ሐሙስ 19 ኤፕሪል 2012

ውረድ


ተው ተው ሲሉህ
 ሲያፈራሩህ
አቅማቸውን አተው
ማንነትህን ዘንግተው
አቅራሩ ሸለሉ
ፎከሩ
ፍጥረት በሙሉ
አንድም ሳይቀሩ
ለአመድ ባንድነት
ለትርፍ ሳይሆን ለጉድለት/ለክስረት/
ተው ተው እያለሁ
እያስፈራሩህ
ውረድ ወይ ፍረድ
ብለው ተሳለቁብህ
ትወርዳለህ ወይስ ትፈርዳለህ?
ቅል ልመናውን ለማያውቅ ፍርዱ
አዕምሮ መስጠት ነው
በትዕግሥት ማለፍ ነው
የፈጣሪ/ የአባት ልምዱ
እላለሁ
አትውረድ
አትፍረድ
ይቅር በለኝ እንጂ
በምህረትህ እንድንዋጅ
ተው ተው ተው አለህ
በመፍጠርህ ሊያስቆጩህ
22/01/03
ደረሰ ረታ
visit us again!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...