ዓርብ 15 ሜይ 2020

ለምን ትኖራለህ? ወዴት ነህ? ምን ይታይሃል?


ለምን ትኖራለህ
ወዴት ነህ?
ምን ይታይሃል?
          በሳይንሱ ክፍለ ዓለም ስንጓዝ የሰው ልጅ ለመኖር ኑሮን ወይም ሕይወትን ለማሸነፍ በቂም ባይሆን አስፈላጊ የሚሆኑት ምግብ መጠለያ ልብስ ወሳኞች ናቸው ይህንን ለማሟላት ‹‹ጥራህ ግራህ›› ብላ ተብሏልና ይወጣል ይወርዳል ላቡን ያነጠፈጥፋል የሰው የበታችና የበላይ ይሆናል ለመኖር ለብቻውም በሕብረትም ይሁን ብቻ ይለፋል፡፡ ከሳይንሱ ዓለም መለስ ብለን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስንመለከትና ወደ ማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 4÷4 አካባቢ ስናነብ ‹‹ሰው ከእግዚአብሄር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም …›› የሚል እናገኛለን በዚህም መሠረት ቅድም ከተጠቀሰው በተጨማሪ የእግዚአብሔር ቃል /ቃለ ወንጌል/ ያስፈልገናል/ ለመኖር ማለት ነው፤ ግን ለምን እንኖራለን?

ሐሙስ 14 ሜይ 2020

ዘመድኩን በቀለ: ከራየን ወንዝ ማዶ


ዛሬ ለየት ባለ መልኩ የምንመለከተዉ በልዩ አፃፃፉ እና በብዙ ተከታዮቹ የሚታወቀዉ ስለ ዘመድኩት በቀለ (ዲያቆን/መምህር) ሲሆን እንደሚታወቀዉ በተደጋጋሚ ፌስቡኩን እንደሚዘጋ የሚታወቅ ሲሆን ወደፊትም እንደሚዘጋበትና አገልግሎቱን እንደሚያቋርጥበት ይታወቃል ስለዚህ ሌላ መፍትሔ ማምጣት ግድ ሆኗል፡፡
ራሱ ዘመድኩን እንዲህ ያቀርበዋልና ስሙት፤ ተከተሉት፡፡
         ወደፊት ልንሠራቸው ያቀድናቸውን ዕቅዶች በሙሉ አስፍሬያለሁና ጦማሯን አንብቧት። ለሌሎችም #SHARE በማድረግ አጋሯት።
#ETHIOPIA | ~ እንዴት ናችሁልኝሳ ? ሀገሩ፣ መንደሩ፣ ሰፈሩ፣ ቀዬው ሰላም ነው? እኔማ አምላክ ክብር ይግባው ደህና ነኝ።
ይኸው ፌስቡክ ድራሽ አባቴን ቢያጠፋኝም እኔ ዘመዴ፣ የድንግል አሽከር የማይሰበረውን የኢትዮጵያዊነት መንፈስ እንደያዝነ፣ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ውበት አጊጠን፣ እንደ መስከረም ወር ጠሐይ ፈክተን፣ በገነት መካከል እንደ ቆመ የወይራ ዛፍ ለምልመን፣ እንደ ኃያሉ አንበሳ እያገሳን፣ እንደ ነብር፣ እንደ አቦ ሸማኔ እየፈጠንነ፣ እንደ ንስር ታድሰን እነሆ በአዲስ ጉልበት፣ በአዲስ ወኔ፣ አለን ነበረን እንል ከነበረው አቅም ላይ እጥፍ ጨምረን፣ እንደ አልማዝ እንደ ዕንቁ እያንጸባረቅን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የፌስቡክን ኳራኒትን ፈጽመን ይኸው ዳግም ተከስተናል። 
እንደተለመደው እንደ አማኝነታችን ስለ ቅድስት የኢትየጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን፣ የኢትዮጵያ ዜጋ በመሆናችን ደግሞ ስለ ውቢቷ ሃገራችን መወያየታችንንና መመካከራችንን፣ መሟገት፣ መፋጨታችንንንም አጠንክረን እንቀጥላለን። መፋታት፣ ማፈግፈግ፣ መሸሽ፣ ማምለጥና፣ ማስቀየስም የለም። ሰምና ወርቅ ፈልግ የሚል ጦማር እኔ ጋር አይሠራም። እንደ ሐረር፣ እንደ ሲዳሞ ግሩም ጣዕም ያለው ቡና አስሬ ተለክቶ እንደተለቀመ፣ ታጥቦ ተቀሽሮ፣ ተቆልቶ፣ ተወቅጦ ተፈልቶ እንደወረደ ቡና ጦማሬን ትጠጡት፣ ፉትም ትሉት ዘንድ ከሃገረ ጀርመን፣ ከራየን ወንዝ ማዶ ለእናንተ መቅረቡን ይቀጥላል።

