1. ሰው መምረጥ
*በብቃቱ፣ በክህሎቱ፣ በተሠጥኦው፣ በትምህርት ዝግጅቱ፣ ወዘተ ከአላማችን ጋር የሚቀራረብ ግባችን ለማሳካት የሚያስችል ሰው መምረጥ አስፈላጊ ነው።
ተቋማት የሥራ እድልን ከመፍጠር ጎን ለጎን ተቋምን ሊያሳድጉ ስኬትን ሊያስመዘግቡ የሚችሉ እና የአገርን ሥም በአለም መድረክ ጭምር ሊያስጠሩ የሚችሉ ሠራተኞችን ከጅምሩ ከላይ በተዘረዘሩት መሥፈርቶች መመልመል ይኖርባቸዋል።
ይህ ሠው ታድያ ግላዊ ጉዳዩን ወደ ጎን ያደረገ የአገር ፍቅር ለወገን ክብር ያለውና ሥራውን እሴት ጨምሮ የሚሰራ ተደርጎ መሠራት አለበት።
የማይረካ፣ የመማር፣ የመሥራት፣ ሁሌም ጀማሪ የሆነ፣ ሁሌም ለአዲስ ነገር ጉጉ የሆነ፣ ዘወትር ለውጥን አሻግሮ የሚያይ፣ ሁሌም ለሥራ የሚሮጥ፣ ጥማት ያለበት ሰው መምረጥ ይኖርብናል።
ሰዉ በመምረጥ
ሂደት ዉስጥ መዘንጋት የሌለብን ነገር ምናልባት ከቦታዉ ጋር የሚሄድ ካልሆነ በቀር አለበለዚያም የትምህርት ዝግጅቱ ከመለያየቱ
በቀር ‹‹የማይረባ›› የሚባል ሰዉ እንደሌለ ልብ ልንል ይገባል፡፡