ማክሰኞ 18 ሴፕቴምበር 2018

COMPETENCY/ብቃት

ብቃት


መግቢያ

ብቃት የሚለዉ ፅንሰ ሃሳብ ዘርዘር አድርገን ስንመለከተዉ በማንኛዉም የሥራ ዘርፍ እና ሙያ በየትኛዉም የሀላፊነት ደረጃ ላይ የሚገኝ መሪ እና ሰራተኛ ሊኖረዉ የሚገባ ዕዉቀት ፣ክህሎት እና አስተሳሰብ ወይም አመለካከትን አጣምሮ የያዘ ድምር ዉጤት ነዉ፡፡አንድ ሰራተኛ ወይም የሥራ ኃላፊ/መሪ ብቃት አለዉ ለማለት ሦስቱንም በአንድ ላይ አሟልቶ መገኘት ግድ ይለዋል፡፡አንዱ ባልተሟለበት ሁኔታ ይቅርና የላቀ ዉጤት ማሰመዝገብ የተሰጠን ኃላፊነት በተሟላ መንገድ ለመፈፀም አይቻልም፡፡አንዱ ለሌላዉ መጋቢ ብቻም ሳይሆን ተደጋጋፊም ናቸዉ፡፡ አንዱ በጎደለበት ሌላዉ የተሟላ ሊሆን ስለማይችል ብቃት ብሎ ነገር የለም ማለት ነዉ፡፡ስለዚህ አንባቢ ስለብቃት ሲያስብ ሶስቱንም ማሟላት ግድ እንደሆነ መገንዘብ ይኖርበታል፡፡
ይህንን ፅሑፍ ከኮሎኔል ፈቃደ ገብረየስ መፅሐፍ "የአመራር ሳይንስና ጥበብ" መካከል ሳገኝ ስለተጠቀምኩበት ለሌሎችም ባጋራዉ ትዉልዱ በየሄደበት የአገልግሎት ቦታ ሁሉ ስለሚያገለግሉት አገልጋዬች ብቃት ማነስ እያነሳ ሲተች እና ሲማረር ባይ እኛም በያለንበት ሥፍራ ጥራት እና እርካታ ያለዉ አገልግሎት ብንሰጥ ይህንን ቅሬታ መቅረፍ የተሻለ አገልጎሎት ለመስጠት ያስችለናል ብዬ በማሰብ ነዉ፡፡ አንባቢ በዚህ ብቻ ሳይገደብ ማንበብ ሙሉ ሰዉ ያደርጋልና የኚህን ምሁር መፅሐፍ ሙሉዉን ብናነብ እኔ ያልዳሰስኳቸዉ መፅሐፉ የሚዳስሳቸዉ ጥልቀት ያለዉ እዉቀት እንደሚያገኙ ለማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡
ዕዉቀት፣ ክህሎት እና አመለካከት ለሥራችን ብቻ ሳይሆን ለህይወታችንም እጅግ ጠቃሚ ነዉና አትኩሮት ሰጥተን በማንበብ ወደ ተግባር እንድንቀይረዉ እያሳሰብኩ በዚህ አጭር ፅሑፍ ብቻ ሳንወሰን ሌሎችንም መፅሐፎች በመመርመር የተሻለ ሥራ እንድትሰሩ የተሻለ ህይወት እንድተመሩ እመኝላችኋለሁ፡፡
መልካም ንባብ፡፡

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...