ማክሰኞ 7 ኤፕሪል 2020

ስኬታማ ተቋም ለመፍጠር Part Three


1. ሰው መምረጥ


*በብቃቱ፣ በክህሎቱ፣ በተሠጥኦው፣ በትምህርት ዝግጅቱ፣ ወዘተ ከአላማችን ጋር የሚቀራረብ ግባችን ለማሳካት የሚያስችል ሰው መምረጥ አስፈላጊ ነው።
ተቋማት የሥራ እድልን ከመፍጠር ጎን ለጎን ተቋምን ሊያሳድጉ ስኬትን ሊያስመዘግቡ የሚችሉ እና የአገርን ሥም በአለም መድረክ ጭምር ሊያስጠሩ የሚችሉ ሠራተኞችን ከጅምሩ ከላይ በተዘረዘሩት መሥፈርቶች መመልመል ይኖርባቸዋል።

ይህ ሠው ታድያ ግላዊ ጉዳዩን ወደ ጎን ያደረገ የአገር ፍቅር ለወገን ክብር ያለውና ሥራውን እሴት ጨምሮ የሚሰራ ተደርጎ መሠራት አለበት።

የማይረካ፣ የመማር፣ የመሥራት፣ ሁሌም ጀማሪ የሆነ፣ ሁሌም ለአዲስ ነገር ጉጉ የሆነ፣ ዘወትር ለውጥን አሻግሮ የሚያይ፣ ሁሌም ለሥራ የሚሮጥ፣ ጥማት ያለበት ሰው መምረጥ ይኖርብናል።

ሰዉ በመምረጥ ሂደት ዉስጥ መዘንጋት የሌለብን ነገር ምናልባት ከቦታዉ ጋር የሚሄድ ካልሆነ በቀር አለበለዚያም የትምህርት ዝግጅቱ ከመለያየቱ በቀር ‹‹የማይረባ›› የሚባል ሰዉ እንደሌለ ልብ ልንል ይገባል፡፡

ሐሙስ 12 ማርች 2020

ስኬታማ ተቋም ለመፍጠር Part Two


በክፍል አንድ እንዴት ስኬታማ ተቋም መፍጠር እንደሚቻል በጥቂቱ መዳሰስ ጀምረን በይደር ማቆየታችን ይታወቃል ክፍል ሁለትን እነሆ፡-



ሰዉን እንዴት መፍጠር ይቻላል?
ሰዉ በእግዚአብሔር በአርአያዉ እና በምሳሌዉ የተፈጠረ ሆኖ እንዴት ድጋሜ መፍጠር ይቻላል? የሚሉ ጥያቄዎች ሊነሱ ይችላሉ፡፡ አዎ! ጥያቄዉ ጤናማ ነዉ፡፡
ሰዉ በፆታ ወንድ እና ሴት ተብሎ በሁለት እንደተከፈለ ሁሉ ሰዉ ሆኖ በእኩልነት አንድ ሆኖ ሊያስቀጥለዉ የሚችለዉን ማንነት መፍጠር ይቻላል፡፡ እንዴት?
ሰዉን መፍጠር የሚቻለዉ በሶስት ነገር ነዉ፤

