እሑድ 22 ጁን 2014

አለመግባባትን ለማሰወገድ



በመኖር ዉስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በምን መልኩ መፍታት ይቻላል?
Image:Resolve Conflict in Marriage Step 8.jpg
የሰዉ ልጅ በህይወት ዘመኑ ረጅምም ይሁን አጭር፣ አስደሳችም ሆነ አሳዛኝ የሆነ ህይወን መኖሩ ግድ ነዉ፡፡በዚህ ወቅት ሁሌ መግባባቶች ብቻ ናቸዉ ብሎ ማሰብ የማይታሰብ ጉዳይ ነዉ፡፡ታዲያ አለመግባባት ካለ ይህንን አለመግባባት እንዴት መፍታት ይቻላል? ዋናዉና መሠረታዊዉ ጥያቄ ነዉ፡፡
ወደ መፍትሄዉ ከመሄዳችን በፊት እስኪ አለመግባባቶች ከምን እና ከማን ዘንድ ይፈጠራሉ የሚሉትን በጥቂቱ እንመልከት፤
ü  ባለትዳሮች (ባል ከሚስት ወይም ሚስት ከባል ጋር)
ü  ወላጆች (ቤተሰብ) ከልጆች ጋር ልጆች ከቤተሰብ/ከወላጅ ጋር፤ (ቤተሰብ በጠቅላላዉ እርስ በርስ ሠላም ዝር የማይልበት ቤት
ü  ፍቅረኞች (ወንዱ ከሴቷ ሴቷ ከወንድ ፍቅረኛዋ ጋር)
ü  ጓደኛሞች (ወንዶች ከወንዶች፣ ሴቶች ከሴቶች፣ ወንዱ ከሴት፣ ሴቷም ከወንድ ጋር ) ትንሽ በሚባሉ ችግሮች የሚፈጠሩ አለመግባባቶች
ü  መንግስትና ህዝብ (ባለመደማመጥና ባለመከባበር እኔ ነኝ የምገዛህ ወይም የማስተዳድርህ፣ አንተ አትገዛኝም ወይም አታስተዳድረኝም አለበለዚያም ወደ ሥልጣን ያመጣሁህ እኔ ነኝ … እንዳመጣሁህ አወርድሃለዉ….)
ü  መንግሥት ከመንግሥታት/ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች (በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች እና ኃይልን ለማሳየት በሚሞከር ትንኮሳ፣ በጉርብትና፣ በድንበር ጉዳይ፣ ቅኝ ለመግዛት በማሰብ እና ላለመገዛት መወሰን፣….)
ü  መንግሥት ከተቋማት ጋር (በሪፖርት፣ በዜና እወጃ፣ ምሥጢር በማዉጣት፣ ጫና በመፍጠር ፣ ጥቅማ ጥቅሞችን በማስቀረት፣ ሌሎች ወገኖችን በማሳመፅ፣ አላስፈላጊና አወዛጋቢ አዋጆችን በማወጅ፣ ….)
ü  ወዘተ
ችግሮች የሚፈጠሩበትን አካባቢ እንዲህ በጥቂቱ ከዘረዘርን በማዕከልነት መፍትሔዎችን እንዲሁ በጥቂቱ ማንሳቱ አወያይ እና ሌሎችንም ሻል ያሉ ምፍትሔዎችን በተጠና መልኩ ያመጣሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ለጊዜዉ ጥናቱን ለባለሙያዎቹ ልተዉና ይሆናሉ የምላቸዉን እነሆ ብያለሁ፡-

