እሑድ 7 ጁን 2020

ዕርገተ ሕሊና - የሀሳብ ከፍታ በዲ/ን ብርሃኑ አድማስ


"ዓረገ ውስተ አርያም ጼዊወከ ጼዋ፣ ወወሀብከ ጸጋከ ለእጓለ እመሕያው - ምርኮን ማርከህ ወደ አርያም ወጣህ፣ ለሰው ልጆችም ጸጋህን ሰጠሐቸው" /መዝ 67/8 ፤ 18/

ጌታችን ያድነን ዘንድ ሰው ሆነ፡፡ በዕለተ ትስብእቱም (ሰው በሆነባት ዕለት) ባሕርያችን አከበረ፡፡ በዚያች ሥጋችንና ነፍሳችንን በተዋሐደባት ቅጽበት ባሕረየ ሰብእ በዘባነ ኪሩብ በየማነ አብ ተቀምጧል፡፡
ሰው ሆኖም ሀፍረታችንና ውርደታችን ሁሉ ይቅር ይለንና አሳፋሪ ከመሆንም ያድነን ዘንድ እርሱ ስለእኛ ተዋረደ፣ የአይሁድን ርኩስ ምራቅ ታገሠ፤ ሐፍረትንም ሁሉ ንቆ ክብር ይግባውና ስለሁላችን ድኅነት ራቁቱን ተሰቀለ፡፡ ስለእኛ ሞተ፣ ተቀበረ፣ ተነሣ፣ በዐርባኛውም ቀን ክብር ይግባውና ዐረገ፡፡

ይህ ሁሉ ከጽንሰት እስከ ዕርገት ያለው ሰውን ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ ከዚያም ላቅና ከፍ ወዳለ ጸጋ ለማድረስ ነው፡፡ ከእነዚህ ጸጋዎች አንዱ ዕርገተ ኅሊና ወይም የሀሳብ ከፍታ ነው፡፡

 ይህነን ከፍታ በአጭሩ በሁለት ወገን ከፍሎ መመልከት ይቻላል፡፡ አንደኛው ለሰው የተሰጠውን ጸጋ ተረድቶ በሕግ በአምልኮ እርሱን በመከተል ወደ ሰማያዊ ምሥጢራት በመመንጠቅ ነው፡፡

ይኸውም አባታችን ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ከምድር እስከ ሰማይ ተዘርግታ በላይዋ እግዚአብሔር ተቀምጦባት መላእክት ሲወጡባት ሲወርዱባት እንዳየ ቅዱሳንም እንደ መሰላሉ ቋሚዎች ባሉ ብሉይና ሐዲስ፣ በመሰላሉ ላይ እንዳሉት ርብራቦች ደግሞ በምገባራት ሠናያት (ከጾምና ከጸሎት ሳይለዩ መልካም ተጋድሎን በየደረጃው በመጋደል) ወደ እግዚአብሔር በተጋድሎ ይጓዛሉ፣ ጸጋ እግዚአብሔርን፣ ትርጓሜና መሥጢራትን ተቀብለው ይዘው ይወርዳሉ፤ በትምህርትም ለሰው ዘር ያደርሳሉ፡፡ ይህ መንፈሳዊው ዕርገተ ኅሊና ነው፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ሁላችንንም የሚመለከተው ዕርገተ ኅሊና ወይም የሀሳብ የዕቅድ የተግባር ከፍታን የሚመለከተው ነው፡፡

ይህንንም በምሳሌ አስቀድሞ አስረድቶናል፡፡ በኦሪት ዘሌዋውያን እንደተጻፈው ንጹሐን ስለሆኑት እና ስላልሆኑት፣ ስለሚበሉትና ስለማይበሉት እንሥሣት ሕግን በሰጠበት አንቀጽ ላይ ስለዐሦች የተናገረበት ክፍል ሁላችንንም የሚመለከት ነው፡፡ የሚበሉት የዐሣ ዘሮች ቅርፊትና ክንፍ ያላቸው እንዲሆኑ ታዝዟል፡፡ የዚህም ምሳሌነቱ ግልጽ ነው፡፡