እሑድ 8 ማርች 2020

ሴቶች ተቋምን ለመፍጠር ያላቸዉ ብቃት March 8

ሴቶች ይችላሉ።

ከዚህ ቀደም ስለ ተቋም ስኬት እየተነጋገርን እንደነበረ ይታወሳል ለዛሬ ከዚያው ቀጣይ ክፍል የተቀነጨበ ስለሴት ልጅ ችሎታ የሚያረጋግጥልን ጽሑፉ መታሰቢያነቱ በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ላሉ ሴቶች እና ህልማቸውን እንዳያሳኩ በማይረቡ ጭንጋፍ ወንዶች የተሳናከለባቸው የታገቱ እህት ተማሪዎች ይሁንልኝ።

$$$$$$$$$$$$$$$$$

2. ሰው መሥራት

የአንድ ሰው ዋጋ እጅግ ውድ እና በምንም የመገበያያ ገንዘብ ሊተመን የማይችል ነው፤ በአንድ ተቋም ውስጥ ከሰው የሚበልጥ ነገር የለም።
ስለዚህ የሰራተኛን አመለካከት፣ የሰራተኛን ችሎታ፣ የሰራተኛውን አቅም ማሳደግ ከሁሉ ነገር መቅደም ይገባዋል።
ለውጤታማነቱ ተከታታይነት ያለው ክትትል በጥንቃቄ ሊተገበር ይገባል።
እርስ በርስ ፍሬያማ የሆነ ውድድር እንዲኖር አዎንታዊ የእርስ በርስ ተቋማዊ ውድድር እንዲኖር ማድረግ አንዱ ሰው የምንሰራበት መሣሪያ ነው።
ሰው በዚህ መልኩ በጥሩ ሁኔታ ከተገነባ ጠንካራ የሰው ሃይል ስኬታማ ተቋምንም ሆነ አገርን መገንባት ይቻላል።
አገርንም ሆነ ተቋምን በጠንካራ መሠረት ላይ ለመመስረት የሴቶች ተሳትፎ ትልቅ ድርሻ አለው፤ ሴቶች ትውልድን በመቅረጽ ላይ ትልቁን ሚና ስለሚጫወቱ።
አገራትም ሆኑ ተቋማት የሴቶችን ቁጥር በመጨመር ለዘላቂ ስኬት መትጋት ይኖርባቸዋል።
በምሳሌ ላስረዳ:- ሴት ከሁሉም የሰው ፍጥረት ጋር ቀዳሚ እና ዘላቂ ቁርኝነት ስላላት ሚናዋ ከፍ ያለ ነው። ምክንያቱም ሴት ልጅ የወንድ ልጅ የተፈጥሮ አጋር ከመሆኗ ባሻገር እናት ነች፣ (ልጇን በስነምግባር አንጻ ለስኬት ብቁ አድርጋ መቅረጽ ትችልበታለች) ሞግዚት ናት፣ (ጤናማ እና በአካል የዳበረ ለትምህርት እና ለሥራ ዝግጁ የሆነ ዜጋ መፍጠር ትችላለች)፣ የሥራ ሃላፊ ነች፣( በቅርበት በእናትነት እና በእህትነት ጸጋ የሥራ ባልደረቦቿን የተጣመመውን አቃንታ የተበላሸውን አስተካክላ ለመጓዝ የሚያክላት እና ከርሷ የተሻለ ልምድ ያለው የለም)፣ ሚስት ናት፣( ባለቤቷን ለተሳካ ውሎ በደስታ እና በተነቃቃ መንፈስ ከቤት መሸኘት የምትችል በውሎው ደስተኛና ስኬታማ እንዲሆን የምታስችል መግነጢሳዊ ጸጋ የተላበሰች ነች) እህት ናት፣( ትንሽ ሆና ትልቅ በእድሜ አንሳ አስተሳሰቧ ትልቅና ሐላፊነትን መሸከም የሚችል ነው።)
ይህ ሁሉ ሴትን ልጅ የዚህ አለም ማጣፈጫ ጨው ናት ብንል ማጋነን አይሆንብንም ሰው መሥራት ትችላለችና።

ሰኞ 2 ማርች 2020

ስኬታማ ተቋም ለመፍጠር Part one


ስኬታማ ተቋም

ተቋም ፡- ማለት የብዙ ግብአት ዉህደት ሲሆን አንድን ተቋም ስኬታማ ለማድረግ አለበለዚያም በመቋቋም ላይ ያለን ተቋም ከግንባታዉ ጀምሮ ስኬታማ ለማድረግ ከታሰበ እያንዳንዱ ግብአቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በእኩል በልዩ አትኩሮት መገንባት ግድ ይላል፡፡