እሑድ 8 ጁን 2014

ክፍል ስድስት… … … አጋጣሚ



ረጅም ዕድሜን ባልኖርም ሊደርሱብኝ የሚችሉትን አስተናግጃለሁ፣ ማየት የነበረብኝን አይቻለሁ፣ ደስታንም ሃዘንንም ከእህቴ የበለጠ አዉቃለሁ፣ ( ከእህቴ እንደምበልጥ የማረጋግጥልህ እሷ በህይወቴ ጣልቃ እየገባች አዉቅልሻለሁ ስትለኝ ይህንን ሁሉ እንደማዉቅ አለማወቋ በቂ ማረጋገጫ ነዉ፤ እስኪ እኔን ከእናቴ ፈርማ ተረክባ ቢሆን አሁን ያለሁበት ሁኔታ ለምን እንደሚዳርጋት አስበኸዋል? ) አሁን ከምነግርህ በላይ አዉቃለሁ፤ ነገር ግን እስካሁን የማዉቀዉ መጥፎ ነገሮችን ነዉ ጥሩ የተባሉትንም ቢሆን ከእርሷ የተሻለ አዉቃለሁ፡፡ የሚገርመዉ ስለግል ህይወቴ ዕድል ሳትሰጠኝ ስለ አገር ጉዳይ ቁጭ አድርጋ ታወራኛለች፤ እስኪ አስበኸዋል እኔ አሁን ስለ አገር የሚያገባኝ ሴት ነኝ የኔን ነፃነት ነፍጋኝ ዲሞክራሲ ስለጠማት እና ስለራባት አገር እኔ ምን አግብቶኝ ነዉ ከእሷ ጋር ስለ አገር ጉዳይ ለማዉራት በጠረጴዛ ዙሪያ የምሰደረዉ? ስለፍቅር እየተከለከልኩ ስለ ፖለቲካ የሚፈቀድልኝ እንዴት ነዉ ነገሩ? እኔ የሚገርመኝ ፖለቲካል ሳይንስ ታጥና ህክምና ግራ ግብት ይለኛል፡፡ ለምን አታገቢም ስትላት መጀመሪያ አገር ባለቤት ይኑራት ትልሃለች፤ ለምንድን ነዉ የራስሽ ነገር የማይኖርሽ ስትላት አሁን ጊዜዉ አይደለም ስንት አንገብጋቢ ነገር እያለ ትልሃለች፤ እሷን የሚያንገበግባት የእኔና የአገር ጉዳይ ብቻ ነዉ፡፡
ልብ በለህ ስማኝ እሷ ወንድ የምታዉቀዉ ስለፖለቲካ ጉዳይ ለማዉራትና በህክምና ሊረዳ በስራ ቦታዋ ሲመጣ ብቻ ነዉ፤ ባለፈዉ አንዱ ከቤት ድረስ ቢመጣ ሁላችን ደስ ብሎን ( መቸስ በባህላችን ሴት ልጅ ወንድ ይዛ እቤት ድረስ ስትመጣ የቱንም ያህል ደስ የማይል ጉዳይ መሆኑ ግልፅ ቢሆንም ይህ የሚያሳየዉ የጉጉታችን ልክ መጠነ ሰፊ መሆኑን ያመላክታል ) ግድግዳዉ ላይ ጆሮአችንን ለጥፈን ( አንድያዉን ለስነን ብትለዉ ይቀላል) ብናዳምጥ ብናዳምጥ አንዳች ነገር አጣንባት ከጆሮዬ ይሆን ብዬ አብራኝ የነበረችዉን የቤታችን አባል ሰራተኛይቱን ብጠይቅ እሷም እንደኔዉ ተበሳጭታ ኖሮ እሷቴ አናዳችም ስለሴትና ወንድ ያወራችዉ ነገር እንደሌለ ነገረችኝ፤ ያዉ የፈረደበትን ፖለቲካ እቤት ድረስ ይዛ መጥታ ታቦካዉ ጀመረ እንጂ፡፡ አሁን እስቲ ማን ይሙት ‹‹ የዘመናችን ብቸኛዋ ፖለቲከኛ ሴት ለመባል ነዉ ወይስ … ›› እስኪ እንደዉ ብቻ ተወኝ፤ ነገረ ዓለሙ ሁላ ፖለቲካ ፖለቲካ የሸተተበት ዘመን ላይ ደርሰን ህጻን አዋቂዉ አልጋና ትራሱ ሁሉ ፖለቲካ ሆኖ ፍቅር ጠፋ አንዴ እኔ ብገኝ በምን እናጥፋሽ ብለዉ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡
( እነማን ናቸዉ ለማለት ፈለኩና የሞቀ ወሬያችንን በኔ ጣልቃ ገብነት እንዳልገታዉ ፈራሁና እየተከታተልኳት መሆኔን አንገቴን ላይ ታች በመነቅነቅ ገለጽኩላት፤) 
ከዚህ ቀደም እንዳወራነዉ ከልጅነት ጓደኛዬ ሌላ ተባራሪዎቹን ሳንቆጥር አንድ ሶስት ወንዶችን በደንብ አዉቃለሁ፤ ነገር ግን ይህቺ ክፉ እህቴ ሁሌ ጥላዋን እያጠላችብኝ እንደዛፍ ላይ እንቅልፍ አስሬ እየባነንኩ ነበር የምኖረዉ፡፡ የመጀመሪያዉ በጣምም ሃብታም ባይባል ለኔ ከበቂ በላይ ሊይዘኝ የሚችለዉ አቅም ነበረዉ ከነበረዉ ገንዘብ ይልቅ ፍቅሩ ይግደለኝ፣ እንክብካቤዉስ ብትል፣ በተለይ በተለይ የትም ስንገባ የነበረዉ ክብር እመቤት የሆንኩ ያህል ነበር የሚሰማኝ ወንበር ስቦ አስቀምጦ፣ የመኪና በር ከፍቶ አዉርዶ አስገብቶ፣ … ስንቱን ልበልህ ከልቡ ነበር ግን ‹‹ ባሪያ ላመሉ … ›› እንደሚባል ልክስክስ ነበር፤

