ዓርብ 20 ኦክቶበር 2017

ትዳር ክፍል ፩



ሰላም ወዳጆቼ እየደጋገመ/እየተመላለሰ ወደ አዕምሮዬ እየመጣ የሚያስቸግረኝ በየአጋጣሚዉም የተለያዩ ጓደኞቼም ሲያነሱት የምሰማዉ ሲነሳም አጨቃጫቂነቱ ሰላም የሚነሳ ጉዳይ ዛሬ ልተነፍሰዉ ፈለኩ፤ "ትዳር" በመፈላሰፍም/መንፈሳዊ በመሆንም/በመዘመንም … ዉስጥ ሆነን እናየዋለን አንባቢ እንደመሰለዉ ሊያቀናዉ ሊያጣምመዉ ሊተቸዉ መብቱ የተጠበቀ ነዉ፡፡
ትዳር የሚለዉን ቃል የከሣቴ ብርሃን ተሰማ የአማርኛ መዝገበ ቃላት " ሰዉ ሁሉ በንብረቱ የሚተዳደርበት የቤት ስራ ፣ ባለ ጠጋም ሆነ ድሃ እንደተሰጠዉ መተዳደር" ብሎ ይፈታዋል፤
የትዳር ዉስጥ ድራማዎች
በመሰረቱ  ድራማ እንደሚታወቀዉ በመድረክ የሚተወን፣ በተለያዩ ሚዲያዎች የሚተላለፍ እና የአጭር ጊዜና የረጅም ጊዜ ድራማዎች አሉ፡፡ እነዚህ በአጭርና በረጅም ጊዜ ተመጥነዉ የሚሰሩ ድራማዎች በባህሪያቸዉ
ü  ኮሜዲ (አስቂኝ )ወይም አዝናኝ
ü  ትራጀዲ
ü  ሆረር ( አስፈሪ) ከማዝናናት ከማስተማር ባለፈ በአስፈሪነታቸዉ የሚታወቁ፤ ነገር ግን ምንም አስፈሪ ቢሆኑ መልዕክት ከማስተላለፍ ወደ ኋላ የማይሉ ናቸዉ፡፡
ልክ ከዚሁ ጋር ተመሳሳይነት ያለዉ  ትዳርም በምድራችን ሁለት ነጠላ ሰወች " ትዳርን " ሲመሰርቱ የሚተዉኑት የህይወት ድራማ ይሆናል፡፡ እነዚህም፡-
ü  የማስመሰል ( በአንድ ቤት መኖር ብቻ ህይወት አልባ ዓላማ የለሽ )
ü  እዉን የሆነና ህይወት ህይወት የሚል
ü  ማስፈራሪያና ዛቻ የሞላበት ከፍቅር ይልቅ ፀብ ጭቅጭቅ የነገሰበት
ü  የሚፈልገዉን (የምትፈልገዉን ) በማድረግ ብቻ (በማሟላት ብቻ) ፕሮዲዉሰር(አዘጋጅ ) መሆን ( እንደቤት ሠራተኛ) በማገልገል ድራማዉን የሚሰሩ ወዘተ
ታድያ ትዳርም ህይወት አልባ እንደሆነና ሌላን ሠዉ መስለዉ የሚተዉኑበት ከሆነና የማይኖሩት ሁለቱ ነጠላ (ሲንግል) ሠወች በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነዉ እንደ አንድ ልብ አሣቢ ሆነዉ የማይኖሩት በድን አሻንጉሊት ከሆነ የሠዉ ልጅ ለምን ይጋባል? ለምንስ ትዳር ይመሰርታል? የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል፡፡
መቀጠሉ አይቀርም፤ እንቀጥላለን
ማሳሰቢያ ፡- የምንቀጥለዉ ግን በዉስጥም በዉጭም ባለዉ አስተያየታችሁ ላይ ተንተርሰን ነዉ፡፡

እሑድ 13 ኦገስት 2017

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ›

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ›: ‹ድኻ ወርቅ አይግዛ ከገዛም ይጥፋበት› ይላሉ የምንዳዬ እናት አባዬ፡፡ ‹ምነው አባዬ ድኻ በመከራ የገዛውን ወርቅ እንዴት ይጥፋበት ይላሉ› ብለን ሞገትናቸው፡፡ ‹እይውልህ እኛ ሠፈር አራት ኪሎ አዲሴ የሚሏት አንዲ...

