ሐሙስ 19 ኤፕሪል 2012

ውረድ


ተው ተው ሲሉህ
 ሲያፈራሩህ
አቅማቸውን አተው
ማንነትህን ዘንግተው
አቅራሩ ሸለሉ
ፎከሩ
ፍጥረት በሙሉ
አንድም ሳይቀሩ
ለአመድ ባንድነት
ለትርፍ ሳይሆን ለጉድለት/ለክስረት/
ተው ተው እያለሁ
እያስፈራሩህ
ውረድ ወይ ፍረድ
ብለው ተሳለቁብህ
ትወርዳለህ ወይስ ትፈርዳለህ?
ቅል ልመናውን ለማያውቅ ፍርዱ
አዕምሮ መስጠት ነው
በትዕግሥት ማለፍ ነው
የፈጣሪ/ የአባት ልምዱ
እላለሁ
አትውረድ
አትፍረድ
ይቅር በለኝ እንጂ
በምህረትህ እንድንዋጅ
ተው ተው ተው አለህ
በመፍጠርህ ሊያስቆጩህ
22/01/03
ደረሰ ረታ
visit us again!

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም

  የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም   ( በዲ / ን ብርሃኑ አድማስ ) አፍጣኒተ ረድኤት ማርያም በጊዜ   ምንዳቤ ወአጸባ ለዐይን እምቀራንባ፤ አንቲ ውእቱ ረዳኢተ ያዕቆብ በቤተ ላባ፤ በኩ...