ሐሙስ 22 ሜይ 2014

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››: click here for pdf ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ በሊቅነታቸው፣ በቆራጥነታቸው፣ ለየት ባለ አስተሳሰባቸውና ለነገሮች በሚሰጡት አስደናቂ ምላሽ የሚታወቁ የትግራይ ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ እስካሁንም እርሳቸውን በተመለከተ ...

እሑድ 18 ሜይ 2014

ክፍል አምስት … … አጋጣሚ



ከመች ወዲህ ነዉ እንዲህ ማምሸት የጀመረችዉ? ከቤት እንዳትወጣ አላልኩሽም? ለመሆኑ ስንት ሰዓት ነዉ የወጣችዉ? ቆይ ስራ በቃኝ! ለተወሰነ ግዜ ማረፍ እፈልጋለሁ ብላ ሥራዋን በገዛ ፈቃዷ የለቀቀችዉ ለመዞር ነዉ እንዴ? እንደከብት እሷን ለመጠበቅ እኔ የግድ እዚህ መዋልና ማምሸት አለብኝ? …. … (ለጥያቄዎቿ መልስ የሚመልስላት ስታጣ ብቻዋን አዉርታ አዉርታ ሲበቃት ስልኳን መደወል ጀመረች፤ ) ደግሞ ስልኳንም ዘግታዋለች፡፡
ነይ እስኪ ወደዚህ ምንድን ነዉ አላማችሁ? ቆይ እስኪ እናንተ ከብቶች ናችሁ እንዴ ያለጥበቃ የማትኖሩት? አልበዛም እንዴ? (ቁጣዋ እየጨመረ መጣ የሚሰማት ሰዉ ግን አልነበረም፤) ምን ይዘጋሻል!
‹‹ እኔን ነዉ? ››
እና ማን አለ? እስካሁን የማወራዉ ለማን መስሎሻል?
‹‹ እስካሁን አዉሪ እንጂ አንዱም አይመለከተኝም፤ … … እኔኮ የቤቱ ጠባቂ እንጂ የሰዉ ጠባቂ አይደለሁም፡፡ ቆይ እስኪ ስራዬ ምንድን ነዉ? ገረድ ነኝ ወይስ እናንተ በተበጣበጣችሁ ቁጥር ሸምጋያችሁ ነኝ? ድርሻዬን አሳዉቁኝ …. ….›› ( በዚህ ቤት ዉስጥ ለመጀመሪያ ጊዜዋ ነዉ እንዲህ አይነት ቃላት ስትናገር፤ )

ማክሰኞ 6 ሜይ 2014

አንድ አድርገን: ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታች...

አንድ አድርገን: ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታች...:  ‹‹ ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታችሁን ለመታደግ በሃይማኖት ጸንታችሁ መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርጉ››   አለቃ አያሌው ታምሩ ሚያዚያ 23 ቀን 1983 የሰማዕቱ ቅዱስ ጊ...

ሰኞ 5 ሜይ 2014

I forget my English ደብተር

ወቅቱ በኛ ዘመን ነዉ ‹የኛን ዘመን› እንግዲህ ቆጥራችሁ ድረሱበት፤ ፍንጭ ለመስጠት ያክል ዛሬ የአማሪኛ ቋንቋን ከብሔሩ ተወላጅ ዉጭ ያሉ ተማሪዎች ‹‹ አማርኛ ›› ብሎ ከመጥራት በስተቀር መናገር እንደተጠመደ ፈንጂ በሚታይበት ሁኔታ እንዳለ ሁሉ እኛም እንግሊዝኛን ከA (ኤ) እስከ Z (ዜድ) ብቻ በሚመስለን ዘመን እንደማለት ነዉ፡፡ የቋንቋ ነገር ከተነሳ አይቀር አንድ ጓደኛዬ እዚሁ መዲናችን አዲስ አበባ ዉስጥ በሚገኝ የግል ባንክ አንድ ዘመዷ ተቀጥራ ለዋስትና ስትሄድ ወደ ህንፃዉ እንደገባች የህንፃዉ ትልቅነት ግራ ስላጋባት መረጃ ትፈልግና አንዷን የባንኩ ሰራተኛ መረጃ ትጠይቃታለች ባነከሯም (የባንኩ ሰራተኛ) በአማርኛ ቋንቋ ለጠየቀቻት ጓደኛዬ አማርኛ እንደማትችል ትመልስላታለች፡፡ ጓደኛዬም የምትሰማዉ ነገር ግራ ይገባትና ‹‹ እንዴት ነዉ የማትችይዉ?›› ብላ ትጠጥቃታለች፡፡
‹‹ በቃ አልችልማ ›› ብላ ግግም ያለ ምላሽ ትሰጣታለች፤
‹‹ እያናገርሽኝ ያለዉኮ በአማርኛ ነዉ ታድያ ይሄንን እንዴት ቻልሽ ወይስ መረጃ መስጠት በአማርኛ መስጠት አትችይም? ›› ትላታለች ፤
የባንክ ባለሙያዋም ‹‹ በቃ ተሳስቼ ነዉ››  ትልና አሁንም በአማርኛ ትመልስላታለች፤
እንግዲህ እንዲህ ቋንቋዉን እየቻሉ መናገር ለሚጠሉት ቋንቋ ‹መግባቢያ› ሳይሆን መዋጊያ የጦር መሳሪያ እየሆነባቸዉ ያለበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነዉ ያለዉ፡፡ (እግረ መንገዳችንንም የግድ እስካልሆነ ድረስ እንዲህ ዘርና ቋንቋ እየመረጡ የሚቀጥሩ መስሪያ ቤቶች ከአካሄዳቸዉ ቢመለሱ የሚሻል ይመስለኛል፤ መልዕክቴ ነዉ፡፡ )

እሑድ 4 ሜይ 2014

ክፍል ሁለት …. … የፀየሙ ገጾች (አዲስ አበባ)

  

