ዓርብ 7 ሴፕቴምበር 2012

“ወይንና ቀበሮ”


በአንድ ወቅት ነው አሉ ቀበሮ እስከማንዘሮቿበወይን ፍሬ ትተዳደራለች ልጆቿን ታሳድጋለች(የልጆቿን ነፍስ ትታደጋለች) እናም ከዕለታት አንድ ቀን የወይኑ ጌታ ለወይኑ ቅፅር/ አጥር/ ቀጠረለት ማስገቢያ ቀዳዳዎችን ደፈነ፤ ቀበሮ መግቢያ አይደለም የትንኝ መግቢያ መንገድ አልተገኘም ነበር፡፡ ነገር ግን ከጊዜ ብዛት ሾልካ የምትገባበትን ቀዳዳ መንገድ አገኘች መግባትም ጀመረች ነገርግንእንደድሮው ወይም እንደምትጠብቀው አልነበርም ወይኑ ከመብሰሉ የተነሳ እንዳይበላሽ በአውሬም እንዳረጋገጥና እንዳይበላ ተደረጎ በባላ ከፍ ተደርጎ ተሰቅሏል፡፡ እስከ ልጆቿ የመጣቸው ቀበሮ በመደናገጥ መዘየድ ጀመረች ይባስ የተራቡ ልጆቿ እየተንጫጩ እያቀለሱአስጨነቋት የነርሱ ርሃብና ልቅሶ ደግሞ የበለጠ ግራ አጋባት፡፡ የወይኑን ዘለላ እያየች ምራቋን ትውጥ እየዘለለች እየፈረጠች ለማውረድ መጣር ጀመረች፤ ጥረቷ ግን ሊሰምር አልቻለም የወይኑ ተክል ረጅም ቁመቱ አጭር ሆነባት፡፡ ዘለለች ዘለለች …. ምንም ሊሆንላት አልቻም፡፡ ተስፋ ስትቆርጥ ወደ ልጆቿ ዘወርበማለት እንዲህ አለቻቸው “ወይኑ አልበሰለምና አይረባም እንሂድ ሌለ የሚበላ ጥሩ ምግብ እንፈልግ” አለቻቸው ነገር ግን እንኳን ጥሩ ነገር ረሃባቸውን ሊያስታገስ የሚችል ምግብ አልሰጠቻቸውም፡፡ወይንን “አይረባም” ብሎ ስም ከማጠፋት በስተቀር፡፡
ይህ የቀበሮ ህይወታችን ዛሬ ዛሬ በአብዛኛውህብረተሰብ ህይወት ይንጸባረቃል ይህ ማለት ግን “የማይረባን “ ነገር አይረባም ከማለትየዘለለ አማራጭ ባይኖረውም የማይረባን ነገር የሚተካ ረሃብን የሚያስታግስ መልካም ነገር እስካልመጣ ድረስ ከመንደር ወሬነት ባለፈ መፍትሔ አይሆንም ምን አልባት የተወሰነ ነገር ያመለክት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ትችት ለበዛበት አገራችን መፍትሔ መጠቆምና ሥራ መሥራት እንጂ የሚረባት ጣት መቀሰርና አይረባም ማለት አይፈይዳትም፡፡ ለምሳሌ አይረቡም ከሚባሉት ተቋት ፓርላማው አይረባም፣ ሲኖዶሡ/ቤተክህነቱ/ አይረባም፤ ትምህርት ሚኒስትር /የትምርት ፖሊስው/ አይረባም፤ ማኀበረ ቅዱሳን አይረባም፣ የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቨዝን አይረባም፣EBS አይረባም፣ ESAT አይረባም፣  የመንግሥት ሚዲያ አይረባም፣የግ(የእንቶኒ) ጋዜጣ አይረባም፣ የግል ዩኒቨርስቲዎች አይረቡም፣ወንዶች አይረቡም፣ ሴቶች አይረቡም፣ መ/ርእገሌ አይረባም፣ ፓስትረ እገሌ አይረባም፣ የነ እገሌ የዕምነት ተቋም አይረባም፣ አርቲስት እገሌ አይረባም፣ህገ መንግስቱ አይረባም፣ ዳኞች አይረቡም፣ ጠበቆች አይረቡም፣ ብሄራዊ ቡድኑ አይረባም፣ አትሌት እገለወእገሊት አይረቡም፣NGO አይረባም፣ የሃይማኖት ተቋም አይረባም፤ ዕድር አይረባም፤ ዕቁብ አይረባም፣ ፌዴሬሽኑ አይረባም፣ የቻይና እቃ አይረባም፣የእንትና መንግሥት አይረባም፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ፓሊሲው አይረባም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አይረቡም፣ የፖለቲካ (የዲሞክራሲ) ስርዓቱ አይረባም፣ የፍርድ ሂደቱ አይረባም፣ አስተሳሰባችንም አይረባም….. ወዘተ ብቻ የማይረባ ነገር የለንም ምክያቱም ከምናመሰግነው ይልቅ የምንነቅፈው ስለሚበዛ ነገር ግን ከዚህ ነቀፋ በስተጀርባ ጸሐፊው የታዘበው ነገር ሰልነበረ ይህን ጽሁፍ ለመፃፍ ተገዷል ብዙዎችን አይረባም ከማለት ባሻገር ምን ፈየድን ምን መፍትሔ ምንስ የተሻለ ነገር አቀረብን? ምንም፡፡ አወራን እንጂ ምን ሰራን?ምንም ለአገራችን ማደግ ለህብረተሰባችን መለወጥ ስራ/ድርጊት/ እንጂ ወሬ አላጠረውም፡፡ ማውራት ማስረጃ አይጠይቅምና እናወራለን ሥራ ግን ትልቅ አቅምና ትልቅነት ይጠይቃል ታዲያ ለምን ራሳችንን አንመዝንም? በመሥራት!
