እሑድ 31 ሜይ 2015

የህይወት ታላቁ ፈተና “ጠላትህን ዉደድ”



ክርስቲያን ሆንን አልሆንን፣ወደድንም ጠላንም፣በየትኛዉም የእምነት አስተምህሮ ዉስጥ ብንሆንም በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርተ ወንጌል ዉስጥ ለማንኛዉም የሰዉ ልጅ ጥሩ የመሆን ፍላጎት ሊሆን ከወደደ የሚገደደዉ ወይም ሊቀበለዉ ግድ የሚለዉ መሰረታዊ ነገር አለ፤ (ፀሐፊዉ ሊዮ ባኩታ በገፀ ድሩ እንዳሰፈረዉ)
ü  በአቅራቢያችን የሚገኙ ጎረቤቶችን መዉደድ አይደለም፣
ü  የሚወዱንን ስለሚወዱን አፀፋ ለመመለስ መዉደድ አይደለም፤ ነገር ግን
v   ጠላቶቻችንን፣ የሚጠሉንን፣ በህይወት መኖራችንን የማይፈልጉትን፣ የእኛን ማግኘት ፣የእኛን ጤና መሆን፣ ወጥቶ መግባት ፣ ሰርቶ ማግኘት ፣ ነግዶ ማትረፍ፣ ዘርቶ መቃም፣ ወልዶ መሳም፣… በጭራሽ የማይፈልጉትን መዉደድ፡፡
ይህ አባባል ፣ ይህ ድርጊት፤ የዚህ ፅሑፍ ዋና መልዕክት ነዉ “ ጠላትህን ዉደድ ” የህይወታችንም ትልቁ ፈተና ፣ ሰዉ የመሆናችን እና የእምነታችን መለኪያዉ ነዉ፡፡
ይህ መልዕክት ትልቅነቱ ∕ ጥቅሙ ⁄ ለምን አስፈለገ?
ይልቁንም ሃይማኖተኛ ለሆነዉም ላልሆነዉም ለምን መልዕክቱ መተላለፍ አስፈለገዉ?
( የዚህ ፅሑፍ ዋና ዓላማ የእምነት ትምህርት ማስተማር ላይ ያዘነበለ አይደልም፤ ምንም እንኳን የሃይማኖት ትምህርት ማስተማር ችግር ባይኖረዉም እና ይልቁንም ክብር ያለዉ እና ዋጋዉም እጅግ እጥፍ ድርብ ክፍያዉም በሰማይ የሆነ ቢሆንም  ) ዋናዉ መነሻዬ በመላዉ ዓለም እና በሁሉም የሰዉ ዘር መካከል የጠፋ ትልቅ ቁምነገር (ሀብት) ከመሆኑ የተነሳ እንጂ፡፡“ ጠላትህን መዉደድ ” እምነት ቢኖርህም ባይኖርህም ችግር የሌለዉና ልታደርገዉ የሚገባ ቁልፍ ጉዳይ ነዉ፡፡ ( ነገር ግን በዓለም ላይ ትልቁ ችግር ፣ ዓለምም ያጣችዉ እና የጎደላት ጉዳይ ቢኖር ጠላትን መዉደድ ነዉ፡፡)

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...