ሐሙስ 22 ሜይ 2014

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››: click here for pdf ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ በሊቅነታቸው፣ በቆራጥነታቸው፣ ለየት ባለ አስተሳሰባቸውና ለነገሮች በሚሰጡት አስደናቂ ምላሽ የሚታወቁ የትግራይ ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ እስካሁንም እርሳቸውን በተመለከተ ...

እሑድ 18 ሜይ 2014

ክፍል አምስት … … አጋጣሚ



ከመች ወዲህ ነዉ እንዲህ ማምሸት የጀመረችዉ? ከቤት እንዳትወጣ አላልኩሽም? ለመሆኑ ስንት ሰዓት ነዉ የወጣችዉ? ቆይ ስራ በቃኝ! ለተወሰነ ግዜ ማረፍ እፈልጋለሁ ብላ ሥራዋን በገዛ ፈቃዷ የለቀቀችዉ ለመዞር ነዉ እንዴ? እንደከብት እሷን ለመጠበቅ እኔ የግድ እዚህ መዋልና ማምሸት አለብኝ? …. … (ለጥያቄዎቿ መልስ የሚመልስላት ስታጣ ብቻዋን አዉርታ አዉርታ ሲበቃት ስልኳን መደወል ጀመረች፤ ) ደግሞ ስልኳንም ዘግታዋለች፡፡
ነይ እስኪ ወደዚህ ምንድን ነዉ አላማችሁ? ቆይ እስኪ እናንተ ከብቶች ናችሁ እንዴ ያለጥበቃ የማትኖሩት? አልበዛም እንዴ? (ቁጣዋ እየጨመረ መጣ የሚሰማት ሰዉ ግን አልነበረም፤) ምን ይዘጋሻል!
‹‹ እኔን ነዉ? ››
እና ማን አለ? እስካሁን የማወራዉ ለማን መስሎሻል?
‹‹ እስካሁን አዉሪ እንጂ አንዱም አይመለከተኝም፤ … … እኔኮ የቤቱ ጠባቂ እንጂ የሰዉ ጠባቂ አይደለሁም፡፡ ቆይ እስኪ ስራዬ ምንድን ነዉ? ገረድ ነኝ ወይስ እናንተ በተበጣበጣችሁ ቁጥር ሸምጋያችሁ ነኝ? ድርሻዬን አሳዉቁኝ …. ….›› ( በዚህ ቤት ዉስጥ ለመጀመሪያ ጊዜዋ ነዉ እንዲህ አይነት ቃላት ስትናገር፤ )

ማክሰኞ 6 ሜይ 2014

አንድ አድርገን: ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታች...

አንድ አድርገን: ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታች...:  ‹‹ ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታችሁን ለመታደግ በሃይማኖት ጸንታችሁ መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርጉ››   አለቃ አያሌው ታምሩ ሚያዚያ 23 ቀን 1983 የሰማዕቱ ቅዱስ ጊ...

