ሰኞ 26 ጃንዋሪ 2015

ሊሰራ የማይወድ አይብላ



ዳንኤል ክብረት "ቁስል ተራ " ብሎ የፃፈዉን ካነበብኩ በኋላ በልቤ ሲላወስ የነበረ ሐሳብ ስለነበር ይህንን አጋጣሚ ተጠቅሜ ልተነፍስ ተነሳሁ፤ የርሱን ሐሳብ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡፡ http://www.danielkibret.com/2015/01/blog-post_20.html#comment-form ወዳጄ ዳንኤል ሥራ አልሆን ሲለን ወደ ልመና ከገባንኮ ቆይተናል፤ አንተ የአካሉን ሥትል ሰዉኮ ለመለመኛ ብሎ ልጅ መዉለድ ከጀመረ ሰነባበተኮ፡፡ በአንድ ወቅት ትራንስፖርት ዉስጥ ቁጭ ብዮ የሆነ ሰዉ ጋቢ ተከናንቦ የጉሉኮስ ዕቃ ታቅፎ አጥሚት አፉ ላይ እንደደረቀ ህፃን እየበረረ ታክሲ ዉስጥ አስጥሉኝ እያለ ገባ ከበስተጀርባዉ ስንመለከት ማንም የሚከተለዉ ሰዉ ስናጣ የባሰ አትኩሮቶቻችንን ሳበዉ …. ይህ ሰዉ ለካንስ ይህቺ ዘዴዉ የመለመኛ መንገዱ ነበረች ……. ወንበር ከመያዙ የልመና ቃላት ማዥጎድጎዱን ተያያዘዉ፤ ( ባጭሩ ታሞ ጥቁር አንበሳ ተኝቶ እንደነበረ፣ ከሁለት ወር በላይ እንደቆየ፣ ከክፍለ ሃገር እንደመጣ፣ በህመሙ ምክንያት ረጅም ጊዜ ስራ ገበታዉ ላይ ስላልተገኘ ከሥራ እንደተቀነሰ፣ በዚህ ምክንያት ቤተሰቡን ማስተዳደር ባለመቻሉ የልጆቹ እናት ጥላዉ ቤተሰቦቿ ጋር እንደሄደች፣ አሁን እንዲህ ሆኖ የተገኘበት ምክንያት ለህክናዉ የሚሆን ገንዘብ በመጨረሱና መድሐኒቱን ከወሰደ በኋላ/ በፊት የሚመገበዉ ምግብ በማጣቱ ከአልጋዉ ተነስቶ ለልመና እንደወጣ ነበር የነገረን፡፡ አስጥሉኝ ማለቱም ከሆስፒታሉ ሲወጣ ያዩት የጥበቃ ሰወችም ሆኑ ሲወጣ ያዩት የጤና ባለሙያዎችን ማለቱ ነበር፡፡) ሁላችንም ያለንን ያህል በተለመደዉ ኢትዮጵያዊ ሩህሩህ ባህሪያችን ሰጠነዉ፡፡ሰዉየዉም ለምስጋና እንኳን ጊዜ ሳያገኝ፣ ሊሄድበት የፈለገዉንም ፒያሳ ሳይደርስ እዉነት ይሁን ዉሸት ለጊዜዉ ባናዉቅም "የምበላዉ ካገኘሁ በቃ ወደ ሆስፒታል ልመለስ" ብሎ ወረደ፡፡
ከቀናት በኋላ ደግሞ ይኸዉ ሰዉ ራሱ በምሰራበት መስሪያ ቤት ጉዳይ ኖሮት ሊስተናገድ በጣም አምሮበት ጥቁር ሙሉ ልብስ በነጭ ሸሚዝ ለብሶ ጥቁር መነፅር ሰክቶ ከተፍ አለ፤ ድኖ በማየቴ ፈጣሪዬን ጤናዉን ስለመለሰለት አመሰገንኩት፡፡ ያንን ዕለት ስላደረግነዉ መልካም ነገር ደስታ እና ኩራት ተሰማኝ … … የአንድ ሰዉ ህይወት ታድገናልና፡፡ሥራ ቦታ መሆኔ ነዉ እንጂ እንኳን እግዚአብሔር ማረህ፣ እንኳን ደስ አለህ፣ … ብለዉ ደስ ይለኝ ነበር፤ ባለማለቴ እጅግ ቆጨኝ፡፡
በዚያኑ ሳምንት ቅዳሜ ዕለት አራት ኪሎ ወደ ፒያሳ ሄጄ ሲኒማ አምፔር ጋር ስወርድ ወርቅ ቤቶቹ ጋር ያደፈ ጋቢ ለብሶ ያቺ የፈረደባትን የጉሉኮስ ዕቃ ታቅፎ እያቃሰተ ወገን አድኑኝ እያለ የመጀመሪያ ቀን ያቀረበዉን ምክንያት እየደረደረ ይለምናል፤ በሱ ቦታ እኔ አፍሬ እያማተብኩ አለፍኩት የዋሁ ህዝብ ጉዳዩን አላወቀ ሳይኖረዉ ካለዉ ላይ የቀረችዉን እያነሳ ሳይሳሳ ይሰጣል፡፡ የሌለዉ ከንፈሩን በሀዘኔታ እየመጠጠ "እግዚአብሔር ይማርህ እያለ ያልፋል" የሰዉ ልጅ ለምንድነዉ ርካሽ የሆነ ባህሪ የሚመቸዉ ብዬ ታዘብኩ፤ ….
ከጊዜ ብዛት ከተማ ዉስጥ ስዘዋወር በተደጋጋሚ ሳገኘዉ ባህሪዉ መጥፎ የምንለዉ አይነት ሰዉ ነበር ( ያጨሳል፣ በጣም ይጠጣል፣ ቁማር ይጫወታል፣ … ) ከረጅም ጊዜ በኋላ ለሆነ ንግስ በዓል ነጭ በነጭ ለብሶ ከጓደኞቹ ጋር አገኘሁት የኔ ቢጤ ሲለምነዉ መርጦ አዉጥቶ 10 ሳንቲም ሲሰጥ አየሁት፤ ፈራ ተባ እያልኩ "መስጠትም ታዉቅበታለህ? " አልኩት፡፡ "ምነዉ መስመር ላይ ተገጣጥመን እናዉቃለን እንዴ ?"አለኝ፤ ….
ባጭሩ ከዚህ ሰዉ ጋር ባደረግነዉ ዉይይት የቅድሙ ታሪክ ሁሉ ዉሸት እንደሆነና ከመስራት መለመን አዋጭ እንደሆነ በድፍረት ነገረኝ፤ ሰዉ ሆይ ስራ መስራትን ጠልተን ልመናን የምንኮራበት እና የምንመርጠዉ እስከ መቼ ነዉ?ልንሰራስ የማንወደዉ ለምንድን ነዉ?
ሊሰራ የማይወድ አይብላ! ያልሰራ አይብላ አላልኩም ስራ አጥቶ ሊሆን ይችላልና፤ በየስራ ገበታዉም ያላችሁ ለታይታ የምትሰሩ፣ የአለቃን ፊት እያያችሁ የምታለምጡ፣ የሰዓት መቆጣጠሪያ ላይ ለመፈረም ብቻ የምትገቡ፣ … እግዚአብሔር ልብ ይስጣችሁ፡፡