ለዛሬዉ አንድን ተቋም ስኬታማ አድርጎ ከጅምሩ ለመፍጠር ጠቃሚ ከሆኑት ዉስጥ ጥቂቱን እንመለከታለን፡፡
1)    የሥራ አከባቢን ምቹ ማድረግ፡- በተለያዩ ቁሳቁስ ማሟላት/ ማደራጀት፤
2)    ሰዉ መፍጠር፡- ሰዋዊ ባህሪ ያለዉና ሰዉ ሰዉ የሚሸት ማንነት የተላበሰ ሰራተኛ በእዉቀት፣ በክህሎት እና በቀና አመለካከት የዳበረ መገንባት፤
3)    የሚተገበር ራእይ ማዘጋጀት፡- ራእይ የሌለዉ ተቋም በዉሃ ላይ እንደሚንሳፈፍ ኩበት አለበለዚያም ወንዝ ዳር እንደበቀለ ሸንበቆ ነፋስ ወደ ነፈሰበት የሚሄድ መሆን ነዉ፤
4)    የሚያሰራ መዋቅር መዘርጋት/መፍጠር፡- ወጥነት ያለዉ፣ መነሻና መድረሻ ያለዉ መዋቅር ወሳኝ ነዉ፤
5)    መፈተሸ፡- ከላይ የተጠቀስናቸዉ ነገሮች ወደምንፈልገዉ ግብ(ስኬታማነት) ያደርሱናል አያደርሱንም? እስከ ዛሬ በመጣነዉ ለምንፈልገዉ ግብ እየቀረብን ነዉ? ወይንስ ገና በብዙ ርቀት ላይ ነን?
6)    እርምት መዉሰድ፡- ጉዞአችን ወደ ግባችን የማያደርሰን ከሆነ ፈትሾ ማስተካከያ መስራት ግድ ነዉ፤ ሁሌም በአንድ መንገድ / አካሄድ መጓዝ አግባብ ስላልሆነ፡፡



ስኬት ምንድን ነዉ?
 


ስኬት ማለት የአንድ ዓላማ አፈፃፀም ማለት ነዉ፡፡አንድ አላማ አፈፃፀም በስኬትም በዉድቀትም ሊጠናቀቅ ይችላል፤ ለዛሬ የምንዳስሰዉ ስለ ስኬት ስለሆነ እንዴት ስኬታማ መሆን እንደሚቻል እና ስለ ስኬት እንዳስሳለን፡፡
ፀሐፍት የስኬትን ምሥጢራት እንዲህ አስቀምጠዉልናል፡-
                              I.        ተነሳሽነቱን መዉሰድ/ስኬታማ ለመሆን ሃላፊነቱን ለራስ መዉሰድ
                             II.        የመጨረሻዉን/መድረሻችንን በአእምሮአችን ይዘን /አስቀምጠን መጀመር
                           III.        ቀዳሚ ነገሮችን ማስቀደም (ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት)
                           IV.        ሁለቱም ወገን አሸናፊ ስለሚሆንበት ማሰብ
                            V.        ቅድሚያ ሌሎች እርስዎን እንዲረዳዎት ሳይሆን እነርሱን ለመረዳት ጊዜ ይስጡ
                           VI.        ቅንጅትን /አብሮነትን መፍጠር/ከአንድ ሁለት ይሻላልና/
                          VII.        መጋዙን መሳል/ ዘወትር ለመቁረጥ ስለት ያለዉ ለመሆን መዘጋጀት

እንግዲህ እነዚህ ምሥጢራት በአግባቡ ከተገበርን ስኬት የምርጫ ጉዳይ ነዉ፡፡
ስኬት አጥብቆ የመፈለግ እንጂ የምኞት  ዉጤት አይደለምና አጥብቀዉ ይፈልጉ፤ ጠንክረዉ ይስሩ፡፡
ስኬት የህልምም ዉጤት ስለሆነ ህልምዎ እንዳይደናቀፍ ህልምዎን አጋርዎ ካልሆነ ሰዉ ዘንድ ያርቁት፡፡ ( ህልምና ፅንስ መሬት እስኪይዝ ድረስ ሊጨናገፍ ይችላልና፡፡ እንደዉም እናቶች ሲያረግዙ ፅንሱ ሶስት ወር እስኪሞላዉ ለማንም አይናገሩም)
̎ ስኬት የቀና አመለካከት ፅንስ የጠንካራ ተግባር ልጅ ነዉ፡፡ ̎   