ሰኞ 5 ሜይ 2014

I forget my English ደብተር

ወቅቱ በኛ ዘመን ነዉ ‹የኛን ዘመን› እንግዲህ ቆጥራችሁ ድረሱበት፤ ፍንጭ ለመስጠት ያክል ዛሬ የአማሪኛ ቋንቋን ከብሔሩ ተወላጅ ዉጭ ያሉ ተማሪዎች ‹‹ አማርኛ ›› ብሎ ከመጥራት በስተቀር መናገር እንደተጠመደ ፈንጂ በሚታይበት ሁኔታ እንዳለ ሁሉ እኛም እንግሊዝኛን ከA (ኤ) እስከ Z (ዜድ) ብቻ በሚመስለን ዘመን እንደማለት ነዉ፡፡ የቋንቋ ነገር ከተነሳ አይቀር አንድ ጓደኛዬ እዚሁ መዲናችን አዲስ አበባ ዉስጥ በሚገኝ የግል ባንክ አንድ ዘመዷ ተቀጥራ ለዋስትና ስትሄድ ወደ ህንፃዉ እንደገባች የህንፃዉ ትልቅነት ግራ ስላጋባት መረጃ ትፈልግና አንዷን የባንኩ ሰራተኛ መረጃ ትጠይቃታለች ባነከሯም (የባንኩ ሰራተኛ) በአማርኛ ቋንቋ ለጠየቀቻት ጓደኛዬ አማርኛ እንደማትችል ትመልስላታለች፡፡ ጓደኛዬም የምትሰማዉ ነገር ግራ ይገባትና ‹‹ እንዴት ነዉ የማትችይዉ?›› ብላ ትጠጥቃታለች፡፡
‹‹ በቃ አልችልማ ›› ብላ ግግም ያለ ምላሽ ትሰጣታለች፤
‹‹ እያናገርሽኝ ያለዉኮ በአማርኛ ነዉ ታድያ ይሄንን እንዴት ቻልሽ ወይስ መረጃ መስጠት በአማርኛ መስጠት አትችይም? ›› ትላታለች ፤
የባንክ ባለሙያዋም ‹‹ በቃ ተሳስቼ ነዉ››  ትልና አሁንም በአማርኛ ትመልስላታለች፤
እንግዲህ እንዲህ ቋንቋዉን እየቻሉ መናገር ለሚጠሉት ቋንቋ ‹መግባቢያ› ሳይሆን መዋጊያ የጦር መሳሪያ እየሆነባቸዉ ያለበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነዉ ያለዉ፡፡ (እግረ መንገዳችንንም የግድ እስካልሆነ ድረስ እንዲህ ዘርና ቋንቋ እየመረጡ የሚቀጥሩ መስሪያ ቤቶች ከአካሄዳቸዉ ቢመለሱ የሚሻል ይመስለኛል፤ መልዕክቴ ነዉ፡፡ )

እሑድ 4 ሜይ 2014

ክፍል ሁለት …. … የፀየሙ ገጾች (አዲስ አበባ)

  