እስኪ የወቀስነውን የትምህርት ፖሊስ እንመልከት እንኳን እኔ/እኛ/ መንግሥትም እንደማይረባ መሻሻል እንዳለበት ያምናል ነገር ግን አይረባም ከማለት የዘለለ ምን አደርግንለት? ምንም፡፡ ነገር ግን ይህ የትውልድ ምንጭ የዜጋ መቅረጫ ሥፍራ ሊወራበት ሳይሆን ሊሰራበት የሚገባ ነበር፡፡ በቃ! መንግሥት ሊሠራ የሚችለውን አደረገ ከኛስ የሚጠበቅ ነገር የለም? ትናንት የተማርንበት ነገር ልጆቻችን ዕውቀትን የሚቀስሙበት የትምህርት ፖሊስያችን የፖሊስ ለውጥ ከእኛ ይጠብቃል ከወሬ ይልቅ ሥራ ይናፍቀል፡፡ ፓርላማውም እንዲሁ ገብቶ የሚተኛ የሚያስቅ ነገር ሲነገር የሚባንንና የሚያጨበጭብ እጁን የማውጣትና የማውረድ የሚቆጠር ሳይሆን ውሳኔ ሰጪ፣ ጥሩ አቋም ያለው፣ ራዕይ ያለው፣ የተቀመጠበትን ዓላማ ግብን የሚመታ ማኀበረሰብን ማዕከል ያደረገ ሥራ የሚሰራ የፓርላማ አባል ያስፈልጋል ከዳር ተቀምጦ አይረባም ከማለት ረሃባችንን ሊያስታግስ ስደታችንን ሊቀንስ የሚችል መፍትሔ የሚያመጣ አባላት ያስፈልጉናል፡፡
ሲኖዶሱ/ቤተክህነት/ አይረባም ሲባል ሁለት አሥርት ዓመታት አስቆጥሯል ታዲያ መፍትሔው ሃያ ዓመት ሙሉ ስአለመርባቱ ማውራትነው ወይስ የሚረባበትን መንገድ መቀየስ፣ አንዲረባ ማገዝ፣ ወይስ ምን ይሻላል ባለው አቅም መልካሙንም የሚስነቅፈውን እስከአሁን ሠራ ከአሁን በኋላስ የዘመንድ ቤት፣ የሙስና የተዘፈቀ፣ የተኩላ የመሸሺጊያ… እንዳሆነ ይቀጥል ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ደም እንደተመሰረተች “የሲኦል ደጆች አይችሏትም” ተብላ በኛ ዘመን የወላድ መካን ሆና ታንባ? ታልቅስ? ክፉ ነገር አውርተንባት ተጠቋቁመንባት ለጠላት አሳልፈን እንስጣት? በሌሎች የዕምነት ተቋማትም በመስኪድ የፀሎት ሥርዓቱን የሚመራው፣ ምዕመኑን የሚስተዳድረው፣ የሚያስመልከው፣ መጋቢው …..መንገድ ሲስት አርአያነት ሲጎለው እናውራ? አይረቡም እያልን እንቀመጥ? ወይስ ድራሻችንን እንወጣ ? እንዴት የተቻለ ፖሊሲ፣መተዳደሪያ ደንቦችን፣ እንቅረፅ እንሳተፍ ውጭ ከማውረት ጠጋ ብለን የሚረባ ነገር ረሀብን የሚያስታግስ ከሽሽት ከስደት የሚመልስ ለአምልኮ እግዚአብሔር የሚጋብዝ ሥራ እንስራ፡፡
ማኀበረ ቅዱሳን ማኀበሩ እንደሚለው ከ120,000 በላይ አባላት በመላው አገሪቱ እና በውጭው ክፍለ ዓለም ከሰንበት ትምህርት ቤት እስከ ግቢ ጉባኤ /በዩኒቨርስቲዎች/ ያሉት ሲሆን በቤተክርስቲያኑልማታዊና መንፈሳዊ ግልጋሎቶችን ሲሰጥ ሃያ አመቱን ደፍኗል፤ ማኀበሩም እንደሚያምን በድካም ውስጥ ጠንካራ ነገሮችን ሰርቷል “ኃይልን በሚሰጠን በክርስቶስ ሁሉ እንችላለን” በማለትም አሁንም በስራ ላይ ይገኛል::ከመምሪያው ኃላፊዎች ጀምሮ ብዙዎቹ አይረባም ይሉታል ታዲያ ይገኛል ከመመሪያው ኃላፊዎች ጀምሮ ብዙዎች አይረባም ይሉታል ታዲያ ይህን የመሰለ በጎ ሥራ እየሰራ ያ ተቋም የቤተክርስቲያን ደጆች ሳይዘጉ፣ከወድቀታቸው እያንሰራሩ የአብነት ትምህርት ቤቶች ቀኑ ሳይጨልምባቸው... እንዴት ይርባ? እንዴት