ቅርፊት ለዐሣዎች ራሳቸውን ከሌላ መርዛማ የባሕር ውስጥ አውሬ የሚጠበቁበት ነው፡፡ ክርስቲያንም አብሮት በዚህ ዐለም ከሚኖር የሰው የነገር፣ የክህደትና የጥላቻ መርዝ መጠበቅ ካልቻለ ተጓድቷልና ንጹሕ አይደለም ማለት ነው፡፡

ክንፋቸው ደግሞ መንሳፈፊያቸው የባሕሩ ወለል ላይ ከመንፏቀቅ የታደጋቸውና የባሕሩ ጠለል ድረስ ከፍ ብለው ተንሣፈው ከባሕሩ ውጭ ያለውን ዐለም እንኳ ለመቃኘት የሚያስችላቸው ሀብታቸው ነው፡፡ ክርስቲያንም በሚኖርበት ዐለም በመጨረሻው በዝቀተኛው ደረጃ መሬት ለመሬት ማለትም ምድራዊና ሥጋዊ ነገርን ብቻ በመከተል ራሱን ደካማ ማድረግ የለበትም፡፡ ወደ ክፍታ ብቅ ማለት መቻል አለበት፡፡

ስለዚህም በጥቅምና በክብር፣ በጌጥና በልብስ፣ በምግብና በመጠጥ፣ በቤትና በመኪና ፍላጎት ብቻ ናላው የሚዞር ወይም ለሚያገኘው ምድራዊ ነገር ብቻ የሚንገበገብ እንስሳ መሆነ የለበትም፡፡ ይልቁንም ከራሱ አልፎ ለሌሎች፣ የእኔ ከሚላቸው ተሸግሮ ሌሎች ለሚላቸው፣ ከሰው አልፎ ለፍጥረት ሁሉ የሚያስብ ደግ መሆን አለበት፡፡

ከጊዜያዊ አልፎ ለዘላለማዊው፣ ከቅርቡ አልፎ ለሩቁ ፣ ከምድራዊው ሕይወት አልፎ ለሰማያዊው፣ ከዛሬ አልፎ ለነገ እያሰበ የሚናገር የሚሠራ የሚያቅድ ከፍ ያለ መሆኑን መዘንጋት የለበትም፡፡
በባሕርይው ምሉዕ በኩለሔ የሆነው አምላክ ያረገው እኮ የባሕርያችን የእኛን ከፍታ ለመግለጽ እንጂ እርሱማ ሁልጊዜም ልዑል ነው፡፡ በሁሉም ያለ ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የተሸከመ እርሱ ነው፡፡

እንግዲያውስ ከዕርገቱ ከፍታን እንማር፡፡ የአነጋገር፣ የአስተሳሰብ የውይይት ባሕል ዝቅታ ይብቃን፡፡ ከወረድንበት አዲስ እንጦሮጦስ እንደምንም ተጎትተን እንውጣ፡፡
ከደንቁርና አዘቅትም ተንደርድረን እውጣ፡፡ ታላቂቱን ቤተ ክርስቲያን በእኛ ደንቁርናና አለማወቅ፣ አለማሰብና አለማቀድ አናሰድባት፡፡

ትልቅ ገደል ውስጥ መሆናችን ተገንዝበን ወደ ላይ ለመውጣት ከፍ ለማለት እንጣጣር፡፡ ከፍ ያደርገን ዘንድ ዐርጓልና ዝቅ ማለት ይበቃን፡፡ እንኳን ለዕርገተ እግዚእ  አደረሳችሁ፡፡

በራስ_መተማመንን (Self Confidence)


በራስ_መተማመንን (Self Confidence) ለማሳደግ የሚረዱ አስር ሙያዊ ምክሮች

 ለራስዎ ያለዎት ከፍ ያለ ግምት ሌሎች እርስዎን የሚያዩበት መንገድ ጥሩ እንዲሆን ከፍተኛ ሚና አለው። በራስ የመተማመን ስሜት ሲኖርዎትም በተሰማሩበት ሥራ ላይ የበለጠ ስኬታማ እንዲሆኑ ከፍተኛ እርዳታ አለው።
ምንም እንኳን በራስ መተማመን ላይ ተጽእኖ የሚያሳድሩት ምክንያቶች ብዙዎቹ ከእርስዎ ቁጥጥር ውጭ ቢሆኑም፣ በራስ መተማመንን ለመገንባት የሚረዱ ብዙ ነገሮችን ማድረግ ይችላሉ። እነዚህን 10 ስትራቴጂዎች በመጠቀም ያልዎትን በራስ መተማመን ከፍ አድርገው ችሎታዎን በትክክለኛው ሁኔታ ሥራ ላይ ማዋል ይችላሉ።