ብዙ መልኮችና ብዙ ስሞች ያሉዋት አዲስ አበባ አንዱ መጠሪያዋ አራዳ ነበር፤  አራዳና አዲስ አበባ ተነጣጥለዉ የሚታዩ አልነበሩም፡፡ በአንድ ወቅት ታላቁ ሰዉ አቶ ይድነቃቸዉ ተሰማ ስለ አዲስ አበባ በሬድዮ ፕሮግራም ተጠይቆ ሲናገር እንዲህ ነበር ያለዉ፡- ‹‹ የአዲስ አበባዉ ስታድየም አሁን አለበት ቦታ እንዲሠራ ሐሳብ ሲቀርብ ኳስ ሜዳዉን ከከተማ ዉጭ አደረጋችሁት ተብለን ተወቀሰን ነበር፤ ›› እንግዲህ በወቅቱ አዲስ አበባ ምን ያህል ጠባብና ስንት ህዝብ ይኖርባት እንደነበር መገመት ቀላል ነዉ፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ስታድየምን ያህል ነገር ሲሰራ ከከተማ ወጥቷል ከተባለ የስልጣኔ ጥጓ ምን ያህል ድረስ እንደነበረ መገመትም አይዳግትም፡፡ በቅርቡ እንኳን በ 20 እና በ 30 አመታት ጊዜ ዉስጥ እንኳን የነበራትን ገጽ ብንመለከት አዲስ አበባ እንኳንስ የዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ ልትሆን ይቅርና ለዋና ከተማነት እንኳን የምትመረጥ አልነበረችም፤ ካረጁ ቤቶቿ እና ከፈራረሱ መንገዶቿ አንፃር፡፡ በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በ1879 ዓ.ም. የቆረቆሯት አጼ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ተነስተዉ የትናንትናዋን ባለጎፈሬዋን እና የዛሬዋን ‹ዉብና ድንቅ› እንዲሁም ሰፊ ከተማ በወቅቱ ከነበረዉ ጋር ለማነጻጸር ‹‹ ዕድል ›› ቢገጥማቸዉ ምን ይሰማቸዉ ይሆን? ያስብላል፡፡  
እንደዉ የሚሉትን ነገር ገምቱ ብንባል ዘና ለማለትና በዚያዉም ምሳ ነገር ለመጋበዝ የቀድሞዉን ‹‹ኢምፔሪያል›› የዛሬዉን     ‹‹ ጣይቱ ሆቴል›› ዉሰዱኝ ሳይሉ እንደማይቀሩ እንገምታለን፤ እኛም መቸስ የጠየቁትን አንነፍጋቸዉም እንወስዳቸዋለን፡፡ መቸስ ስለ ጣይቱ ሆቴል ከተነሳ አንድ እዉነት ልንገራችሁ፡- በራዲዮ የቀረበ ነዉ፤ እኔም ከ100ኛ ዓመት በዓል መዘከሪያ መጽሔት ላይ ያገኘሁት ነዉ፡፡
 ላዲላስ ፋራጎ ይባላል፡፡ ጋዜጠኛ ነዉ፡፡ላዲስ ፋራጎ ከለገሃር ባቡር ጣቢያ ተነስቶ ጣይቱ ሆቴል ይሄዳል፡፡ከጅቡቲ፣ከድሬደዋና ከአዋሽ ተሸክሞት ከመጣዉ አዋራና ላብ ለመገላገል ቸኩሎ ነበር፡፡
ከመኝታ ቤቱ ሲገባ ግሩም የሆነ የገላ መታጠቢያ ገንዳ (ባኞ) በማግኘቱ እጅግ ተደስቶ ቦዩን ጠራና ‹‹ ገላዬን ስለምታጠብ ገንዳዉን ሙላልኝ ›› ይለዋል፡፡
ቦዩም (አስተናጋጁ) ስንት ታንካ (ጀሪካን) ዉሃ ላስመጣልዎ ›› ይለዋል፡፡
ፈረንጁ ግራ ይገባዉና ‹‹ ገንዳዉን ሙላልኝ ነዉ የምልህ፡፡ ቧንቧዉን ክፈተዉ፡፡›› ይለዋል፡፡
 አሁንም ቦዩ ይመልስና ‹‹ ገላዎን መታጠብ ከፈለጉ የሚፈልጉትን የዉሃ መጠን ይንገሩኝ፡፡ ያንዱ ታንካ ዉሃ ዋጋ አራት ግርሽ (ጠገራ ብር ወይም ማርያቴሬዛ) ነዉ፡፡ ›› ይላል፡፡  (ገንዳዉን የሚሞላዉ ስድስት ታንካ (108 ሊትር) ዉሃ ነዉ፡፡) ላዲስላስ ፋራጎ ቀጠለና ‹‹ እንዴ? የቧንቧዉን ዉሃ በታኒካ ልክ ታስከፍላላችሁ ማለት ነዉ?›› ሲል ቦዩን ጠየቀዉ፤
ቦዩም ‹‹ አይደለም! ዉሃዉ የሚመጣዉ ከፍል ዉሃ ነዉ፡፡ ኩሊዎ (ተሸካሚ) ይላኩና ፍልዉሃ ሄደዉ ታኒካዉን በፈላ ዉሃ ከሞሉ በኋላ ተሸክመዉ ያመጡታል፡፡ አንድ ኩሊ ዳዉን 6 ታኒካ ዉሃ ይሞላዋል፡፡ ገላዎን አንዴ ታጥበዉ መለቅለቅ ከፈለጉ ደግሞ ተጨማሪ ታኒካ ዉሃ ማስመጣት ያስፈልጋል ›› አለዉ፡፡
‹‹ገንዳችሁ ላይስ የተተከለዉ ቧንቧ?››
‹‹ እንዳልኩዎት ዉሃዉ የሚመጣዉ ክፍል ዉሃ ነዉ፡፡››
ላዲስላስ ፋራጎ ገባዉ፡፡ ገንዳዉ ላይ የተተከለዉ ቧንቧ ለጌጥ ነበር፡፡