ወደተሻለ አኳኃን ይሻገር? ጥያቄው እዚህ ጋር ነው ጥቄቶች “ይዘጋ” ይላሉ ይህ የጠላት ወሬ ካልሆነ በቀር እንኳንስ ይህን የመሰለ ተግባር ያለው ቀርቶ ሃሳብ ይዞ የመጣ ይቋረጥ ሳይን እንዴት ይቀጥል በሚባልበት ዘመን አይመከርም፡፡ እሺ ምን ይደረግ? ሥንል የሚሻሻልበትን መንገድ እንጠቁም ይህ ነው አገርን፣ ተቋመን፣ ህብርተሰብን… የሚጠቅመው ችግሩን እንኳንስ እኛ ተቋሙም ያምናል ጠንካራ ነኝ ብሎ አይከራከርም፡፡
የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን አይረባም፡፡ አዎ! አይረባም ታዲያ መፍትሔው ምንድን ነው? ሜዳ ገብተው ሲጫወቱ አትርቡም አንበላቸው ወይስ ከሜዳ ውጭ ሜዳ ከመግባታቸው በፊት አሰልጣኝ እንቅጠርላቸው? ዳጎስ ያለ ደሞዝ/አበረታች/ ይከፈላቸው? የሚጎድላቸውን እናሟላላቸው? በቂ የስልጠና ሥፍራ እናዘጋጅላቸው?...  ወይስ ቁጭ ብለን ስለ አለመርባታቸው እንነጋገር? የቱነው የኳስ ፍቅር ርሃባችንን የሚያስታግሰው? የቱስ የአገራችንን ስም በተሸለ ውጤት የሚያስጠራው? መነቃቀፍ ወየስ መደጋገፍ?
የቻይና ዕቃ አይረባም በኢህአዴግ ዘመነ ሥልጣን ቻይና 81 ብሔር ትሆናለች ብለው ይተነትናሉ ቀልደኞች እውነትም ከገጠር እስከ ከተማ ቻይናዊ የማይገኝበት ድንበር የለምያገባት የስራ ዘርፍ ሻይና ፓስቲመንገድ ላይ መሸጥ ብቻ እስኪመስለን ድረስ ሁሉም ተቆጣጥረውታል አብዛኛው ወደ አገር ወስጥ የሚገቡ ቃዎች የትውልድ አገራቸው ቻይና መሆኑን መርካቶን በእማኝነት መጥራት አሰገዳጅ አይደል ሁላችንም ምስክሮች ነንና፡፡ነገር ግን ይህቺ ለአሜርካን ለአውሮፓ አምርታ የምታቀርብ አገር ወደ ኢትዮጵያ የምትለካቸው ዕቃዎቿ አይረቡም ይባላ?እንደያውም ካጅማ የተባለው የመንገድ ስራ ተቋራጭ ከአዲስአበባ ደጀን ያለውን መንገድ ሲገነባ በጫማዋ ያቃጠለችን አንሶ በመንገዷ ልታቀጥለን መጣች የሚል ምሬት አዘል ቀልድ ሲቀለድ እንደነበር የቅርብ ትዝታ ነው፡፡ አዎ አይረባም ነገር ግን ምን ይደረግ? የማይረባ ነገር ምርት አገር እንደልሆነች የኢኮኖሜ ዕደገቷ ምስክር ነው ችግር የመግዛት እቅማችን የፈጠረው አቅርቦት ነው፡፡ ደሃ ከመሆናችን የተነሳ የመግዛት አቅም አጠረን አዎ ቻይና የሚረባውንም የማይረባውንም እንደ መግዛት አቅማችን ትልካለች ብዙዎቻችን የመግዛት አቅማችን የወረደ ከመሆኑ የተነሳ የምትልከው አይረባም፡፡ ባለመርባቱ ቻይና ተጠያቂ ናት? የሚረባ ነገር እንድትልክ ምን ይደረግ? እንዲህ በደፈናው የቻይና እቃ አይረባም ማለት የተሟላ ወቀሳ አለመሆኑን የአሜሪካና የአውሮፓ ገበያ ምስክርነው፡፡ እነ ኢትዮ ቴሌኮም፤ እነ መብራት ኃይል፣ የውሃናፍሳሽ፤ መንገድና ትራንስፖትስ አትረቡም ሥንላቸው  እነርሱም እንደማይረቡ ያውቁት ይሆን? ልብ ይስጥልን፡፡
ለማመላከት ያህል ይህን ያህል ፀሐፊው ከተጋራ ቀሪውን ደግሞ አንባቢያን ልብ እንደምትሉት ተስፋ ያደርጋል፡፡ አዎ ሁሉም ቦታ ችግር አለ ሁሉም ቦታ የማይረባ ነገር አለ እኛስጋ ረሃብ የሚያስታግስ፤ ከስደት የሚመልስ፤ ዕምባ የሚያብሰና ጫጫታውን የሚቀንስ ምን መፍትሔ አለ? ወይንስ “ችግር አለ፤ “አይረባም” እያሉ ማውራት ብቻ ይሆን? የተፀናወተን ችግርን የሚፈታው ችግርን መጠቆም ብቻ ሳይሆን መፍትሔን ማምጣት ነውና፡፡