ማክሰኞ 14 ጁላይ 2015

ሳይማር ያስተማረን … … … ሳይማር ያስመረቀን ትዉልድ




የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
የሚሊንየም አዳራሽ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች በተለያየ የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ፣የሁለተኛ እና የዶክትሬት ትምህርታቸዉን ያጠናቀቁ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን ለግማሽ ቀን ያህል አስተናግዶ ዉሎአል፡፡ይህንን ታላቅ የምርቃት በዓል አስመልክቶ ታዋቂዉ የኤፍ.ኤም.ሬድዮ ጣቢያ እዚያዉ ከሚገኘዉ ጊዜያዊ ጣቢያዉ የተማሪዎችን፣ የዩኒቨርስቲዉን መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች፣ የተመራቂ ተማሪዎችን ወላጅ ዘመድ ጓደኞች የእንኳን ደስ አላችሁ እና የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ቀጥታ ስርጭት እያስተላለፈ ይገኛል፡፡
አድማጮቻችን ዛሬ በልዩ ፕሮግራም ከቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ ፊት ለፊት በሰፊዉ ሜዳ ላይ ተንጣሎ ከሚገኘዉ የሚሊንየም አዳራሽ ጊዜያዊ የማሰራጫ ጣቢያችን ይህንን በዓይነቱ ልዩ የተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ቀጥታ ተቀብለን ለማስተላለፍ እና ከማለዳዉ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከስፍራዉ በመገኘት ለስለስ ባሉ ጣዕም ባላቸዉ ሙዚቃዎች ስናዝናናችሁ መቆየታችን ይታወሳል፡፡
ለስለስ ያለዉን ሙዚቃ ከዚህ ጊዜያዊ የማሰራጫ ጣቢያችን ያስደመጡንን የስቲዲዮ ባለሞያዎቻችን፣ የደቡብ ሱዳኑን፣ የቻይናዉን እና የደቡብ ኮርያዉን አቀንቃኞች በቅደም ተከተላቸዉ ላመሰግን እወዳለሁ፡፡
አስቀድሜ እንደነገርኳችሁ የዛሬዉ በዓል እጅግ ልዩ ነዉ፤ ልዩ ከሚያደርጉት ነገሮች መካከል የአሜሪካዉ ፕሬዘዳንት እዚህ ጎረቤታችን ኬንያ መጥተዉ ጎብኝተዉ በተመለሱበት ማግሥት እና ወደ ኢትዮጵያም በተመሳሳይ ሁኔታ ጉብኝታቸዉን ያደርጋሉ ተብሎ ከሚጠበቅበት ዋዜማ መሆኑ ነዉ፡፡
አድማጮቻችን እንግዲህ የምረቃ መርሀግብሩ እየተጠናቀቀ እና በስፍራዉ የታደሙ የተመራቂ ተማሪ ቤተሰቦች ከአዳራሽ እየወጡ መሆኑ በርቀት ይታየኛል፤ በዚህ ታላቅ የምረቃ በዓል ላይ ክቡር ሚኒስትሩ ባይገኙም የተከበሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እና የአንድ ቋሚ ኮሚቴ ሠብሳቢ የሆኑት እኚህ ሠዉ ከክልል ከመጡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋራ በጋራ በመሆን ተማሪዎቹን ለማስመረቅ ተገኝተዋል፡፡