ቅዳሜ 3 ሜይ 2014

የፀየሙ ገጾች (Part One)

‹‹ ይህች ቦታ ለኛም ለነፋሱም ትመቸናለች፡፡ እንጦጦ ብርድ ነዉ፡፡ እዚህ ከተማ እናብጅ፡፡ ቦታዋንም አዲስ አበባ ብያታለሁ፡፡›› እቴጌ ጣይቱ
‹‹ እቴ አዲስ አበባ ብለሽ መሰየምሽ ደግ አድርገሻል፡፡ አዲስ አበባ በያት፡፡›› ዳገማዊ አጼ ምኒልክ
ጸሐፊ ትዕዛዝ ገ/ሥላሴ ስለ አዲስ አበባ አመሰራረት ሲናገሩ ‹‹ … ጣይቱ ከድንኳናቸዉ በር ሆነዉ ሲመለከቱ የአካባቢዉን የተፈጥሮ ዉበትና የአየር ንብረት ሁኔታ በማድነቃቸዉ ምኒልክን ፍል ዉሃ አካባቢ ቤት ለመሥራት እንዲፈቀድላቸዉ ጠየቁ፡፡ ምኒልክም ፈቃደኛ ሆነዉ የቤቱ ሥራ በፍጥነት ተጀመረ፡፡›› ይለናል፤
የአዲስ አበባ 100ኛ ዓመት በተከበረበት ወቅት የተዘጋጀዉ የበዓሉ ማክበሪያ መጽሔትም ‹‹ … አዲስ አበባ ከ1883 - 1979 ዓ.ም. ድረስ በርዕሰ ከተማነት የተጫወተችዉ ሚና እጅግ በጣም ብዙና መሠረታዊም ነዉ፡፡›› በማለት ስለአዲስ አበባ ርዕሰ መዲናነት ያስነብበናል፤ ዛሬም አዲስ አበባ የአፍሪካ አገራት መዲና ሆና እንዳለች እኛ የዛሬዎቹ ትዉልድ የዓይን ምስክሮች ነን፡፡
በአንድ ወቅት የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ክቡር መለስ ዜናዊ በቴሌቪዥን መስኮት ስለ አዲስ አበባ ሲናገሩ ‹‹ … አዲስ አበባ አሁን እንደምታዩዋት ለነዋሪ ምቹ አይደለችም ስለዚህ አሁን ካላት ሶስት መልክ ቢያንስ ወደ ሁለት ልናጠጋጋት ግድ ይላል፤ ስለዚህ እንደገና እንሰራታለን …›› ብለዉ እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነዉ፡፡አጼ ምኒልክም አዲስ አበባን ሲቆረቁሩዋት ከጫካነት ነበር መነሻዋ አሁንም ከ100 ዓመት በኃላ ከጫካ የማትሻል ጎስቋላ ከተማ ናት ነገር ግን የአፍሪካ መዲና ነች፡፡ ለዚህ ነዉ አሁንም አዲስ አበባ እንደገና መሰራት ያስፈለጋት፤ እየተሰራችም ትገኛለች፡፡
አዲስ አበባ የማይካድ ሀቅ ነዉ አሮጌ መንደር ነች!

