ሰኞ 18 ኦገስት 2014

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነዉ፤"



ደብረ ታቦር ከገሊላ ባህር በምዕራብ ደቡብ በኩል አስር ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ተራራ ሲሆን ከባህር ጠለል በላይ ከፍታዉ 572 ሜትር ነዉ፡፡
ደብረ ታቦር፡-
1.     ባራቅ ሲሳራን ያሸነፈበት ተራራ ነዉ፡፡ መሳፍንት 4፡6-14
2.    ሳኦል እንደ ሳሙኤል ትንቢት ከሶስት ሰዎች ጋር የተነጋገረበት ነዉ፡፡ 1ኛ ሳሙኤል 10፡3
3.    ደብረ ታቦር በዛብሎን ዕጣ ያለ ለጨራራ ልጆች የተሰጠ ቦታ ነዉ፡፡ 1ኛ ዜና መዋዕል 6፡77
4.    ጌታችን ክብረ መለኮቱን የገለጠበት ቦታ ነዉ፡፡ ማቴዎስ 17፡1-8
ጌታ በማንኛዉም ቦታ ክብረ መለኮቱን መግለፁን ትቶ ደብረ ታቦርን ለምን መረጠ?
አንድም ትንቢቱ ይፈፀም ዘንድ
" ሰማያት ያንተ ናቸዉ ምድርም የአንተ ናት አለምንና ሞላዋን አንተ መሰረትክ ሰሜንና ደቡብን አንተ ፈጠርክ ታቦርና አርሞን በስምህ ደስ ይላቸዋል፡፡" መዝሙር 88፡11-12 የተባለዉ ይፈፀም ዘንድ ነዉ፡፡ ከሌሎች ተራሮች ሁሉ ደብረ ታቦርን የመረጠዉ ሌላዉም ተራራ ከመሬት እንዲርቅ የመለኮትም ምሥጢር ከሰዉ የራቀ የጠለቀ መሆኑን ለማጠየቅ ነዉ፡፡
ሌላዉ፡-

እሑድ 22 ጁን 2014

አለመግባባትን ለማሰወገድ



በመኖር ዉስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በምን መልኩ መፍታት ይቻላል?
Image:Resolve Conflict in Marriage Step 8.jpg
የሰዉ ልጅ በህይወት ዘመኑ ረጅምም ይሁን አጭር፣ አስደሳችም ሆነ አሳዛኝ የሆነ ህይወን መኖሩ ግድ ነዉ፡፡በዚህ ወቅት ሁሌ መግባባቶች ብቻ ናቸዉ ብሎ ማሰብ የማይታሰብ ጉዳይ ነዉ፡፡ታዲያ አለመግባባት ካለ ይህንን አለመግባባት እንዴት መፍታት ይቻላል? ዋናዉና መሠረታዊዉ ጥያቄ ነዉ፡፡
ወደ መፍትሄዉ ከመሄዳችን በፊት እስኪ አለመግባባቶች ከምን እና ከማን ዘንድ ይፈጠራሉ የሚሉትን በጥቂቱ እንመልከት፤
ü  ባለትዳሮች (ባል ከሚስት ወይም ሚስት ከባል ጋር)
ü  ወላጆች (ቤተሰብ) ከልጆች ጋር ልጆች ከቤተሰብ/ከወላጅ ጋር፤ (ቤተሰብ በጠቅላላዉ እርስ በርስ ሠላም ዝር የማይልበት ቤት
ü  ፍቅረኞች (ወንዱ ከሴቷ ሴቷ ከወንድ ፍቅረኛዋ ጋር)
ü  ጓደኛሞች (ወንዶች ከወንዶች፣ ሴቶች ከሴቶች፣ ወንዱ ከሴት፣ ሴቷም ከወንድ ጋር ) ትንሽ በሚባሉ ችግሮች የሚፈጠሩ አለመግባባቶች
ü  መንግስትና ህዝብ (ባለመደማመጥና ባለመከባበር እኔ ነኝ የምገዛህ ወይም የማስተዳድርህ፣ አንተ አትገዛኝም ወይም አታስተዳድረኝም አለበለዚያም ወደ ሥልጣን ያመጣሁህ እኔ ነኝ … እንዳመጣሁህ አወርድሃለዉ….)
ü  መንግሥት ከመንግሥታት/ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች (በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች እና ኃይልን ለማሳየት በሚሞከር ትንኮሳ፣ በጉርብትና፣ በድንበር ጉዳይ፣ ቅኝ ለመግዛት በማሰብ እና ላለመገዛት መወሰን፣….)
ü  መንግሥት ከተቋማት ጋር (በሪፖርት፣ በዜና እወጃ፣ ምሥጢር በማዉጣት፣ ጫና በመፍጠር ፣ ጥቅማ ጥቅሞችን በማስቀረት፣ ሌሎች ወገኖችን በማሳመፅ፣ አላስፈላጊና አወዛጋቢ አዋጆችን በማወጅ፣ ….)
ü  ወዘተ
ችግሮች የሚፈጠሩበትን አካባቢ እንዲህ በጥቂቱ ከዘረዘርን በማዕከልነት መፍትሔዎችን እንዲሁ በጥቂቱ ማንሳቱ አወያይ እና ሌሎችንም ሻል ያሉ ምፍትሔዎችን በተጠና መልኩ ያመጣሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ለጊዜዉ ጥናቱን ለባለሙያዎቹ ልተዉና ይሆናሉ የምላቸዉን እነሆ ብያለሁ፡-