እነዚህ የጠቀስናቸውና ሌሎችም አይረቡም ብለን ተስማማን ግን ለዚህ ማህበረሰብ እነረሱ ካደረጉት አስተዋጽኦ የተሻለ ያደረግነው ነገር ምን አለ? ለዚህ ማህበረሰብ ከቻይና ልብስና ጫማ ውጭ እኛ ምን ሰጠነው? ምን አጫማነው /ምን አለበስነው?/
ለዚህች አገር ባለው ነባራዊ ሁኔታ ካለው “መንግሥት” ምን የተሻለ ነገር አደረግን ባለመርባት ውስጥም እያስተዳደረ እያለ የምንተችው መንግሥት ነው: ለቤተክርስቲያንስ ቢሆን ከማኃበረ ቅዱሳን በተሻለ ምን ፈየድንላት? ካለው የትምህርት ፖሊሲ የትኛው ተቋም ትምህርት ሊያደርስ ማን ቻለ? የተሻለ ፖሊስና አሠራር ያለው እኔ ነኝ ይበል ተንፍሱ ተያዩበት ተችቱ፣ አመስግኑ፣ አቅጣጫ አመልክቱ፣……(ልብ በሉልኝ ቤተመንግስትም ሆነ ቤተ ክህነት ይረባልም አይረባምም ማለት አልፈልግም መለኪያ የለኝምና፣ ራሴን ማግለሌ ከፍርሐት እንዳልመነጨ ይታወቅልኝ ተከባበሩ እንጂ አትፈራሩ እግዚአብሔርን ፍሩ ሠውን አክብሩ፡፡)
God bless Ethiopia!

‹‹ጌታ አግኝቶሃል?››

-->
-->
ሁለት ሰዎች በካፍቴሪያ ተቀምጠዋል በዚህ መሆን የዕለት ተዕለት ሥራቸው ነው ጨዋታቸውን ድምፃቸውን ከፍ እያደረጉም መጫወትም ልዩ ምልክታቸው ነው፤ ቶሎ ገብቶ የመውጣት ልምድ የላቸውም ብዙ ሰው ይተዋወቃሉ ይግባባሉ ለጨዋታቸውም ይጋብዛሉ፡፡ ምናልባት አብረው ሻይ ቡና ብለው ከሆነ በይሉኝታ ሂሳብ ከፋይ እርስዎ ይሆናሉ ፀባያቸውን ካላወቁ፡፡
ከዕለታት በአንደኛው ቀን እንደልማዳቸው ተቀምጠ ትኩስነገር እየተጎነጩ ሳለ አንድ ለግላጋ ወጣት እነርሱ ከተቀመጡበት ፈንጠር ብሎ ይቀመጣል እርሱም ቡና ያዛል፤ ስልክ ይደወልለታል ተንቀሳቃሽ የመነጋገሪያ ሥልኩን አውጥቶ "ሃሎ" ይላል ደዋይም ያወራዋል ሰላምታ ይለዋወጣሉ ወጣቱም "እግዚአብሔር ይመሰገን ደህና ነኝ" በማለት ስለጤናውም ስለ ሥራም ሌላም ሌላም ያወሩና ሥልኩ ይዘጋል፡፡
ከሁለቱ የካፍቴሪያ ተስተናጋጆች ይገረማል! ይገርማል! ይባባላሉ፡፡ ወዳጄ ይህ ቃል ከጆሮው ጥልቅ ትላ  ለወጣት ይልቁንም ብቻውን ለተቀመጠ አጨዋች ለሌለው የሚገርም ነገር ሲገኝ እጅጉን ይገርማል ሳንቲም ቅጭልታ እና የሚገርም ነገር ጀሮውን የማይገዛው የለምና፡፡
እነዚህ ሁለት አጥማጆች የጣሉት መረብ ሠው ያዘላቸው ለዚያውም ወጣት እግዚአብሔር የሚያመሰግን፤ ትህትና የተላበሰ፤ ብቻውን የተቀመጠ፤ ….. ሰላምታ ተለዋውጡ እርሱም እንደልማዱ እግዚአብሄርን ይመስገን ብሏቸው ሳያስበው ከብቸኝነት ወደ ሶስተኛ ሰው ተቀላቀላቸው “ደስ ይላል …. በዚህን ሰዓት ከጐረምሳ አንደበት እግዚአብሔር ሲመሰገን” ወዘተ ይሉትና ያሞጋግሱታል ያቺን በስልክ ሲነጋገር “እግዚአብሔር ይመስገን” ብሎ የተናገራትና ካአፉ ነጥቀው በማውራት (ለነገር መነሻ ወይም መግቢያ) ሲያደርጓት፡፡