1. አለባበስዎ ጥሩ ይሁን (Dress sharp)።
የእርስዎ አካላዊ ገጽታ እና አለባበስ ላይ ከማንም ሰው በላይ እርስዎ የቀረበ እይታ እና ግንዛቤ አለዎት። ስለሆነም፣ ጥሩ ሆነው እንደማይታዩ በሚሰማዎት ጊዜ፣ ከሌሎች ጋር የሚያደርጉት የሃሳብ ልውውጥ ሂደት ውስጥ ምቾት እንዳይሰማዎት ያደርጋል። ስለራስዎ ገፅታ ግን መልካም አመለካከት ሲኖርዎ ምቾትዎ ይጠበቅና ከሰዎች ጋር የሚያደርጉዋቸው ግንኙነቶች ላይ ልበ ሙል ይሆናል። የራስ ገፅታን ጥሩ ለማድረግ የሰውነትን እና የገላን ንፅህና መጠበቅ፣ ፀጉርን እና ፂምን በቅጡ መከርከም እንዲሁም በወቅቱ ተቀባይ የሆኑ ፋሺኖችን በማዎቅ እና አቅም በፈቀደ መልኩ መከተል ይረዳል። ይህ ማለት በልብስ ላይ ብዙ ገንዘብ ማውጣት አለብዎት ማለት አይደለም። ነገር ግን፣ ብዙ ርካሽ ልብሶችን ከመግዛት ይልቅ፣ ጥቂት የተመረጡ እና ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ዕቃዎች መግዛት አለባበስን ጥሩ ለማድረግ ከመርዳታቸውም በላይ ለረጅም ጊዜ ዘመናዊ ሆነው እንዲቆዩ ስለሚያደርጉ ረዘም ላለ ጊዜ ወጪን ይቀንሳሉ።

«ደስተኛ ሕይወት»

ከጭንቀት ነፃ የሆነ «ደስተኛ ሕይወት» ለመኖር ወሳኝ የሆኑ #አሥር_የሕይወት_መርሆች

1. እራስህን ከሌላ ሰው ጋር አታፎካክር፦ ሁላችንም እንደ አሻራችን ሁሉ ባህሪያችን እና ፍላጎታችንም በጣም ይለያያል። ደስታን ከሚያጠፉ ምክንያቶች አንደኛው እራስን ከሰው ጋር ማፎካከር ነው።

2. አትኩሮትህ በሌለህ ነገር ላይ ሳይሆን ባለህ ነገር ላይ ይሁን፡- ደስተኛ ለመሆን ሁሉም ነገር ሊኖርህ አይገባም። በደንብ ካስተዋልከው አሁን ያለህ ነገር ደስተኛ ለመሆን በቂ ነው። ምክንያቱም አንተ ያለህን የሚመኙ ምስኪኖች ብዙ ናቸውና።

3. እራስህን ሁን፦ በዚህ ምድር ላይ ሌላውን ለመምሰል እንደመሞከር ከበድ ነገር ምን አለ? እውነተኛ ወዳጆችህ አንተን ባንተነትህ ይቀበሉሃል…..ከምንም በላይ እራስህን በመሆን ከራስህ ጋር ሰላም ፍጠር፡፡

4. ሁሉን ለማስደሰት አትሞክር፦ አንድ ነገር ስታደርግ ሰዎች ደስ እንዲላቸው ብለህ ሳይሆን ትክክለኛ እና አንተ ያመንክበት ነገር ስለሆነ ይሁን። ለሰው ሳይሆን ለህሊናህ ኑር።

