ክፍል አንድን ለመዳሰስ
እንደሞከርነዉ ሁሉ ክፍል ሁለትን እንዲህ እንቃኘዋለን፤ መልካም ንባብ፡፡
2.5. የሰብአዊ
ግንኙነት ክህሎት #
አንድ ተቋም
የሚፈጠረዉ እና የሚንቀሳቀሰዉ በሰዉ ነዉ፤ በእርግጥ ለሰዉ ሥራ ማቀላጠፊያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ቁሳቁሶች
ሰወችን ይደግፉ ይሆናል እንጂ በራሳቸዉ ሰዉን አይተኩም፡፡ ስለሆነም በየትኛዉም የስልጣን እርከን ይሁን በየትኛዉ የስራ መስክ
ላይ የሚሰራ ሰራተኛ የሰብአዊ ግንኙነት (የሰዉ ለሰዉ ግንኙነት) ክህሎት አካል የሆነዉን የስሜት ብልህት (Emotional Intelligence/Quotient) ሊያዳብር ይገባዋል፡፡
Øአንድ መሪ የግሉንና የሌሎች ሰዎችን ስሜት የማወቅና
የመቆጣጠር እንዲሁም ለራሱና ለሌሎች ሰዎች ስሜት ሊሰጥ የሚገባዉን ትክክለኛ ምላሽ ለይቶ የማወቅ ግላዊ እና
ማኅበረሰባዊ ብልሀት ችሎታ ሊኖረዉ ይገባል፡፡
የሰብአዊ
ግኙነት ማለት መሪዉ የሚመራዉን ሰራተኛ በአግባቡ ስሜቱን የማወቅ እና የመረዳት ችሎታ ሲሆን ሰራተኛዉ ደግሞ የሚያስተናግደዉን
ደንበኛ፣ አብሮት የሚሰራዉን ሰራተኛ፣ እንዲሁም የሚመራዉን የቅርብ አለቃዉን ስሜት የመረዳት ችሎታ ማለት ነዉ፡፡ ይህ ካለ መሪዉ ሰራተኛዉን የማበረታታት፣
ለስራ የማነሳሳትን፣