እነርሱ በዚች ትንሸ ቀዳዳ ገብትው ያጣደፉት ገቡ በመሃልም እነዚህ ወጣቶች ይሰብኩት ጀመር ከሚያነሷቸውም ቃላቶች መካከል “ጌታ አግኝቶሃል?” የሚለው አንድና ዓብይ አጀንዳቸው ነበር፤ይኸው ለግላጋ ወጣት እግዚአብሔርን አመስጋኝ “የጌታ ልጆች” መሆናቸው ይገባዋል፡፡ አልተጣላቸውም አልተቃወማቸውም….በጸጥታ ያዳምጣቸዋል አንዳችም  ቃላት ከአንደበቱ አይወጣም እነርሱ ግን እየተቀባበሉ ቃላት ይወረውራሉ ተናግረው ተናግረው ሲጨርሱ ልጁ ምንም አይልም ቢሉት አሁንም አንዳች ቃላት አይናገረም ተደናገጡ እርስ በርስ ተያዩ እርሱንም አዩት ዝም ሏል አንዳችም ክፉ ነገር ከአፉ አይወጣውም የተለየ ነገር አጋጠማቸው በዚህ ቤት እንዲህ ዓይነት ባነሱ ቁጥር የሚያጋጥማቸው ዓይነት  ባህርይ ዓይደለምና የርሱ ፀባይ ሌላው ተሰማምቷቸው ጌታ ይባርካችሁ ብሎ የሚወጣ ወይም በጌታ የሚባርክ ሲሆን ሌላኛው ወገን ደግሞ  ተሳድቦ “ጌታ ይገሰፅህ” ብሎ የሚወጣ በዛዋል፡፡ ይህ ወጣት ግን እግዚአብሔርን ከማመስገን በቀር አንዳች ነገር አላገኙበትም ጌታ እንዲባርከው ወይም ጌታ እንዲገስፀው፡፡
በዋዛ ሊለቁት አልፈልጉምና “ምን ትላለህ” አሉት
“ምኑን?”
“ስለጌታ፤”
“ስለጌታ ምን?”
ድፍን ቅል ሆነባቸው ቢሉት ቢሰሩት ቢከረኩሩት አንዳች ነገር አልገናገር አላቸው፡፡
“ወንድሞቼ ሥለምን እንደምታወሩኝ:ምንስ እንደምትፍልጉ አልገባኝም ምንስ ፤ማንንስ ትፈልጋላቸሁ?በዚህ የተቀመጣችሁት እኔን ፍለጋ ነውን?” ይላቸዋል፡፡
“ወንድማችን የምናወራህ ስለ ጌታ ነው ሥለ ኢየሱስ ጌታ መሆን”
“አዎ ኢየሱስ ጌታ መሆን”
“በጌታ በኢየሱስ እመን ጌታ ያድንሃልና”
“አዎ ያድናል አምናለሁ!”
ጨዋታቸው እንዲህና እንዲህ እየደራ ድምፃቸው ከፍ እያለ ተመልካችን ቀልብ እየገዛ ከሶስት ወደ አራትነት እየጨመረ ንግግሩ እየከረረ በካፍቴሪያነት ወደ ኤማሁስ መንገድነት ተቀየረ ሥብከቱ ዳራ መረብ ተዘረጋ አንም ዓሣ ግን ወደ መረቡ አልገባም መረባቸው ወደ ባህር ግን ከመወርወር ግን አልቦዘኑም፡፡ ለዘብ እያሉ ድምፃቸው እየወረደ ሥሜታቸው እየበረደ መጣ “ለማንኛውም ጌታ ይወድሃል….”፤ “ጌታ ይባርክህ”፤ “መዳን በጌታ ብቻ ነው፤ “በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ”……ወዘተ የሚጠቀሟቸው ጥይቶች ነበሩ፡፡
ይኽ ደካማ የመሰለ ሰው፤የማይናገር ሰው መናገር ጀመረ “ሞኝ ካመረረ...” እንደሚባለው ማለት ነው በጥያቄ በቃላት ያጣድፋቸው ጀመር፡፡
“ወንድቼ ጌታ አገኝቶሀል ነው ያላችሁኝ?”
“አዎ!”
“እናንተንስ አግኝቷችኋል?”
“እኘ የጌታ ነን …….” በልበ ሙሉነት
“ለነገሩ የጌታ ልጅ መሆናችሁን አለባበሳችሁ፣ ደፋርነታች፣ወዛችሁ ……. ይናገራል” ከነረሱ ግን በተራቸው የሚመልስ ጠፋ ዝምታ ነገሰ እርሱ ከመናገር ሌሎች ተመልካቾች በተመስጦ ከማዳመጥ እነዚያም ሁለት ባልንጀሮች ግራ በመጋባትና እጃቸውን በአፋቸው ላይ በመጫን ከማዳመጥ አልቦዘኑም፡፡
“አንድ ነገር ልጠይቃችሁ እስኪ ዕድሜዬ ሥንት የሚሆን መስላችኋል?”