5. የውሸት ደስታን አትፈልግ፦ በውሸት ደስታና በእውነተኛ ደስታ መካከል ትልቅ ልዩነት አለ። የውሸት ደስታ ጊዜያዊ በሆኑና ከውጪ በምናገኛቸው ነገሮች የሚመጣ ሃዘናችንን ለጊዜው የሚጋርድ ጊዜያዊ ማስታገሻ ሲሆን እውነተኛ ደስታ ግን ሃሳባችን፣ አላማችንና ምግባራችን ሲጣመር የሚፈጠር ስሜት ነው። ሃዘን እና መከራችንን ሳንደብቅ የምንጽናናበትም ነው፡፡

6. ማንን እንደምታገኝ አታውቅምና ለሁሉም ሰው ቅን ሁን፦ ሰዎችን አትና፤ በየትኛውም አጋጣሚ ለምታገኛቸው ሰዎች ትክክለኛውን ነገር አድርግ፡፡

7. መለወጥ የማትቻለውን ነገሮችን ተቀበላቸው፦ ከአቅምህ በላይ በሆኑ ነገሮች እራስህን አታስጨንቅ። ከአቅምህ በላይ የሆነውን ነገር ለአምላክህ/ለፈጣሪህ ስጠው።

8. የራስህ እውነተኛ ወዳጅ ሁን፦ ራስህን መውደድ ተለማመድ፤ የሚገርመው ሰዎች እራሱ ሊወዱህ የሚችሉት አንተ በመጀመሪያ እራስህን መውደድ ስትችል ነው። እራስህን ሲያጠፋ ይቅር በማለት፣ ሲደክም በማበርታት፤ ሲሳካለት በማሞካሠት ተንከባከበው፡፡

9. መልካም አስብ መልካም ተናገር፦ በመጀመሪያ ሰው ያስተሳሰቡ ውጤት መሆኑን እመን፤ አሁን የምንኖረው ህይወት ያመለካከታችን እና ያስተሳሰባቸን ውጤት ነው። ይህን ካወቅክ አስተሳሰብህን በጥንቃቄ አጢነው። ደስተኛ ለመሆን የተመረጠ አስተሳሰብ ሊኖርህ ይገባል።

10. ለምን እንደምትኖር እወቅ፦ ህይወት ማለት የተሰጠህን ሃላፊነት ለመጨረስ የተሰጠችህ ጊዜ ናት። ሃላፊነትህ ምንድን ነው? በህይወትህ ማድረግ የምትፈልገው ነገር ምንድን ነው? መልሱን ካወቅክ ለህይወት ያለህ አመለካከት ይቀየራል፡፡

📌❇️ ደስተኛ ህይወትን ለሁላችንም ይስጠን ! መልካም የጤና ጊዜ!!!

ምንጭ - (ቶማስ እንደፃፈዉ፣ ፅሁፉ ከዶክተር አለ የተወሰደ)

እያንዳንዱ ትልቅ ነገር ትናንሽ መነሻዎች አሉት

እያንዳንዱ ትልቅ ነገር ትናንሽ መነሻዎች አሉት

ተፈጥሮ በኡደት (Process) የተመላች ናት፡፡ ዘመናትን በጊዜ ቀመር አስልታ ከአንዱ ምዕራፍ ወደ ሌላኛው ታሻግራለች፡፡ የኡደት ስሌትዋ ከትልቅ ወደ ትንሽ ሳይሆን ከትናንሽ ወደ ትላልቅ የሚያመራ ነው፡፡

የሰው ልጅ የዕድገት ለውጥ ዓላማ በተፈጥሮ የወረሰውን እምቅ ኃይል ከከፍተኛ ደረጃ ላይ ማድረስ ነው፡፡ ኤልሳቤጥ ሃርሎክ የተባለች የሳይኮሎጂ ምሁር እንደገለጸችው ሰዎች በአእምሮ ፤ በአካል ከሌሎች የተሻሉ ሆነው ለመገኘት የሚያደርጉት ጥረት ወደ ዕድገት ለውጥ ግብ ለመድረስ የሚደርጉት ጥረት ስለሆነ እነዚህን ጥረቶቻቸውን እውን ለማድረግ ይችሉ ዘንድ ዕድሉ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡

እዚህ ላይ ትልቁ ጉዳይ ሰዎች እራሳቸውን ለማሻሻል እምቅ አቅምና ችሎታ ካላቸው ከወዴት ነው የሚጀሚሩት የሚለው ነው፡፡ ብዙዎቻችን በስራችንና በህይወታችን የምንፈልገውንና የምንሻውን ያህል ውጤታማ መሆን ያልቻልነው ዕቅዶቻችንንና ስኬቶቻችንን ከታች ከትንንሽ ነገሮች ስለማንጀምራቸው ነው፡፡ ቀድሞ የሚታየን ትልቁ ስዕል እንጂ ወደ ትልቁ የስኬት ጎዳና ለመድረስ ከትንሽ ነገር መጀመር እንዳለብን አንገነዘብም፡፡ ከዚህ በታች ከትንንሽ ነገር ተነስተን ወደ ትልቁ ስኬት ለመጓዝ የሚረዱንን ነጥቦች እንመለከታለን፡፡

ዸራቅሊጦስ (መንፈስ ቅዱስ)


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖታዊ ሥርዓት መሠረት የዛሬዋ እሁድ በዓለ ጰራቅሊጦስ ይባላል።

 "ወላጆች_እንደሌላቸው_ልጆች_አልተዋችሁም" (ዮ.ሐ14፥18)

✍️ጰራቅሊጦስ፡- ቃሉ ግሪክ ነው፡፡ ጰራቅሊጦስ ማለት

#መጽንኢ በእምነት የሚያጸና፣
#መንጽሒ ከኃጢአት የሚያነጻ፣
#ናዛዚ ያዘኑትን የሚያረጋጋ፣
#መስተፍስሒ፣ የተጨነቁትን የሚያስደስት፣
#ከሣቲ ምስጢርን የሚገልጽ ማለት ነው፡፡

#ጰራቅሊጦስ፡- መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የጰራቅሊጦስ በዓል ታሪክም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም የሚሠራውን ሥራ ከጨረሰ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ አባቴ እሄዳለሁ (አርጋለሁ) ሲላቸው ደነገጡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስም መደንገጣቸውን አይቶ👉 (ልባችሁ አይደንግጥባችሁ በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ ማለት ባባቴ ቤት በመንግሥተ ሰማያት ብዙ ማዕርገ ሀብታት አለ)

ዓርብ 5 ጁን 2020

ሕይወትን እንደ ንሥር አሞራ ኑር!