እሑድ 8 ጁን 2014

ክፍል ስድስት… … … አጋጣሚ



ረጅም ዕድሜን ባልኖርም ሊደርሱብኝ የሚችሉትን አስተናግጃለሁ፣ ማየት የነበረብኝን አይቻለሁ፣ ደስታንም ሃዘንንም ከእህቴ የበለጠ አዉቃለሁ፣ ( ከእህቴ እንደምበልጥ የማረጋግጥልህ እሷ በህይወቴ ጣልቃ እየገባች አዉቅልሻለሁ ስትለኝ ይህንን ሁሉ እንደማዉቅ አለማወቋ በቂ ማረጋገጫ ነዉ፤ እስኪ እኔን ከእናቴ ፈርማ ተረክባ ቢሆን አሁን ያለሁበት ሁኔታ ለምን እንደሚዳርጋት አስበኸዋል? ) አሁን ከምነግርህ በላይ አዉቃለሁ፤ ነገር ግን እስካሁን የማዉቀዉ መጥፎ ነገሮችን ነዉ ጥሩ የተባሉትንም ቢሆን ከእርሷ የተሻለ አዉቃለሁ፡፡ የሚገርመዉ ስለግል ህይወቴ ዕድል ሳትሰጠኝ ስለ አገር ጉዳይ ቁጭ አድርጋ ታወራኛለች፤ እስኪ አስበኸዋል እኔ አሁን ስለ አገር የሚያገባኝ ሴት ነኝ የኔን ነፃነት ነፍጋኝ ዲሞክራሲ ስለጠማት እና ስለራባት አገር እኔ ምን አግብቶኝ ነዉ ከእሷ ጋር ስለ አገር ጉዳይ ለማዉራት በጠረጴዛ ዙሪያ የምሰደረዉ? ስለፍቅር እየተከለከልኩ ስለ ፖለቲካ የሚፈቀድልኝ እንዴት ነዉ ነገሩ? እኔ የሚገርመኝ ፖለቲካል ሳይንስ ታጥና ህክምና ግራ ግብት ይለኛል፡፡ ለምን አታገቢም ስትላት መጀመሪያ አገር ባለቤት ይኑራት ትልሃለች፤ ለምንድን ነዉ የራስሽ ነገር የማይኖርሽ ስትላት አሁን ጊዜዉ አይደለም ስንት አንገብጋቢ ነገር እያለ ትልሃለች፤ እሷን የሚያንገበግባት የእኔና የአገር ጉዳይ ብቻ ነዉ፡፡
ልብ በለህ ስማኝ እሷ ወንድ የምታዉቀዉ ስለፖለቲካ ጉዳይ ለማዉራትና በህክምና ሊረዳ በስራ ቦታዋ ሲመጣ ብቻ ነዉ፤ ባለፈዉ አንዱ ከቤት ድረስ ቢመጣ ሁላችን ደስ ብሎን ( መቸስ በባህላችን ሴት ልጅ ወንድ ይዛ እቤት ድረስ ስትመጣ የቱንም ያህል ደስ የማይል ጉዳይ መሆኑ ግልፅ ቢሆንም ይህ የሚያሳየዉ የጉጉታችን ልክ መጠነ ሰፊ መሆኑን ያመላክታል ) ግድግዳዉ ላይ ጆሮአችንን ለጥፈን ( አንድያዉን ለስነን ብትለዉ ይቀላል) ብናዳምጥ ብናዳምጥ አንዳች ነገር አጣንባት ከጆሮዬ ይሆን ብዬ አብራኝ የነበረችዉን የቤታችን አባል ሰራተኛይቱን ብጠይቅ እሷም እንደኔዉ ተበሳጭታ ኖሮ እሷቴ አናዳችም ስለሴትና ወንድ ያወራችዉ ነገር እንደሌለ ነገረችኝ፤ ያዉ የፈረደበትን ፖለቲካ እቤት ድረስ ይዛ መጥታ ታቦካዉ ጀመረ እንጂ፡፡ አሁን እስቲ ማን ይሙት ‹‹ የዘመናችን ብቸኛዋ ፖለቲከኛ ሴት ለመባል ነዉ ወይስ … ›› እስኪ እንደዉ ብቻ ተወኝ፤ ነገረ ዓለሙ ሁላ ፖለቲካ ፖለቲካ የሸተተበት ዘመን ላይ ደርሰን ህጻን አዋቂዉ አልጋና ትራሱ ሁሉ ፖለቲካ ሆኖ ፍቅር ጠፋ አንዴ እኔ ብገኝ በምን እናጥፋሽ ብለዉ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡
( እነማን ናቸዉ ለማለት ፈለኩና የሞቀ ወሬያችንን በኔ ጣልቃ ገብነት እንዳልገታዉ ፈራሁና እየተከታተልኳት መሆኔን አንገቴን ላይ ታች በመነቅነቅ ገለጽኩላት፤) 
ከዚህ ቀደም እንዳወራነዉ ከልጅነት ጓደኛዬ ሌላ ተባራሪዎቹን ሳንቆጥር አንድ ሶስት ወንዶችን በደንብ አዉቃለሁ፤ ነገር ግን ይህቺ ክፉ እህቴ ሁሌ ጥላዋን እያጠላችብኝ እንደዛፍ ላይ እንቅልፍ አስሬ እየባነንኩ ነበር የምኖረዉ፡፡ የመጀመሪያዉ በጣምም ሃብታም ባይባል ለኔ ከበቂ በላይ ሊይዘኝ የሚችለዉ አቅም ነበረዉ ከነበረዉ ገንዘብ ይልቅ ፍቅሩ ይግደለኝ፣ እንክብካቤዉስ ብትል፣ በተለይ በተለይ የትም ስንገባ የነበረዉ ክብር እመቤት የሆንኩ ያህል ነበር የሚሰማኝ ወንበር ስቦ አስቀምጦ፣ የመኪና በር ከፍቶ አዉርዶ አስገብቶ፣ … ስንቱን ልበልህ ከልቡ ነበር ግን ‹‹ ባሪያ ላመሉ … ›› እንደሚባል ልክስክስ ነበር፤