እነርሱም የሚመስላቸውን ገምተው ነገሩት “ጥሩ የሚገርማችሁ ይኸን ዘመን ሙሉ ጌታን አውቀዋለሁ፤ አይደለም ጌታን እናንተንም አውቃችኋለው በሥራችሁ በቃላቶቻችሁ …… የጌታ ልጅ መሆናችሁን በሥራችሁ ግን አይደለም….. ለመሆኑ ከእኔ ምን ትፈልጋላችሁ?....በዚህ የሆናችሁት ከጌታ ልታገናኙኝ ነው?...ወንድሞቼ እኔ ሥራ አለኝ ጌታ ደግሞ ሥራ ያለውን አይፈልግም ሥራ ላይ ያሉትን አይደለም የሚጠራው ሥራ የፈቱትን ነው…..ቅዱስ ጴጥሮስን በጠራው ጊዜ ያገኘው ዓሣ ማጥመዱን ትቶ ሥራ ፈትቶ በተቀመጠ ሰዓት ነው እኔ እድሜ ዘመኔን የጌታ ነበርኩ አሁንም ነኝ ወደፊትም ከርሱ የሚለየኝ የለም እናንት ግን ስራ ፈታችሁ በመርቢቷ ላይ ቁጭ ብላችኋልና ኑ ለጌታ ታስፈልጉታለችሁ ኢየሱስ ጌታ ነው ጌታም ብቻ አይደለም የጌቶች ጌታ፡ የዓለም መድኃኒት: የአብ የባህርይ ልጅ:ወልደ አብ ወልደ ማርያም: የሰውን ልጅ ለማዳን በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ተወስኖ ወዲዚህ ምድር የመጣ ደግሞ ለፍርድ ወደዚህ ዓለም በግርማ ሞገስ በክ ትስብዕት የሚመጣ አምላክምነው: ጌታ ብቻ አይደለም ሰው አይደለም ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ እንጂ: ሠይጣን አዳምን ለማሳት የእባብን ሥጋ እንደለበሰ ኢየሱስ ክስቶስም አዳምን ለማዳን የሠውን ልጅ ሥጋ የለበሰ…..” 
በዚያ ሥፍራ ዝምታ ነገሰ አግራሞት ጨመረ::
“ወንድሞቼ ከእኔ የምትፈልጉት አለን?” በዚህ ሆናችሁ እኔን ነው ወይንስ ጌታ ትፈልጉታላችሁ? …. አንድ ነገር ልንገራችሁ በዚህ ቁጭ ብላችሁ ጊዜአችሁን በዋዛ በፈዛዛ ሥታባክኑ አባቶቻችሁ ሲያርግ ያዩት ጌታ በዚህ እንዳተቀመጣች ለፍርድ መጣልና ንቁ ንስሐም ግቡ ልባችሁን መልሱ መንገዳችሁንም አቅኑ...” ብሏቸው የቡናውን ሂሳብ ከፍሎ ወደየት እንዳገባ ሳይታወቅ ከፈታቸው ተሰወረ፡፡
ይህን ታሪክ በኢየሩሳሌም ጉዳና ላይ ሐዘን በነገሰበት ሰዓት ስለተሰቀለውና ሥለምተው ኢየሱስ ክርስቶስ ልባቸው ተነክቶ እየተጫወቱ ሲጓዙ እንደ ነበሩትና በመንፈስም ራሱ በመሃላቸው ተገኝቶ እየተጫወቱ ሲጓዙ እንደነበሩትና በመንፈስም ራሱ በመሃላቸው ተገኝቶ ሲያጫውታቸው ሲያፅናናቸው ሲያበረታታቸው እንደነበረው የኤማሁስ መንገዶኞች ታሪክ ይመስላል ሉቃስና ቀላዮጳ ምንም እንኳን ልባቸው ተነክቶ እያዘኑ እየተከዙ በመንገዳቸው ቢያወሩት ያ የተሰቀለው ማን እንደሆነ ገና አላወቁም በመሃላቸው ተገኝቶም ያወረቸው አልተረዱትም የአገሬ ሰው 'ለቀባሪው አረዱት' እንደሚባለው ከራከሩት ነበር እንጂ:: እነዚህም ወንድሞቼ ምንም እንኳን ደጋግመው በመንገዳቸው በህይወታቸው በመቀመጫቸው በመድረካቸው…….ወዘተ ቢያወሩት ቢጫወቱት ገና ጌታ ምን እንደሆነ አላወቁትም ጌታ ነው ሲሉ ጥቂቱን አብዝቶ ሲመግብ ተመልከተው ባዕለ ጸጋ ነው ብለው፤ ተዓምራቱን (ለምፃምን ሲያነፃ ጎባጣ ሲያቀና ሽባ ሲተረትር፤ አጋንንት ሲያወጣ) ተመልከተው ለማድነቅ ነው:ግን ይኸን ሁሉ መንገድ ይኸን ሁሉ ዘመን ሲከተሉ ከባለፀግነቱ (ጌታነቱ)፤ ከተዓምር ሰሪነቱ በስተቀር አምላክ መሆኑን አላመኑም አላወቁም ለዚህ ነው “አማላጅ” ብለው የሚሟገቱት ሎቱ ሰብሐት፡፡
