መንግስታዊ፡ ሃይማኖታዊ፡ መንግስታዊ ያልሆኑ አካላት፡ ሚድያዎች … ወዘተ ጠንከር ያለሥራ ሊሰሩ ይገባል፡፡ ዝምታ ወርቅ የማይሆንበትም ጊዜ አለና ዝም አንበል! በተለይ FM ሬድዮኖቻችን ልብ ሊሉትና አገራዊ ግዴታቸዉንና የሚድያ ስነ ምግባሩን ተግባራዊ ሊያደርጉ ይገባል፡፡    
በዛሬዉ ዕለት ሱቆች የቀይ አልባሳት መሸጫ፣ የአበባ መሻጫዎች የአበባ ንግዳቸዉ የሚጧጧፍበት፣የስጦታ መሸጫዎችም እንዲሁ ገበያቸዉ የሚደራበት፣የጥበብ ባለሞያዎቻችንም የሙዚቃ ድግሳቸዉን ደግሰዉ ወጣቱን አስጎንጭተዉ የሚያሳክሩበትና ክብራቸዉን እንዲያጡና ከድንግልናቸዉ እንዲናወሩ የሚያደርጉበት ታላቅ ቀናቸዉ ነዉ፡፡ ጎዳናዋም ቀይ በለበሱና በአበባ ትሸማቀቃለች፤የሆቴል መኝታ ክክሎችም በደምና በበደል ይጨማለቃሉ፡፡ ወይኖች ለሐዘን ይጎነጫሉ፣ሻምፓኞች ይረጫሉ፣ገንዘቦች እንዲሁ ይመነዘራሉ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ኔትዎርኮች ይጨናነቃሉ፣የፌስ ቡክ ገፆች እንዲሁ በመልካም ምኞት ገላጮች ትዋከባለች፣ጓደኛ የሌላቸዉ አንገታቸዉን ደፍተዉ ክብራቸዉን ጠብቀዉ ያመሻሉ፡፡ እግዚኦ!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...