ክቡራን አድማጮቻችን እነኚህን ሁለት የአገራችን ታላላቅ ሰወች ስለምርቃቱ እና አንዳንድ ወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች አንስተን በሰፊዉ እናወራቸዋለን በጥሞና ተከታተሉን፡፡ እስከዛዉ በጣም የምንወደዉ እና የኢትዮጵያ ወዳጅ እና ባለዉለታ የቦብ ማርሊን stand up for your right የሚለዉን ተጋብዛችኋል፡፡
አድማጮቻችን ሁለቱን የአገሪቱን ታላቅ ባለስልጣናት አየር ላይ ልናቀርብላችሁ የሞከርነዉ ሙከራ ባለስልጣናቱ ለአስቸኳይ አገራዊ ጉዳይ ተጣድፈዉ ባልጠበቅነዉ የመዉጫ በር ስለወጡብን ሙከራችን አልተሳካም፡፡
አድማጮቻችን እንደሚታወቀዉ ብዙ ተማሪዎች ጥሩ ዉጤት በማስመዝገብ የዋንጫ እና የሚዳልያ ተመራቂዎች እንዳሉ ሰምተናል፤ ከነዚህ መካከል አንድ ልጅ እዚህ አጠገቤ አለ ከእርሱ ጋር የማደርገዉን ቆይታ ተከታተሉን፡-
እስኪ ስምህንና እዚህ የተገኘህበትን ምክንያት ለአድማጮቻችን ግለፅልን
̋ ሴባ እባላለሁ የመጣሁት የትምህርት ጊዜዬን አጠናቅቄ ለምርቃት ነዉ የተገኘሁት ˝
እንኳን ደስ አለህ
̋እንኳን አብሮ ደስ አለን  ̋
ሴባ በዛሬዉ ዕለት በመመረቅህ ምን ተሰማህ?
˝ እንዴ! … በጣም … በጣም … ግልግል ነዋ! ትልቅ ግልግል ̋
በምን የትምህርት ዘርፍ ነዉ የተመረከዉ?
˝̋ በFBI ነዉ የተመረኩት፤ ˝
ከFBE ፋክልቲ ማለትህ ነዉ?
˝ ያዉ ነዉ … ምን ልዩነት አለዉ ፍሬንድ  ̋
ከየት አካባቢ ነዉ የመጣኸዉ?
˝ እዚሁ ነኝ ከየትም አልመጣሁም  ̋
ሥምህ ለየት ያለ ነዉ ትርጉሙን ብትነግረኝ?
˝ ጓደኞቼ ናቸዉ ያወጡልኝ እንደምታየዉ ፀጉሬን ሹሩባ መሰራቴን ተከትሎ እና ሴባስቶፖል የሚለዉን ሲያቆላምጡ ነዉ ሴባ ያሉኝ  ̋
ኦ! ሴባስቶፖል ነዉ ሰምህ?
˝ ኖ! ስሜ ቴዎድሮስ ነዉ  ̋
በጣም ጥሩ የዋንጫ ተሸላሚ ነህ መሰለኝ ዋንጫም በእጅህ ሜዳልያዉንም አንገትህ ላይ እንደማየዉ ባለድርብ ድል ነህ፤
˝ አቦ ለገተታ ነዉ ባክሽን … … ከፍሬንዳችን ለፎቶ ተቀብዬ ነዉ  ̋
እናመሰግናለን፡፡
አድማጮቻችን የመጀመሪያዉን ቆይታችንን ተከታትላችሁታል በጣም አዝናኝ እና አስተማሪ ነበር ቀጣዩን ደግሞ አንዲት ወጣት ተመራቂ ከጎናችን ትገኛለች ከእርሳ ጋር ጋር ያለንን ቆይታ ተከታተሉን፡፡
እህታችን እንኳን አደረሰሽ ደስም አለሽ
˝ እንኳን አብሮ ደስ አለን  ̋
ስምሽን እና ስለዛሬዉ በዓል ለአድማጮቻችን የሚሰማሽን ነገር በአጭሩ ብትገልጭልን?        
˝ ስሜ እንኳን ይለፈኝ በአጭሩ የማስተላልፈዉ በዛሬዉ በደስታዮ ዕለት ሳይማሩ ያስተማሩኝን አርሶ አደር ቤተሰቦቼንና ሳይማሩ እዚህ በክብር እንግድነት ተገኝተዉ ያስመረቁንን የክብር እንግዶች፣ የትምህርት ቤቱን ማህበረሰብ ፣ አራት ነጥብ አምጥቼ እንድመረቅ ላበቁኝ መምህራኖቼ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፤ ˝
አድማጮቻችን መርሀግብሩ እንደቀጠለ ነዉ ተከታተሉን … …