ሐሙስ 22 ሜይ 2014

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››: click here for pdf ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ በሊቅነታቸው፣ በቆራጥነታቸው፣ ለየት ባለ አስተሳሰባቸውና ለነገሮች በሚሰጡት አስደናቂ ምላሽ የሚታወቁ የትግራይ ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ እስካሁንም እርሳቸውን በተመለከተ ...

እሑድ 18 ሜይ 2014

ክፍል አምስት … … አጋጣሚ



ከመች ወዲህ ነዉ እንዲህ ማምሸት የጀመረችዉ? ከቤት እንዳትወጣ አላልኩሽም? ለመሆኑ ስንት ሰዓት ነዉ የወጣችዉ? ቆይ ስራ በቃኝ! ለተወሰነ ግዜ ማረፍ እፈልጋለሁ ብላ ሥራዋን በገዛ ፈቃዷ የለቀቀችዉ ለመዞር ነዉ እንዴ? እንደከብት እሷን ለመጠበቅ እኔ የግድ እዚህ መዋልና ማምሸት አለብኝ? …. … (ለጥያቄዎቿ መልስ የሚመልስላት ስታጣ ብቻዋን አዉርታ አዉርታ ሲበቃት ስልኳን መደወል ጀመረች፤ ) ደግሞ ስልኳንም ዘግታዋለች፡፡
ነይ እስኪ ወደዚህ ምንድን ነዉ አላማችሁ? ቆይ እስኪ እናንተ ከብቶች ናችሁ እንዴ ያለጥበቃ የማትኖሩት? አልበዛም እንዴ? (ቁጣዋ እየጨመረ መጣ የሚሰማት ሰዉ ግን አልነበረም፤) ምን ይዘጋሻል!
‹‹ እኔን ነዉ? ››
እና ማን አለ? እስካሁን የማወራዉ ለማን መስሎሻል?
‹‹ እስካሁን አዉሪ እንጂ አንዱም አይመለከተኝም፤ … … እኔኮ የቤቱ ጠባቂ እንጂ የሰዉ ጠባቂ አይደለሁም፡፡ ቆይ እስኪ ስራዬ ምንድን ነዉ? ገረድ ነኝ ወይስ እናንተ በተበጣበጣችሁ ቁጥር ሸምጋያችሁ ነኝ? ድርሻዬን አሳዉቁኝ …. ….›› ( በዚህ ቤት ዉስጥ ለመጀመሪያ ጊዜዋ ነዉ እንዲህ አይነት ቃላት ስትናገር፤ )

ማክሰኞ 6 ሜይ 2014

አንድ አድርገን: ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታች...

አንድ አድርገን: ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታች...:  ‹‹ ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታችሁን ለመታደግ በሃይማኖት ጸንታችሁ መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርጉ››   አለቃ አያሌው ታምሩ ሚያዚያ 23 ቀን 1983 የሰማዕቱ ቅዱስ ጊ...

ሰኞ 5 ሜይ 2014

I forget my English ደብተር

ወቅቱ በኛ ዘመን ነዉ ‹የኛን ዘመን› እንግዲህ ቆጥራችሁ ድረሱበት፤ ፍንጭ ለመስጠት ያክል ዛሬ የአማሪኛ ቋንቋን ከብሔሩ ተወላጅ ዉጭ ያሉ ተማሪዎች ‹‹ አማርኛ ›› ብሎ ከመጥራት በስተቀር መናገር እንደተጠመደ ፈንጂ በሚታይበት ሁኔታ እንዳለ ሁሉ እኛም እንግሊዝኛን ከA (ኤ) እስከ Z (ዜድ) ብቻ በሚመስለን ዘመን እንደማለት ነዉ፡፡ የቋንቋ ነገር ከተነሳ አይቀር አንድ ጓደኛዬ እዚሁ መዲናችን አዲስ አበባ ዉስጥ በሚገኝ የግል ባንክ አንድ ዘመዷ ተቀጥራ ለዋስትና ስትሄድ ወደ ህንፃዉ እንደገባች የህንፃዉ ትልቅነት ግራ ስላጋባት መረጃ ትፈልግና አንዷን የባንኩ ሰራተኛ መረጃ ትጠይቃታለች ባነከሯም (የባንኩ ሰራተኛ) በአማርኛ ቋንቋ ለጠየቀቻት ጓደኛዬ አማርኛ እንደማትችል ትመልስላታለች፡፡ ጓደኛዬም የምትሰማዉ ነገር ግራ ይገባትና ‹‹ እንዴት ነዉ የማትችይዉ?›› ብላ ትጠጥቃታለች፡፡
‹‹ በቃ አልችልማ ›› ብላ ግግም ያለ ምላሽ ትሰጣታለች፤
‹‹ እያናገርሽኝ ያለዉኮ በአማርኛ ነዉ ታድያ ይሄንን እንዴት ቻልሽ ወይስ መረጃ መስጠት በአማርኛ መስጠት አትችይም? ›› ትላታለች ፤
የባንክ ባለሙያዋም ‹‹ በቃ ተሳስቼ ነዉ››  ትልና አሁንም በአማርኛ ትመልስላታለች፤
እንግዲህ እንዲህ ቋንቋዉን እየቻሉ መናገር ለሚጠሉት ቋንቋ ‹መግባቢያ› ሳይሆን መዋጊያ የጦር መሳሪያ እየሆነባቸዉ ያለበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነዉ ያለዉ፡፡ (እግረ መንገዳችንንም የግድ እስካልሆነ ድረስ እንዲህ ዘርና ቋንቋ እየመረጡ የሚቀጥሩ መስሪያ ቤቶች ከአካሄዳቸዉ ቢመለሱ የሚሻል ይመስለኛል፤ መልዕክቴ ነዉ፡፡ )

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...