የደህንነት ቀበቶ
በምድር
ላይ ህጎች በአራቱም አቅጣጫ ይወጣሉ፤ ህግ አዉጭ፣ ህግ ተንታኝ፣ ህግ አስፈጻሚ፣ ህግ ፈፃሚ፣ ዳኛ፣ አቃቢ ህግ፣ ጠበቃ፣ከሳሽ፣ተከሳሽ፣
ምስክር፣ዋስ፣ … ወዘተ ይኖሩታል፡፡ ህጎች ከህገ ልቡና ዛሬ በየመንደሩ እና በየቤቱ በየፌስቡኩ እስከ ሚወጡት እንሰማለን እናያለን
እንተዳደርበታለን እናስተዳድርበታለን ሌሎችን እንዳኝበታለን እራሳችንም እንዳኝበታለን፡፡ከሚሻር ህግ እስከማይሻር ለዘለዓለም የሚፀና
ከኦሪት ህግ (ብሉይ ኪዳን) እስከ አዲስ ኪዳን (የወንጌል ህግ ) ድረስ ይዘልቃል፤ ከዚሁ ጋርም የህግን መሰረት ያለቀቁ ዘመናትን
ያስቆጠሩ በህብረተሰብ ዘንድ የተከበሩ ብዙ ስርዓቶችም አሉን ለምሳሌ ያህል ለመጥቀስ (የገዳ ስርዓትን የመሰለ ብዙ ሚሊዮኖች የሚተዳደሩበት
ዘመን ያስቆጠረ) በቤተሰብ ዘንድ እና በተለያዩ ማህበረሰቦች መካከልም እንዲሁ ለዘመናት ህዝቡን ከሰንሰለት በጠነከረ አስተሳስሮ
ያለ ስርዓት በሁሉም ብሄር ብሔረሰብ ዘንድ አለን ቱባ ባህልን ጨምሮ፡፡
ለዛሬ
ከዚህ ወጣ ብለን አንድ ህግን መዘን አጠር አድርገን እንወያያለን ስለ ደህንነት ቀበቶ ህግ፤ በኢትዮጵያ ህግ ወጥቶለት በመተግበርና
ባለመተግበር በመቀጣትና በማስተማር እንዲሁም ላለመማር በማስተባበል ዉስጥ የዘለቀ ህግ አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ ዓለም አላት፡፡
የደህንነት ቀበቶ/ ሴፍቲ ቤልት/ ጥቅሙ በዋናነት ለባለቤቱ ሲሆን