ንስር አሞራ ፀሐይን ቀጥ ብሎ ማየት የሚችል ወደ ፀሐይ አቅጣጫ ጨረሩን እያየ መብረር የሚችል ብቸኛው ፍጡር ነው። ሌሎች ቁራዎችና ጭልፊቶች 100 ወይም 200 ሆነው ከበው ሲጮሁበት ወደ ፀሐይ እያየ ከፍ ብሎ ይበራል። ሌሎቹ ፍጥረቶች ወደ ፀሐይ እያዩ መብረር ስለማይችሉ ይጠፋባቸዋል!!
- ንስር ከሰው አይን 8 እጥፍ የተሻለ ማየት ይችላል፣
- ንስር ከ 2.30-3 ሜ ይረዝማል፣
- ንስር ከ5-7 ኪሎሜትር ያለን ለማደን የሚፈልገውን ነገር በደንብ ለይቶ ማየት ይችላል፣
- ንስር ለአደን እስከ 120 ኪሎሜትር አካሎ ይበራል፣
- ንስር መጠለያ ከሌለበት አካባቢ ሆኖ ኃይለኛ ዝናብ ቢመጣ ወደላይ በመምጠቅ ከደመና በላይ በሮ ዝናብና ወጀቡን ከስር ያደርጋል እንጂ በዝናብ አይቀጠቀጥም፣
- ንስር አድኖ እንጂ ጭራሽ የሞተ አይበላም፣
- ንስር ሲታመም ፀሐይን አተኩሮ በማየት ነው ህክምና የሚያገኘው፣
- ንስር 340° ማየት ይችላል። ከ360° በአንድ እይታ 340° ማየት ይችላል። ሰው 180° አካባቢ ነው ማየት የሚችለው፣
- ንስር አሞራ እስከ 70 አመት የሚኖር የእድሜ ባለፀጋ ነው ካልክ ልክ ነህ። ግና 70 አመት ሙሉ በደስታ ከመኖሩ በፊት በእድሜው አጋማሽ ማለትም በ35 - 40 ባለው እድሜው ላይ ከባድ ነገር ይገጥመዋል።
የመጀመሪያው ፤
ምግቡን ለማደን የሚገለገልበት ጥፍሮቹ ከመጠን በላይ ስለሚያድጉ ምግቡን ከመሬት ላይ ማንሳት ያቅተዋል፣
ሁለተኛው ፤
አጥንትን ሳይቀር መስበር አቅም ያለው አፉ (መንቁሩ) ስለሚታጠፍና ስለሚጣመም ምግቡን እንደወትሮው መመገብ ይሳነዋል፣
ሶስተኛው፤
ክንፉና በአካሉ ላይ ያሉ ላባዎች ስለሚከብዱት ያ ሰማየ ሰማያትን እየሰነጠቀ ይበር የነበረው ሀይሉ ይክደዋል።
እነዚህ ሶስት ከባድ ነገሮች ንስር አሞራ በእድሜው አጋማሽ የሚያጋጥሙት ከባድ ችግሮች ናቸው። አሁን ንስር አሞራ ያለው ምርጫ ሁለት ነው።
1ኛ. ካረጀ አካሉ ጋር ዝም ብሎ በመቀመጥ ሞቱን መጠበቅ ?
2ኛ. አምስት ወር የሚፈጅ ስቃይና መከራ ያለበት መስዋዕትነትን ከፍሎ ቀሪውን 35 አመት በደስታ ማሳለፍ ?
የመጀመሪያውን ከመረጠ በእድሜው አጋማሽ ይሞታልና ታሪኩ እዛ ጋር ያበቃል።
ሁለተኛውን ምርጫ ከመረጠ ግን እነዚህን አምስት መስዋዕትነቶች ማለፍ ይኖርበታል።
፩ኛ. ከፍተኛ ተራራ ላይ በመውጣት የብቻውን ጎጆ ይቀልሳል።
፪ኛ. ጎጆ ከቀለሰ በኋላ የመጀመርያ ስራዉ የአፉን መንቁር ከአለት ጋር በማጋጨት ነቅሎ ይጥላል።