                                                     1.    ሥራ አከባቢን ምቹ ማድረግ

የሥራ አከባቢ ሥንል ሥራን ለማከናወን ብቻ መሆን የለበትም ምክንያቱም በየዕለት ተዕለት ህይወታችን ዉስጥ ከ37% በላይ ጊዜያችንን የምንኖረዉ የመኖሪያ ሥፍራችን መስሪያ ቤታችን አከባቢ ነዉና፡፡ ስለዚህ የመስርያ ከባቢያችን ለመኖር ምቹ መሆን ይኖርበታል፡፡

ምቹ፡- ፅዱ፣ አረንጓዴ፣ ማራኪ፣ ሰላማዊ፣ ከክፋት፣ ከተንኮል፣ ከቂም፣ ከጥላቻ፣ ከአላስፈላጊ አለመግባባት፣ ወዘተ በአንፃራዊነት የፀዳ መሆን ይጠበቅበታል፡፡
1.1.   ለሠራተኛ ምቹ፡- ለመስራት የሚጋብዝ
መሰረተ ልማት የተሟላለት፡- ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ ኮምፒዉተር፣ ኔትወርክ፣ የጽህፈት መሳሪያ ቁሳቁስ፣ ወዘተ
 የመስርያ ቁሳቁስ፡- በስምና በቁጥር ኮምፒዉተር፣ ወንበር፣ ጠረጴዛ፣ … አንድ፣ ሁለት፣ ብለን የምንጠራቸዉ ሳይሆን በትክክል የሚሰሩ፣ የሚያገለግሉ፣ ተገልጋይን የማያጉላሉ፣ አገልጋይን ላሰበዉ ስኬት መንገድ ጠራጊ የሚሆን እንጂ እንቅፋት የሚሆኑ መሆን የለባቸዉም፡፡
እንደዚህ ዓይነት ቁሳቁስ ከመኖራቸዉ ይልቅ አለመኖራቸዉ ይጠቅማልና፤ ምክንያቱም ባለሙያዉ አለመኖራቸዉን አዉቆ ይሟላልኛል ብሎ በሥራ ተነሳሽነት እና በትልቅ ተስፋ ይጠብቃልና፡፡ አንድም በተቋማት ዉስጥ ትልቅ ትኩረት የሚያገኘዉ አንድን ያረጀ ነገር ከመቀየር የሌለን ነገር ማሟላት ስለሚቀላቸዉ፡፡ የለዉም ከሚለዉ ይልቅ ይቀየር ለሚለዉ ጆሮ ስለማይሰጡ፡፡
1.2.   ለሥራዉ ደህንነት፡- ምሥጢሩ ተጠብቆ ተኣማኒነት ተረጋግጦ መስራት አለበት፤
ደህንነቱ የተጠበቀ፡- ፋይል ማስቀመጫ፣ ለአደጋ ተጋላጭ ያልሆነ አከባቢ፣ ለዝርፍያ ተጋላጭ እና ሰነዶች ለመሰወር፣ ለመሰረዝ፣ ለመደለዝ፣ ተጋላጭ የማይሆን ሥፍራ ወዘተ

2.    ሰዉ መፍጠር

ሰዉ ማለት ሰባቱ ባሕርያት የተሟሉለት ቆሞ የሚሄድ ፣ ሮጦ የሚያመልጥ፣ አባሮ የሚይዝ፣ ወጥቶ የሚገባ፣ ሰርቶ የሚበላ፣ ወዘተ የሚለዉ እንዳለ ሆኖ ከዚህ ባሻገር ጭንቅላቱን ፣ አስተሳሰቡን፣ እዉቀቱን፣ ጉልበቱን፣ ሃብቱን፣ ወዘተ ተጠቅሞ ዓለምን መለወጥ የሚችል ፍጡር ነዉ፡፡



ይቀጥላል ...
for more information join my telegram channel
https://t.me/deressereta
 





ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...