አንባቢ ሆይ! መቸስ በመንገድህ በመቀመጫህ፤ በህይወትህ…….ወዘተ እንደዚህ አውቅልሃለሁ ባይ: እኔ የምልህን ብቻ ሥማ እኔ የምሰጥህን ብቻ ተቀበል የሚልህ ብዙ ነው ሠላምህን ነስቶ ሰላሙን ካልተቀበልከኝ ብሎ የሚያስገድድህ በግህን ውሻ ነው ብሎ ሊያስጥልህ የሚያባብልህ: ... ብዙ ነውና ተጠንቀቅ፡፡ ሲጠይቁህ ለመመለስ የተዘጋጀህ ሁን በከንቱ የምትበሳጭ ለመስማት ብቻ የማትፈልግና በደህና የምሮጥ አትሁን እወቅ ጠይቅ ስለምታምነው ነገር ጠንቀቅህ እወቅ ሰዎች ሲናገሩ ግራ እየገባህ ራስህን የምትወዘወዝ ብቻ አትሁን የምትወዘውዘው ራስህ ይታዘብሃልና፡፡
እንግዲህ ወገኔ በየመንገዱ በየመስሪያ ቤቱ በየሻይ ቤቱ እንዲህ የተቀመጡ “ወንድሞች” አይታጡምና እንጠንቀቅ የሚገርመው ይህ ሰው ሌላ ቀንም ብቻውን ቡና ለመጠጣት ወደዚህ ቤት ሲመጣ ሶስት ሆነው ተቀምጠው አገኛቸው እነርሱም ተመልክተውት ለሶስተኛው ጓደኛቸው አወሩለት ዝ ባለ ድምፅ የማያያቸው የማይሰማቸው መስሏቸው እርሱ ግን ቡናውን ጠጥቶ ሂሳቡን ከፍሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
ሲወጣ ግን አንድ ነገር አላቸው “በዕድሜ ዘመኔ ይኸንን ጆርዬን ተሸክሜው ሲሄድ ጆሮዬ ይሰማል የእናንተም አንደበት ይናገራል” ብሏቸው ወጥቶ ሄደ፡፡
ምን ማለት ነው ተርጉምልን እንዳይሉ እርሱ በዚያ የለም፤ ወንደሞቼ ዛሬም የሚናገረውን የሚሰማውንም ተሸክመውት የሚናገሩበትን ብቻ እንጂ መስሚያቸውን የይጠቀሙበት በርከት  ብለዋልና እኛም ከነርሱ ወገን እንዳንሆን ለመናገር የዘገየን ለመስማት ግን የፈጠንን እንሁን፡፡
ጊዜ ጊዜን እየተካ ዘመኑ ይፈጥናል ይኸው ወጣት እንደተለመደው ወዲዚህ ቤት ይመጣል ቡና ሊጠጣ ሂሳቡን ከፍሎ ሊወጣ እነዚያም ጓደኛሞች ከሶስት አራት ሆነው እዛ አገኛቸው፡፡ እነርሱም መግባቱን ተመለከቱ ሶስተኛው ሰው ወደብቸው ወጣት በማምራት እንደተለመደው ወደ ወንበሩ እያለከተ “ሠው አለው?” ይለዋል ይኽም ወጣት በፈገግታ እየቀለደ “ለእኔ የሚታየኝ የለም” ይለዋል
“ምናልባት የተያዘ ከሆነ ብዬ ነው”
“የአራት ኪሎ ወንበር ሳይሆን የካፍቴሪያ ወንበር ስለሆነ ተቀመጥ” ይለውና ይቀመጣል ሠላምታም ይለዋወጣሉ እንግዳው ሰው “ጨዋታውን” (ሥብከቱን) ይጀምራል፡፡ ወደጓደኞቹ በጣቱ እያመለከተ “ባለፈውኮ ጓደኞቼ ሥለአንተ አውርተውለኝ በጣም ገርሞኝ …..” እያለ ሲቀጥል “እናንተ ሠዎች ለምን አተውኝም እኔ ጌታን አውቀዋለሁ አምነወለሁ…እኔ የማምን ከሆነ ኢየሱስ ጌታ ነው፤ ኢየሱስ ያድናል፣….. ወዘተ ሥትሉኝ አንዳች ነገር ካልተቃወምኳችሁ ሥለምን ትፈራረቁብኛላቸሁ ልታሳምኑኝ ነው ወይስ ልታስቱኝ እኔ ክርስቲያን (ኦርቶዶክስ ) ነኝ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እንዳምን ከሆነ ጥረታችሁ እኔ የጌታን አዳኝነት የኢየሱስን ጌትነት አምናለሁና ኢየሱስ ጌታ ነው ሥትሏቸው አይደለም ነቢይ ነው የሚላችሁ በዚያ በዚህ ቤት በአፍአ (በውጭ) አሉላችሁ ወደነርሱ ሂዱ ቢያምኑላችሁ ዋጋ ታገኛላችሁና” ብሎ የቡናውን ሂሳብ ከፍሎ ወጣ::
አዎ! ለምንድን ይሆን እነዚህ ወንድሞች ያመነውን የሚያሳድዱ? ለማሳመን ወይስ ለማስካድ? እነርሱስ እርስ በርስ በተገናኙ ቁጥር ሥለሰው አውርተው ከሚገረሙ ይልቅ ስለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት አውርተው የማይደነቁትና የማይደመሙት? መቼስ ይህን እዚህ ወንድሞች ሥራ ፈተው ከተቀመጡበት መርከብ ላይ መጥቶ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ የሚያገኛቸውና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የራሱ የሚያደርጋቸው? 