፫ኛ. ይህን ካደረገ በኋላ አዲስ መንቁር ይወጣለታል፡፡ መንቁሩ እስኪያድግ ድረስ ታግሶ በጎጆው ምንም አይነት ምግብ ሳይመገብ መቆየት ግዴታው ይሆናል፡፡
፬ኛ. አዲስ መንቁር ከበቀለለት በኋላ በአዲሱ መንቁሩ የገዛ እግሩን አሮጌ ጥፍር ነቃቅሎ ይጥለዋል።
፭ኛ. አዲሱ የእግር ጥፍር ከበቀለለት በኋላ ደግሞ ይህንን አዲስ ጥፍር እንደ መሳርያ በመጠቀም በሰዉነቱ የተጣበቁትን እንዳይበር እንቅፋት የሆኑትን የገዘፉና ያረጁ ላባዎችን ነቃቅሎ ይጥላል። በምትኩ አዲስ ላባ ያበቅላል። ይህን 5 ወር በዚህ መልኩ በጀግንነት ከተወጣ በኋላ እንደገና ራሱን በራሱ ወልዶና ወጣት ሆኖ ወደ ንስሮች መንደር ብቅ ይላል፡፡
ንስር እጅግ ግዙፍ፣ እጅግ ጠንካራ፣ በሰማይ ከሚበሩ ሁሉ እጅግ የተለየ ባህርይ ያለው፣ ረጅም እድሜ መኖር የሚችል ሲሆን ድንቢጥ ግን ይህን ልዩ ፍጥረት ትፈታተነዋለች። ድንቢጥ ንስርን ፈተና የምትሆንበት ክንፎቹ ሥር በመግባት በመንከስ ነው።
ንስር ምንም እንኳን ድንቢጥ ፈተና ብትሆንበትም በቀላሉ እጅ አይሰጥም፤ በከፍታ በመብረር ብቃቱ ተጠቅሞ ወደ ላይ ይበራል። ድንቢጥ ንስር ሊደርስበት የሚችለው ክልል መብረር አቅሙ የላትምና ትወድቃለች። ድንቢጥም ፈተና ከመሆን አልፋ ትፈተናለች ትወድቃለችም።
ወዳጄ ሆይ:
ችግር ገጠመኝ ብለህ ያዙኝ ልቀቁኝ አትበል ፣ ችግሬ ...ችግሬ ... እያልክም ነጠላ ዜማ አትልቀቅ ፣ ፊትህንም ችግር ፊት አታስመስል ፣ ጥቅም ላይ እያፈጠጠ የሚከተል ሰው በበዛበት አለም ላይ መውደቅህን መጥሪያ ካርድ አታሰራበት ፣ መራብ መጠማትህን ፖስት ለማድረግ አትቸኩል ፣ መገፋትህን እንደ ትልቅ ነገር ቆጥረህ ኡ.ኡ.. አትበል ፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን የተሻለ ነገር ለመስራት ጣርና ሕይወትህን ቀይር!
ሰው ነህና የሥነፍጥረት ሁሉ ገዥ ተደርገህ ተፈጥረሃልና ሃይልህን፣ ጥበብህን ተጠቀም።
እንደ ድንቢጥ የሚፈታተንህ ዘረኝነት፣ ብሔርተኝነት፣ ፖለቲካ፣ የእምነት ጽንፈኝነት፣ አክራሪነት፣ ሙስና ወዘተ ሊጥልህ ከክብርህ ዝቅ ሊያደርግህ ይጥራልና በከፍታ ብረር፣ በአስተዋይነት ተንቀሳቀስ፣ የዘረኝነት መንደር፣ የብሔርተኝነት የፖለቲካ ጎጥ ውስጥ አትርመጥመጥ፣በሙስና ለመበልጸግ በእምነትህ ልትከፋፈል እጅ አትስጥ።
ለነዚህ ሥትል ከሰውነት ክብርህ ዝቅ አትበል። ሰው ሆነህ እንደተፈጠርክ ሰው ሆነህ ኖረህ ሰው ሆነህ እለፍ።
ፈተናዎችን እንደ ንስር በጥበብ እለፍ።