ብዙ መልኮችና ብዙ ስሞች ያሉዋት አዲስ አበባ አንዱ መጠሪያዋ አራዳ ነበር፤  አራዳና አዲስ አበባ ተነጣጥለዉ የሚታዩ አልነበሩም፡፡ በአንድ ወቅት ታላቁ ሰዉ አቶ ይድነቃቸዉ ተሰማ ስለ አዲስ አበባ በሬድዮ ፕሮግራም ተጠይቆ ሲናገር እንዲህ ነበር ያለዉ፡- ‹‹ የአዲስ አበባዉ ስታድየም አሁን አለበት ቦታ እንዲሠራ ሐሳብ ሲቀርብ ኳስ ሜዳዉን ከከተማ ዉጭ አደረጋችሁት ተብለን ተወቀሰን ነበር፤ ›› እንግዲህ በወቅቱ አዲስ አበባ ምን ያህል ጠባብና ስንት ህዝብ ይኖርባት እንደነበር መገመት ቀላል ነዉ፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ስታድየምን ያህል ነገር ሲሰራ ከከተማ ወጥቷል ከተባለ የስልጣኔ ጥጓ ምን ያህል ድረስ እንደነበረ መገመትም አይዳግትም፡፡ በቅርቡ እንኳን በ 20 እና በ 30 አመታት ጊዜ ዉስጥ እንኳን የነበራትን ገጽ ብንመለከት አዲስ አበባ እንኳንስ የዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ ልትሆን ይቅርና ለዋና ከተማነት እንኳን የምትመረጥ አልነበረችም፤ ካረጁ ቤቶቿ እና ከፈራረሱ መንገዶቿ አንፃር፡፡ በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በ1879 ዓ.ም. የቆረቆሯት አጼ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ተነስተዉ የትናንትናዋን ባለጎፈሬዋን እና የዛሬዋን ‹ዉብና ድንቅ› እንዲሁም ሰፊ ከተማ በወቅቱ ከነበረዉ ጋር ለማነጻጸር ‹‹ ዕድል ›› ቢገጥማቸዉ ምን ይሰማቸዉ ይሆን? ያስብላል፡፡  
እንደዉ የሚሉትን ነገር ገምቱ ብንባል ዘና ለማለትና በዚያዉም ምሳ ነገር ለመጋበዝ የቀድሞዉን ‹‹ኢምፔሪያል›› የዛሬዉን     ‹‹ ጣይቱ ሆቴል›› ዉሰዱኝ ሳይሉ እንደማይቀሩ እንገምታለን፤ እኛም መቸስ የጠየቁትን አንነፍጋቸዉም እንወስዳቸዋለን፡፡ መቸስ ስለ ጣይቱ ሆቴል ከተነሳ አንድ እዉነት ልንገራችሁ፡- በራዲዮ የቀረበ ነዉ፤ እኔም ከ100ኛ ዓመት በዓል መዘከሪያ መጽሔት ላይ ያገኘሁት ነዉ፡፡
 ላዲላስ ፋራጎ ይባላል፡፡ ጋዜጠኛ ነዉ፡፡ላዲስ ፋራጎ ከለገሃር ባቡር ጣቢያ ተነስቶ ጣይቱ ሆቴል ይሄዳል፡፡ከጅቡቲ፣ከድሬደዋና ከአዋሽ ተሸክሞት ከመጣዉ አዋራና ላብ ለመገላገል ቸኩሎ ነበር፡፡
ከመኝታ ቤቱ ሲገባ ግሩም የሆነ የገላ መታጠቢያ ገንዳ (ባኞ) በማግኘቱ እጅግ ተደስቶ ቦዩን ጠራና ‹‹ ገላዬን ስለምታጠብ ገንዳዉን ሙላልኝ ›› ይለዋል፡፡
ቦዩም (አስተናጋጁ) ስንት ታንካ (ጀሪካን) ዉሃ ላስመጣልዎ ›› ይለዋል፡፡
ፈረንጁ ግራ ይገባዉና ‹‹ ገንዳዉን ሙላልኝ ነዉ የምልህ፡፡ ቧንቧዉን ክፈተዉ፡፡›› ይለዋል፡፡
 አሁንም ቦዩ ይመልስና ‹‹ ገላዎን መታጠብ ከፈለጉ የሚፈልጉትን የዉሃ መጠን ይንገሩኝ፡፡ ያንዱ ታንካ ዉሃ ዋጋ አራት ግርሽ (ጠገራ ብር ወይም ማርያቴሬዛ) ነዉ፡፡ ›› ይላል፡፡  (ገንዳዉን የሚሞላዉ ስድስት ታንካ (108 ሊትር) ዉሃ ነዉ፡፡) ላዲስላስ ፋራጎ ቀጠለና ‹‹ እንዴ? የቧንቧዉን ዉሃ በታኒካ ልክ ታስከፍላላችሁ ማለት ነዉ?›› ሲል ቦዩን ጠየቀዉ፤
ቦዩም ‹‹ አይደለም! ዉሃዉ የሚመጣዉ ከፍል ዉሃ ነዉ፡፡ ኩሊዎ (ተሸካሚ) ይላኩና ፍልዉሃ ሄደዉ ታኒካዉን በፈላ ዉሃ ከሞሉ በኋላ ተሸክመዉ ያመጡታል፡፡ አንድ ኩሊ ዳዉን 6 ታኒካ ዉሃ ይሞላዋል፡፡ ገላዎን አንዴ ታጥበዉ መለቅለቅ ከፈለጉ ደግሞ ተጨማሪ ታኒካ ዉሃ ማስመጣት ያስፈልጋል ›› አለዉ፡፡
‹‹ገንዳችሁ ላይስ የተተከለዉ ቧንቧ?››
‹‹ እንዳልኩዎት ዉሃዉ የሚመጣዉ ክፍል ዉሃ ነዉ፡፡››
ላዲስላስ ፋራጎ ገባዉ፡፡ ገንዳዉ ላይ የተተከለዉ ቧንቧ ለጌጥ ነበር፡፡

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...