የእናንተን አላውቅም ይኼ የእኔ ጥያቄ ነው፡፡
 አንባቢ ሆይ! እስኪ ህይወታችን ወደኃላ ወደ ትናንት እንመለስ በትናንትናው ዕድሜያችን በትናንትናው ህይወታችን በትናንትናው ማንነታችን ምን አደረግን? ምን አሳለፍን? ዛሬስ ምን እያደረግንበት ነው? ነገስ ምን ልናደርግ ተዘጋጅተናል?(ሁለት ሶስት አራት…… ሆነን በተቀመጥን ጊዜ ሰዓቱን ምን ተጠቀምንበት? ምን አወራንበት?) ዕውቀታችንንስ ዕምነታችንንስ ራሳችንን ምን ተጠቀምንበት? ለሰው ሥናወራ ራሳችንን ምን አልነው? ሰዎች እንዲያምኑ “የጌታ” እንዲሆኑ ከአልባሌ ቦታ ርቀው የጌታ እግር ሥር በጌታ ቤት እንዲገኙ ቃሉን እንዲሰሙ በጌታ እንዲያምኑ ግድ ንላቸው እኛ የት ቆመን ነው ? ካፍቴሪያ? መንገድ ላይ? …..ግን ለምን? እኛ እርስ በርስ ሥለ ሠው እያወራን እየሳቅን እና እያፌዝን ሌላው በተመሥጦና ልብ ተነክቶ ሥለ ጌታው እንዲያወራ መጋበዝ ማነሳሳት ክፋት ባይኖረው አግባብ ነው? "ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ መልካም ነው" የተባለው ወሬ ለማውራት ቢቀመጡ መልካም ነው:የተባለው ወሬ ለማውራት አይደለም፤ ሌላው ፍጹም አማኝ እንዲሆን እና እኛ ግን "የእምነት መልክ" ያለን ነገር ግን የማናምን በማሳመን ሥራ የተጠመድን መሆን የለብንም ማመናችን በወሬ በአውቅልሃለሁ ሳይሆን በሥራ ቢገለጥ መልካም ነው፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ ባለአመኑት መካከል እየተመላለ በሚያስተምርበት ሰዓት ያላመኑትን ሰዎች ልብስ እያለበሱ ለጣኦት የተሰዋውን እየተመገቡ እነርሱን እየመሰለ ሲኖር ምንም እንኳን የነርሱን ልብስ ቢለብስ ምግባቸውን ቢበላ ባልንጆሮቹም ወደ ጥንት ምግባሩ ተመለሰ ብለው ቢለምኑት እርሱ ግን በወንጌል የልጅነት ልብስ የክብር ልብን ኢየሱስ ክርስቶስን አለበሳቸው ለጣኦት የተሰዋውን እየበላ ሥጋውን እያረከሰ ነፍስንም ስጋንም የሚቀድሰውን የእግዚአብሔርን ቃል መግቦ የእግዚአብሔር አደረጋቸው፡፡ በጨለማ ውስጥ እየተመላለሰ አበራላቸው የእነዚህ ወንድሞቼ አካሄድ ወዴት ይሆን እንደሻማ እየቀለጡ ለሰው ብርሃን መሆን ወይንስ የሻማን ብርሃን እየጋረዱ ማጨለም? የዓለም ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ” እንዳለው በህይወታቸው ያብራላቸው የሚያወሩት ብቻ ሳይሆን የሚኖሩት ይሁንላቸው፡፡ አውቅልሃሁ ከማለት ለራሳቸው የሚያውቁ ያድረጋቸው ያብራላቸው የሚያወሩት ብቻ ሳይሆን የሚኖሩት ይሁንላቸው፡፡ አውቅልሃለሁ ከማለት ለራሳችን የሚያውቁ ያድርጋቸው ተናጋሪ እንደበት ብቻ ሳይሆን አድማጭ ጆሮንም ይስጥልኝ ሥራ ፈተው ከተቀመጡበት መጥቶ ከሚፈርድባቸው ሥራ ፈተው ከተቀመጡበት መጥቶ ጌታ ያግኛቸው የራሱ ያድርጋቸው ለንሰሐ ያብቃቸው፡፡ እኛንም በቤቱ ፀንተን ከማታልፈው መንግሥቱ ያስገባን ፡፡ ባለፈው ይቅር ብሎ በሚመጣው ጠበቆ ቀሪውን ለዘመናችን የወሬ ሳይሆን የስራ የኃጢያት ሳይሆን የንሰሐ ዘመን ያድርግልን፡፡ የአባቶቻችን በረከታቸው ድል የማትነሳ ጥርጥር የሌለባት ተዋህዶ እምነታቸው በኛ ትደርብን የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት የቅዱሳን መላዕክት የቅዱሳን አባቶች ተራድኢነት አይለየን አሜን ይቆየን፡፡

መታሰቢያቱ ለጓደኛዬ ለአዳነ ይሁንልኝ
  God bless Ethiopia!

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...