ዓርብ 2 ሜይ 2014

ክፍል አራት ….. ….. አጋጣሚ

የክፍል ሶስት መጠናቀቅ ብዙም ቀጣዩን ክፍል እንድንጓጓለት ባያደርገንም አንድ ነገር ይዞ እንደሚመጣ ግን ተስፋ እናደርጋለን፤ ከፊሎች ደግሞ በጉጉት ጠብቀዉታል ይህ አጋጣሚ መጨረሻዉ ምን ይሆን? እያሉ ለሁላችሁም ክፍል አራትን እነሆ እላለሁ፡፡ መልካም ንባብ ! የማነበብ ባህላችንን እናዳብር፡፡


‹‹ በልቼ ዕቃ ሳላጥብ ማዋልና ማሳደር አልወድም ንጽህና የሌላትንም ሴት እንደዛዉ አልወድም ፣ ማንንም ቢሆን …. አላደረገችዉም እንጂ እናቴም ብትሆን
ይቅርታ አጥቤ እስክመጣ አልበም ነገር ልስጥሽ እንድትደበሪበት?››
ቆይ ሴት እያለማ ወንድ ልጅ ምንም ቢሆን ዕቃ አያጥብም ባይሆን የእስካሁኑ እንግድነት ይብቃኝና እኔ ልጠብ (የሴትና የቄስ እንግዳ የለዉም ሲባል ስለምሰማ) አልኩት የዉሸቴን ዉስጤ ግን የሚፈልገዉ  በአልበሙ ገጾች ላይ ከተሰደሩት መካከል አንድ ጉብል አንገቱ ላይ ተጠምጥማ፣ እሱ ደግሞ እንደ ዘንዶ ወገቧን አለቅ ብሎ ‹‹ችቦ አይሞላም ወገቧ›› እያለ ሲያወድሳት ያለበትን ፎቶግራፍ አይቼ ልቤ እንዲያርፍ ፈለኩ ምንም እንኳን እሱን ፎቶ ለማየት የዉስጥ ጥንካሬ ባይኖረኝም፤
‹‹ በፍፁም አይደረግም እስካሁን ያደከምኩሽ አንሶ በዛ ላይ …. የማይታሰብ ነዉ፤ ባይሆን ….››
ምን አደከምከኝ መብላት ያደክማል እንዴ? ያወራነዉ ሁለታችን ምን የተለየ ነገር አደረኩና ነዉ ያደከምከኝ? …. ‹‹ ባይሆን›› ያልከዉ ምኑ ነዉ?
‹‹ ባይሆን ሌላ ጊዜ ማለቴ ነዉ፤ ››
ልላ ጊዜ መቼ? ልቤ ከቅድም ይልቅ አሁን የባሰ መምታት ጀመረ፤ ደስስስ    …. …ስ አለኝ በቃ ዳግም በዚህ ቤት እንደምስተናገድ ተስፋ ሰነኩ፡፡
‹‹ የእስካሁኑ ይሁን ብለናል አሁን ለምን ፍራሹ ላይ አትቀመጭም … … እኔ ሳህኖቹንና ድስቱን ልጠብ የተዝረከረከ ቤቴን ላጽዳ ድንገት እንግዳ እንኳን ቢመጣ፤ ››
እንዴ የሚመጣ ሰዉ አለ እንዴ? … በማለት ፍራሹ ላይ ልቀመጥ ጫማዬን ላወልቅ የነበረችዉ ሴትዮ ‹‹ ባለህበት ቁም ›› የሚል ወታደራዊ ትዕዛዝ እንደደረሰዉ ሰዉ በንቃት ባለበት ቆምኩ፤
‹‹ ኧረ ስቀልድሽ ነዉ እንኳን ሌላ ሰዉ ቤቴ እኔንም በስራ ቀን ቤቴ እንዲህ በብርሃን ያገኘችኝም ዛሬ ነዉ ››
አብረን ተገኘና፤ … ታድዬ አልኩ ሳላዉቀዉ አልሰማኝም ነበርና መልስ አልሰጠኝም
‹‹ ጫማሽን አዉልቂና ዘና ብለሽ ተቀመጭ የወንደላጤ ፍራሽ ስለሆነ ግዴለም፤››

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...