ማክሰኞ 13 ጃንዋሪ 2015

Ethiopia Zone9: " ህልም አንደሆነ አይታሰርም " ጦማሪ አቤል ዋበላ

Ethiopia Zone9: " ህልም አንደሆነ አይታሰርም " ጦማሪ አቤል ዋበላ: ‹‹ ስሜ አቤል ዋበላ ነው፡፡ አዲሱ አመት ሲጠባ በአዲስ መንፈስ አዲስ ህልም ለአገሬ ማለም የነበረኝንም ማጠናከር እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያችን የብሄር፣ የሃይማኖት፣ የሀብት፣ የትምህርት፣ የፖለቲካ አመለካከት እና ሌሎች...

እሑድ 4 ጃንዋሪ 2015

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: የትልቁ ዋርካ ትልቁ ቅርንጫፍ

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: የትልቁ ዋርካ ትልቁ ቅርንጫፍ:   click here for pdf ታኅሣሥ 19 ቀን 2007 ዓም በቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታወቁት ሊቃውንት መካከል አንዱን አጥተናል፡፡ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየን፡፡ ስለ ሥርዓተ ...

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: እንደ ሰው ወይስ እንደ እንስሳ

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: እንደ ሰው ወይስ እንደ እንስሳ: click here for pdf   The Indian Folktales በተሰኝ ከዛሬ 100 ዓመት በፊት በ1919 እኤአ በታተመ መጽሐፍ ላይ እንዲህ ይላል፡፡ አንድ የሕንድ ጠቢብ ደቀ መዝሙሮቹን ሥራ እንዲሠሩ አዘ...