"አንዱ ስለ ሁሉ ቤዛ ሞተ"

"አንዱ ስለ ሁሉ ቤዛ ሞተ"

መምህር ዘለአለም ወንድሙ
፪ቆሮንቶስ 5: 14
አንዱ:- ማን ነው? አካላዊ ቃል ወልድን ነው። ከሶስቱ አካል አንዱ ወልደ እግዚአብሔር ነው
በምን ሞተ:- ለባህሪው ሞት የማይስማማው ጌታ በፈቃዱ ሞተ። ነፍሱን ሊጥላት እና ሊያነሳት ስልጣን አለውና ዮሐንስ 10: 17
የሞተው በፍቅሩ ነው ሮሜ 5: 8 ሐጢያተኞች ሳለን
ፍቅር ኋያል ወልድን ከመንበሩ ሳበው እንዲል
በግፍ ተሰቅሎ ሞተ
ዮሐንስ15: 22
ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ብዙ የመጽናኛ ቃል እየተናገረ፣ ድውያንን በተአምራት፣
መዝሙር 68: 4 በከንቱ የሚጠሉት በዙ፣ በረቱ
በስጋ ሞተ
፩ ጴጥሮስ 3: 18 ሞት በሚስማማው በስጋ ሞተ በባህሪው/በመንፈስ ህያው ነው
ለምን እንደሞተ:-
ጠላችን ዲያብሎስን ሊሽርልን ነው ለ5ሺ 5 መቶ ዘመን ወደ ሲኦል ስንጋዝ የነበርነውን የሰው ልጅ ነጻ ያወጣ ዘንድ ሞተልን
እብራዊያን 2: 14- በሞቱ በሞት ላይ አለቃ የነበረውን ከስልጣኑ ሰይጣንን ሊሽረው ሞተልን።
በሥጋ ምክንያት የሞተውን አዳምን በስጋ ማርያም አድሮ ከርሷ ተወልዶ፣ መከራ ተቀብሎ ፣ ሞቶ አዳነን።
ዮሐ3: 16 የዘለአለም ህይወት እንዲሰጠን ሞተ
ከሲኦል ባርነት ሊያወጣን ሞተ
ቆላሲስ 2: 14 በመከራ ሳለን የሚቃወመንን የእዳ ደብዳቤ ሊሽር፣ ነጻ ሊያወጣን፣ ሞትን በመስቀል ላይ ሊጠርቀው እኛን ነጻ ሊያወጣን፣ ህይወት ሊሰጠን፣ ሞተልን።
በህገ ልቡና የነበሩ ሌዋውያን ካህናት፣ ቅዱሳን፣ የተሰውት የእንስሳት መስዋእት ሊያድነን አሌቻለም። ይህ አልተቻላቸውም።
ትንቢተ ሆሴእ 13: 14 በትንቢት እንደተናገረ የሞትን መውግያ ሠበረ፣ ድል ነሳው።
ሞታችንን በሞቱ ሊያስወግድልን ሞተ
ሮሜ 15
ከርሱ አስቀድሞ አንዳችም ሃይል አልነበረም።
ዮሐንስ 11: እኔ ትንሣኤ እና ህይወት ነኝ እንዳለ ከሞት ቀስቅሶ በስጋ ሞቶ ህይወት ሰጠን።
፩ ቆሮንቶስ15: 3 ስለኛ ሃጢያት በሥጋ ሞተ በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ፤ ሞቶ አልቀረም። መቃብሩን ባዶ አድርጎታል። ሞት ሊያስቀረው፣ ሊያሸንፈው አልቻለም።
ኢሣይያስ 25 :8 - ሞትን ለዘለዓለም ይውጣል፣ይሽረዋል፣ ያስወግዳል ተብሎ እንደተጻፈ
እንባችንን አበሰ፣ ስድባችንን ያስቀር ዘንድ ተሰደበ፣ መከራችሁን በቃችሁ ሊል መከራ ተቀበለ፣ ሞተልን፣ የትንሣኤ በኩራት ይሆን ዘንድ ተነሳ።
፩ቆሮ15: 20
እኛም የማይቀረውን ሞት ስንሞት ምተን አንቀርም እንነሳለን። ከሞት በኋላ መቃብር እንዳለው ከመቃብር በኋላ ትንሣኤ አለ።
ለእርሱ ክብር እንድንነሳ ሞተልን ፩ ቆሮንቶስ ፭: 14
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንድንኖር ሞተልን የአይናችንን አምሮት የሥጋችንን ፍላጎት እንዳንኖር ውድ ዋጋ ከፈለልን።
፩ ቆሮንቶስ 6: 19
ስለዚህ በሥጋችን እንድናከብረው የሞት ዋጋ ከፈለልን
ሮሜ 8: 12 የሥጋና የደሙ እዳ አለብን።
የምንሰማው ቃሉ፣ የምንጠራበት ሥሙ፣ የተቀበልነው ሥጋና ደሙ፣ እዳ አለብን።
በፈቃዳችን ፈቃደ ሥጋችንን ለፈቃደ ነፍሳችንን አስገዝተን ልንኖር ይገባል። ሐብታችን፣ እውቀታችን፣ ሠውነታችን ጣኦት ሊሆንብን አይገባም። ከዚህ እስር
ኤፌሶን 5: 14 አንተ በሐጢያት አለም መካከል የምትተኛ በንሰሐ ንቃ ከአእምሮ ሞት ንቃ የእግዚአብሔር ፍቅር ልብህን ይግዛው።
ከእርሱ ጋራ ለዘለዓለም እንድንኖር ስለኛ ሞተ።
፩ ተሰሎንቄ 5: 9
የህይወትን አክሊል እንድንቀዳኝ ሞተ
እግዚአብሔር ለምን ወደክ ሳይሆን ለምን አትነሳም ነው አለማው። ንሰሐ አዘጋጅቶልናል። በንሰሐ እንድንነሳ፣ በሕይወት አብረን እንድንኖር ሞተ።
በሞት እንድንመስለው እንዲሁ ደግሞ በትንሣኤው ልንመስለው ይገባናል።
ስለዚህ የተከፈለልንን ዋጋ አስበን ወልድ ወደዚህ አለም የመጣበትን አላማ እያሰብን በንሰሐ ሁላችንም ከወደቅንበት ኃጢአት እንነሳ፣ በህይወት እንመላለስ፣ በክብር ለዘለዓለም የተከፈለልንን ዋጋ የሚመጠን የጽድቅ ኑሮ እንኑር።

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...