ዓርብ 26 ማርች 2021

እንተወው

 "እንተወው"


መጋቢ ሐኪስ እሸቱ ሁሌም በጨው እንደተቀመመ ቃላቸው ሁሌም ይጥመኛል።


እንዲህ ይላሉ፦ "እንተወው ... ካልተውንው እና የሆነብንን፣ እየሆነ ያለውን፣ ሊሆን ያለውን ካሰብን አይደለም ከሰው ጋር ያለን ጉዳይ ይቅርና ትዳራችንን እስክንፈታ ድረስ የሚሄድ ጉዳይ ነው ይላሉ።" 


እውነት ነው ካልተውነው በቀር ስለ አገራችን ፖለቲካ እና ፖለቲከኞች፣ ስለ አገራችን እምነቶች እና በእምነቱ ስም ስለሚተውኑ ሰወች፣ የኑሮ ሁኔታ እና ኑሮውን ስለሚዘውሩ ሰወች፣ ስለ ሶሻል ሚዲያው እና በሶሻል ሚዲያው እንጀራቸውን ስለሚጋግሩ ሰወች፣ ወዘተረፈ የምናውቀውን እንናገር ካልን ጓደኝነታችን አይደለም ትዳራችን ይፈርሳል።


 መንደራችን፣ ብሔራችን፣ ቤተእምነታችን፣ ቡድናችን፣ ፓርቲያችን፣ ወዘተ ይፈርሳል። 


ከመጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ በተማርኩት መሠረት ስለምታውቅ፣ መረጃው ስላለህ፣ ከሁነኛ ሰው ስለሰማህ፣ አትንገር ብለው ስለነገሩህ፣ ... ሁሉ ነገር አይነገርም።


አንተ የደረሰብህ ጉዳይ ፀሐይ የሞቀው አገር ያወቀው ምስክር ጥራ ብትባል አገር ምድሩ ግልብጥ ብሎ ስለሚመሰክርልህ በሕግ ፊት ፍትህ ስለምታገኝ ሁሉ ነገር አይወራም።


መረጃ ማስረጃ አቅርበህ፣ ጠበቃ አቁመህ መርታት ስለምትችል ሁሉ ነገር አይወራም።


አንዳንዴ ጊዜ የሚፈታው፣ አንዳንዴ ለምጣዱ ሲባል አይጧን እንደምታልፋት ሁሉ ዝም ብለህ ማለፍ ትተህ የምታልፈው ነገር እንዳለ መተው ግድ የሆነበት ጊዜ እንዳለ ልብ በል።


@deressereta

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም

  የቀኝ ዐይን - ድንግል ማርያም   ( በዲ / ን ብርሃኑ አድማስ ) አፍጣኒተ ረድኤት ማርያም በጊዜ   ምንዳቤ ወአጸባ ለዐይን እምቀራንባ፤ አንቲ ውእቱ ረዳኢተ ያዕቆብ በቤተ ላባ፤ በኩ...