ማክሰኞ 18 ማርች 2014

ጊዜና ዘመን

ጊዜ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ይታሰባል ይከወናል ትናንት ዛሬን እየሆነ ይቆጠራል፤ ትናንትናና ዛሬ ተደማምሮ ሳምንት ሳምንታትና ቀናት ተደማምረው ወራትና ዓመታትን /ሦስት መቶ ስልሳ አምስት ቀናትን/ ይሰጣሉ፡፡ ከአዳም ጀምሮ ዓመት ይቆጠራል፡፡ የዓመታት ጥርቅም ዘመን ተብሎ ይጠራል ዘመን ረጅም ጊዜ ነው ወይም አንድ አይነት አገዛዝ አምልኮ ሌላም የተደረገበት ጊዜ መጠሪያ ነው፡፡
       ዘመን የተፈጠርንበት /የተወለድንበት/ ትምህርት የጀመርንበት፣ ሥራ የያዝንበት፣ መከራን ያየንበት፣ ከውድቀታችን የተነሳንበት፣ የተማመንበት፣ የተፈወስንበትወቅት ማስታወሻ /መጠሪያ/ ሊሆን ይችላል፡፡
       ወደ ፍሬ ነገሩ ልምጣና ከብዙ ሰዎች አንደበት ስሰማና ከብዕራቸው የዕምባ ጠብቃ ሳነብ ብዙዎች ዘመንና ጊዜን ሲደግፉ በከንቱ ስሙን ሲያጠፉ ሲኮንኑ አዳምጣለሁ አነባለሁ ‹‹አይ ዘመን፣ አይ ጊዜ›› ‹‹ጊዜው ነው፣ ዘመኑ ነው›› ሲሉ ነገር ግን ጊዜና ዘመን ምን አደረገ ምንስ በደለ ጊዜና ዘመን በራሱ ምን ያመጣው ለውጥ ምንስ ያደረሰው ተፅዕኖ አለ? አንዳንድ ፀሐፍት እንደሚሉት ዘመንና አህያ አንድ ነው ይላሉ አህያ እንዳሸከሟትና የጫኑባትን ይዛ እንደምትገኝ ዘመንም

‹‹ቅዳሴ›› ክፍል -2-

አይነጋ የለ ነጋ ጊዜው 1130 ሰዓት ነው የሞላኋት የግድግዳ ሰዓቴ ድምፅ አሰማች እኔም ከእንቅልፌ ነቃሁ ሲረፍድብኝ እንዳላደርኩ ሳይረፍድብኝ ወደ ቅዳሴ ሄድኩ የቀን መዘውሩ ተገባዶ ሌሊቱ ለንጋት ስፍራውን መልቀቁን የተገነዘበ ሕዝበ አዳም ታጥቆ ተነስቷል ፀሐይ የንጋት ብርሃኗን ለመፈንጠቅ ሰማዩን አድርጋዋለች ነጭ ነጠላ የለበሱ ምዕመን መንገዱን ሞልቶታል አብያተ ክርስቲያናት የጥሪ ደውላቸውን (ድምፃቸውን) እያሰሙ ነው ሱቆችም የአሁኗን ንጋት በጥዋፍና ሻማ ዕጣን ሽያጭ ጀምረዋል ነዳያን ቤተክርስቲያን ጌጥ መስለው ከደጇ በረድፍ ተቀምጠዋል አስቀዳሹ እኔም አላረፈድኩም በሚል ስሜት በርጋታ እየተራመድኩ የደጃፉን በር ተሳልሜ ከግቢው ከመግባቴ ‹‹አሐዱ አብ ቅዱስ …›› የሚለውን የካህኑ ድምፅ በዜማ ተሰማኝ ተፈጥሮ ካስዋበው ከቤተክርስቲያኑ አጸድ ሥር ተጠንቅቄ በመቆም እጆቼን ከላይ ሆኖ ወደሚያየኝ አምላክ በማንጋጠጥ ዘረጋሁ ዙሪያው ጭር ያለው ግቢ በምዕመናን እየተጨናነቀ መጣ የቅዳሴውየተሰጥኦዜማ ሥፍራውን የመላዕክት ከተማ ኢዮር፣ ኤረር፣ ራማን አስመስሎታል የዕጣን የሽታ መአዛ ግቢውን አውዶታል ነፍሳችን እጅግ ተደስታለች ቅዳሴውን የሰማይ አዕዋፍ በድምፃቸው አብረው ሲያጅቡት የበለጠውን ውበት ሰጥተውታል የዕጣን ጢስ ወደላይ ማረግ የተመለከተ ልቡናችን አብሮ ከመንበረ ፀባኦት ደርሷል

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

ትቶ እና ችሎ

  ትቶ እና ችሎ ብጹእ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ በደረሰ ረታ ብጹዕነታቸው ለሶስት አሥርት አመታት እኛ በማናውቀው እግዚአብሔር በሚያውቀው በብዙ መከራ በብዙ ፈተና ውስጥ ነው ያሳለፉት። ...