ማክሰኞ 12 ፌብሩዋሪ 2013

ማህበራዊ ድረ ገፆች እና ንባብ



”ማህበራዊ ድረ ገፆች እና ንባብ

ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመፃሕፍት ኤጀንሲ ባለፈዉ የካቲት 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ከ7፡30-11፡00 የቆየ በ”ማህበራዊ ድረ ገፆች እና ንባብ” በሚል ርዕስ ዉይይት አካሂዶ ነበር: በዕለቱም የተለያዩ ምሁራን ተገኝተዉ ነበር::  ከነዚህም መካከል አወያይ የነበሩት ገጣሚና ሃያሲ አያልነህ ሙላቱ የጥናታዊ ፅሁፍ አቅራቢ ነፃነት ተሰፋዬ እና ሌሎች የዉይይቱ አቅራቢዎች ታዋቂዉ የ”ዳንኤል እይታዎች” ብሎገር ዲ/ን እና ደራሲ ዳንኤል ክብረት ታዋቂዉ የ”እማማ ጨቤ” ተከታታይ ድራማ ደራሲ የሬድዮ ባለሙያ ጋዜጠኛ ዮናስ አብረሃ ሲሆኑ :
አቶ ነፃነት በጥናታቸዉ ለመዳሰስ የሞከሩት
ü  ማህበራዊ ድረ ገፆች እና ንባብ
ü  ማህበራዊ ድረ ገፆች ያላቸዉ አጠቃላይ አዉንታዊ አስተዋፅኦ
ü  ማህበራዊ ድረ ገፆች በንባብ ባህል ላይ የፈጠሩት አዉንታዊ እና አሉታዊ ተፅእኖ…ወዘተ


ማህበራዊ ሚድያ፡-
Ø  Internet forums
Ø  Weblogs /blogs
Ø  Social blogs
Ø  Micro blogging
ከነዚህ ማህበራዊ ሚድያዎች መካከል ፌስቡክ ቁጥር አንድ እንደመሆኑ መጠን በኣለም ላይ ከአንድ ቢልዮን በላይ ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን አጥኝዉ አቶ ነፃነት አፍሪካ አዉሮፓ ኤስያ ና አሜሪካን በመከተል 48.3 ሚልዮን ተጠቃሚዎች እንዳሉት ተናግረዋል፤ከዚህ ዉስጥም የተወሰነዉ ኢትዮጵያዊ መሆኑ እሙን ነዉ፡፡ (883160 ሰዎች ሲሆኑ 72 በመቶ ወንዶች ቀሪዉ 28 በመቶ ሴቶች ናቸዉ) ከዓለም በ86ኛ ደረጃ ላይ እንገኛለን፤ … በጥናቱ መሰረት፡፡
አክለዉም እነዚህ ማህበራዊ ድረ ገፆች፡
§  አማራጭ የንባብ መድረኮች
§  ሃሳብን በነፃነት የመናገርና የመፃፍ
§  በዉድ ዋጋ የሚገኙ መፃህፍትን ለማንበብ
§  አንብቦ  ሃሳብን ለመለዋወጥና ለመከራከር
§  ለተማሪዎች በቂ መፃህፍትን ለመስጠት
§  መፃህፍትን በሚፈለገዉ መጠን ለማቅረብ … ወዘተ
በነዚህ ማህበራዊ ድረ ገፆች፡
v  በአሜሪካ 43 በመቶ ነዋሪዉ ንባባቸዉን አዳብረዋል
v  በኢንግሊዝ 20 በመቶ ልብወለድ 67 በመቶ ድረ ገፅ 55 በመቶ ኢሜል 46 በመቶ ብሎጎችን ተጠቃሚ ሆነዋል
v  በአገራችንም እንዲሁ ከእለት ወደ ዕለት የንባብ ባህል እየዳበረ መሆኑን በማስረጃ አስደግፈዋል፡፡
ከህብረተሰቡ ወደ ማህበራዊ ድረ ገፅ ማዘንበል የተነሳ በአለም ታዋቂዉ News week  መፅሔት ከ2013 የፈረንጆች ዘመን መለወጫ ጥር ወር አንስቶ ወደ ድጅታልነት ተቀይሯል፡፡ ይህ የሚያሳየዉ ደግሞ የማህበራዊ ድረ ገፅ በአለም ላይ መስፋፋትን ነዉ፡፡
ከማህበራዊ ድረ ገፆች መካከል፡-
·         የዳንኤል እይታዎች
·         የኤፍሬም እሸቴ እይታዎች
·         የብስራት እይታ
·         የደረሰ ረታ እይታዎች
·         በቅርቡ ደሞ የበዉቀቱ ስዩም….ጥቂቶቹ ናቸዉ፡፡
·          
እነዚህ ድረ ገፆች ፋይዳቸዉ፡-
Ø  የንባብ ባህልን ያዳብራል
Ø  አማራጭ መፃህፍትን ይሰጣል
Ø  የሃሳብ ልዉዉጥን ያሰፋል
Ø  የተማሪዎችን የማጣቀሻ መፃህፍትን ይቀርፋል
አሉታዊ ተፅዕኖዉ፡-
ü  የመረጃ ተአማኒነት ያሳጣል
ü  የቆዩ መፃህፍትን መዘንጋት
ü  የፀሃፊዎችን ድካም ዋጋቢስ ያደርጋል
ወዘተ…
ይህንን ዝግጅት ያዘጋጀዉ ኤጀንሲዉ ጅማሮዉ ይበል የሚያሰኝ ነዉ፡ እኔም በበኩሌ የንባብ ባህላችንን እናዳብር ዘንድ ተማፅኖዬን አቀርባለሁ፡፡ኤጀንሲዉንም ሆነ አቅራቢዎችን በመቀጠልም ታዳሚዎችን ከልብ አመሰግናለሁ፡፡መልካም የንባብ ዘመን!


1 አስተያየት:

  1. It is a precised summery of the program. I appreciate your effort. This issue is serious and need the effort of all of us specially bloggers to disseminate useful information & article to the public to promote reading and to exchange ideas.

    ምላሽ ይስጡሰርዝ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...