ማክሰኞ 16 ጁን 2015

ከእናንተ መካከል ንፁህ የሆነ ይዉገራት (ለአሌክስ አብርሃም)

https://www.facebook.com/alex.abreham.31/posts/1607429286206948
ማህደር የእኛን ማህደር ስትከፍተው !!
(አሌክስ አብርሃም) ለተፃፈዉ ምላሽ ...


“ የተኛዉን በሬ ቆስቁሰዉ አደረጉት አዉሬ ”  ይላል የአገሬ ሰዉ፤ ሰምቼ መፃፍ ያላሰኘኝ ነገር ቢኖር የቢግ ብራዘሩ የሃና ጉዳይ፣ ሊቢያ ላይ የተፈፀመዉ የንፁሐን ዜጎች ደም በከንቱ በኤሲስ መፍሰስ እና መሰዋት፣ አሁን ደግሞ ከግራ ወደ ቀኝ እንደመሰለን ትንሽ ነገር አንጠልጥለን የነፈስንበት የአርቲስት ማኅደር አሰፋ ጉዳይ ናቸዉ፡፡ አሁን ግን የማደንቀዉ ጸሐፊ (ጦማሪ) አሌክስ አብርሃም ፅንፈኛ ሆኖ የፃፈዉ እና ህዝቡን የዘለፈበት ጉዳይ ዝምታን እንዳልመርጥ አድርጎኛል፡፡
1ኛ. ይህ ወዳጄ መጽሐፍ ቅዱስን ደስ ሲለን ብቻ የምንጠቀምበት፣ ሐብታሞች የማይነቀፉበት እና የማይገሰፁበት፣ እሱ ብቻ ሲፈቅድ ለአዕምሮዉ የሚመቸዉ ተግሣፅ ሲሆን ይለፍ የሚለዉ ጉዳይ አስመስሎታል፣ ተግሣፆችንም እንደሱ ፅሑፍ እኔ ካላረምኳቸዉ አይነት ነገር አይቼበታለሁ፣ ሌላዉ ለአሌክስ አብርሃም አክብሮቴ እና አድናቆቴ እንዳለ ሆኖ መጽሐፍ ቅዱስን እንደ አንድ ተራ ጥራዝ ባያየዉ እመርጣለሁ፡፡
2ኛ.እንደ አንዳንድ የሥነ ፅሑፍ ስነምግባር ያልገባቸዉ የኔ ቢጤዎች ዘለፋ የበዛበት ነገር ባይፅፍ ለዚያዉም አግባብነት የጎደለዉ እንዲህ ስል ግን ተጨባጭነት ያለዉ ተግሳፅ አይገባም ማለቴ አይደለም፡፡
3ኛ. ሰዉየዉ ሃብታም ስለሆኑ ብቻ የሳቸዉ ጉዳይ በክፉ አይነሳ ብሎ አግባብነት የጎደለዉ ሙገሳ ቢያቆም፤ እኚህ ሰዉ በአንድም በሌላም ምክንያት ለዚህ ህዝብ ባለዉለታ መሆናቸዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚነገረዉ አይደለም፡፡ ገንዘብ ሰጡ ማለት ንፁህ በኩለሄ (ሁሉም ቦታ ንፁህ ) ናቸዉ ማለት እንዳይደለ ልብ ቢል ሰብአዊነታችን በሳንቲም ድቃቂ ሲገዛ ዝም የምንል ህዝቦች መሆን የለብንም እና፡፡
4ኛ. ሌሎች ሃብታሞች በየጓዳ ጎድጓዳዉ ያሻቸዉን ስለሚሰሩ እሳቸዉን ዝም ማለት ከየት የመጣ የበደል ማጣፊያ ነዉ? አልገባኝም
5ኛ. አዎ ማኅደር አገር የሚያደንቃት ባለሙያ ነች ይህ ማለት ግን እንዳሻት እንድትሆን ማካካሻ አይደለም፤ እርሷ ስታጠፋም ዝም እንድንላት ይህን ያህል የወረደ ሞራል እንደሌለን ልብ በል፡፡ ይህ ህዝብ እንኳንስ በቴሌቭዢን መስኮት ያያትን ማኅደርን ይቅርና አንተን የሚያደንቁ አድናቂዎችህ ፅሑፍህን ታዝበዉ እንዴት አስተያየት እንደሚሰጡህ ልብ በል፡፡
6ኛ. እዛዉ ማኅደር ላይ ባለህ አቋም እርሷ ለዚህ መጪ ትዉልድ (ህፃናት) አርአያ ካልሆነች ማን ሊሆን ነዉ ሲጀመር እኮ አንተ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ጥፋቷ እንደወደድካት ህዝቡም (ህጻናትም) እንደዚያዉ ማድረግ እንዲችሉ ማድረግ አይቻልም፡፡
ሳጠቃልለዉ እንደጦማሪነትህ ሃላፉነትህ ይህ ነዉ? እንዲህ ሽንጥህን ገትረህ የተከራከርከዉ፣ አርቲስት መሐሙድን፣ ባለፀጋዉ የለገሱትን ገንዘብ እያጣቀስክ የፃፍከዉ እንደ አርቲስቶቹ የብር ሽልማቶችን ሽተህ ይሆን? ሰዉየዉ እንኳን ፅፈህ … ካልፈለጉ አይሰሙም፤ ህዝቡን ያዝ …
እኔ እና እኔን ለምትመስሉት፡­
በሰዉ በደል ሆያ ሆዬ ለምንል እስኪ የሌሎችን ጉድፍ ትተን የራሳችን ምሰሶ ዞር ብለን እንመልከት፤ አሌክስን ባስቆጣዉ መጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዳለዉ ታሪክ ( አንዲት ሴት ስታመነዝር ቢያገኙዋት ጌታ ጋር ይዘዋት በመሄድ ከሰሱዋት እንዲህ በማለት “ ስታመነዝር አገኘናት  ስለዚህ እንደ ስርአታችን በድንጋይ ወግረን እንድንገድላት ፍቀድልን ” በማለት  ጌታም “ በአጭሩ ከእናንተ ንጹሕ የሆነ ይዉገራት … ) በደላቸዉን ያዉቀዉ ነበር እና እንዲህ አለ፡፡ አሁንም እኔም እላለሁ ከማኅደር ንጹሕ የሆነ ፌስ ቡክ ላይ ይፃፍ፣ ይተቻት፣ ይማት፣ ይስደባት፣ ….
የተሻለ ነገር አለን የምንል ደግሞ ለዚህ ትዉልድ በጎዉን ቃል እንፃፍ ፣ በጎዉን ነገር እናሳይ፣ በጎዉን እንኑር፣ …   

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...