ረቡዕ 10 ሴፕቴምበር 2014

መልካም አዲስ ዓመት፡

ራስን ሁልጊዜ በአሸናፊነት ዙፋን ላይ …
ይህ ዓለም የዉድድር ዓለም እንደመሆኑ መጠን ይበልጡኑ የሰዉ ልጅ ትልቁን ዉድድር በተሳታፊነት እና በበላይነት ሚናዉን ይወጣል፡፡ ይሁን እንጂ በዉድድሩ ሁሉም በመንፈሰ ጠንካራነትም ሆነ አልሸነፍ ባይነት መንፈስ መሸነፍን አይወድም፡፡ ሁሌም እርሱ አሸናፊ ቢሆን እና በድል ቢያጠናቅቅ ደስ ይለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ዉድድሩ በአንድ ሰዉ የበላይነት ( አንደኝነት ) መጠናቀቁ ግድ ይላል፡፡   ሆኖም ሁሉም ሰዉ በአንደኝነት ሊጨርስ ይቻለዋል፤ ጨርሻለሁ ብሎ ማመንም ማሳመንም ይችላል፡፡ እንዴት?
ሁሉም ሰዉ የሥራ ድርሻ እንዳለዉ የታመነ ነዉ፤ ሁሉም ወደ ዉድድሩ የሚገባዉና የአሸናፊነት አክሊሉን ሊደፋ የሚችለዉ እየሰራ ባለዉና በሚሰራዉ መስክ ነዉ፡፡ ማንም ሰዉ አንተ እየሰራህ ያለዉን ሥራ አንተ በምትሰራዉ መንገድ አይሠራም፣ አልሠራምም፤ ስለዚህ ይህንን ሥራ በምታጠናቅቅበት ሠዓት አሸናፊዉ አንተ ነህና፡፡ ተወዳዳሪህን ባታሸንፈዉ ሥራህን አሸንፈሃልና፡፡የሰዉ ልጅ በአሸናፊነት ዙፋን ላይ ለመቀመጥ ሁል ጊዜ ሥራዉን ማሸነፍ አለበት፡፡ በተገቢዉ ሁኔታ ተጀምሮ እስኪያልቅ ሥራዉን ካወቀ፣ ከሰራ፣ ካጠናቀቀ፣ እሱ ሰዉ ባለድል ነዉ፡፡

ሁላችንም ከፊታችን በሚመጣዉ አዲስ ዓመት ራሳችንን ሁል ጊዜ በአሸናፊነት ዙፋን ላይ ማስቀመጥ የሚችል ልዩ ሞራል ባለቤት እንድንሆን መልካም ምኞቴን ገልፃለሁ፤ መልካም አዲስ ዓመት፡፡

ሰኞ 18 ኦገስት 2014

"በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነዉ፤"



ደብረ ታቦር ከገሊላ ባህር በምዕራብ ደቡብ በኩል አስር ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ተራራ ሲሆን ከባህር ጠለል በላይ ከፍታዉ 572 ሜትር ነዉ፡፡
ደብረ ታቦር፡-
1.     ባራቅ ሲሳራን ያሸነፈበት ተራራ ነዉ፡፡ መሳፍንት 4፡6-14
2.    ሳኦል እንደ ሳሙኤል ትንቢት ከሶስት ሰዎች ጋር የተነጋገረበት ነዉ፡፡ 1ኛ ሳሙኤል 10፡3
3.    ደብረ ታቦር በዛብሎን ዕጣ ያለ ለጨራራ ልጆች የተሰጠ ቦታ ነዉ፡፡ 1ኛ ዜና መዋዕል 6፡77
4.    ጌታችን ክብረ መለኮቱን የገለጠበት ቦታ ነዉ፡፡ ማቴዎስ 17፡1-8
ጌታ በማንኛዉም ቦታ ክብረ መለኮቱን መግለፁን ትቶ ደብረ ታቦርን ለምን መረጠ?
አንድም ትንቢቱ ይፈፀም ዘንድ
" ሰማያት ያንተ ናቸዉ ምድርም የአንተ ናት አለምንና ሞላዋን አንተ መሰረትክ ሰሜንና ደቡብን አንተ ፈጠርክ ታቦርና አርሞን በስምህ ደስ ይላቸዋል፡፡" መዝሙር 88፡11-12 የተባለዉ ይፈፀም ዘንድ ነዉ፡፡ ከሌሎች ተራሮች ሁሉ ደብረ ታቦርን የመረጠዉ ሌላዉም ተራራ ከመሬት እንዲርቅ የመለኮትም ምሥጢር ከሰዉ የራቀ የጠለቀ መሆኑን ለማጠየቅ ነዉ፡፡
ሌላዉ፡-

እሑድ 22 ጁን 2014

አለመግባባትን ለማሰወገድ



በመኖር ዉስጥ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በምን መልኩ መፍታት ይቻላል?
Image:Resolve Conflict in Marriage Step 8.jpg
የሰዉ ልጅ በህይወት ዘመኑ ረጅምም ይሁን አጭር፣ አስደሳችም ሆነ አሳዛኝ የሆነ ህይወን መኖሩ ግድ ነዉ፡፡በዚህ ወቅት ሁሌ መግባባቶች ብቻ ናቸዉ ብሎ ማሰብ የማይታሰብ ጉዳይ ነዉ፡፡ታዲያ አለመግባባት ካለ ይህንን አለመግባባት እንዴት መፍታት ይቻላል? ዋናዉና መሠረታዊዉ ጥያቄ ነዉ፡፡
ወደ መፍትሄዉ ከመሄዳችን በፊት እስኪ አለመግባባቶች ከምን እና ከማን ዘንድ ይፈጠራሉ የሚሉትን በጥቂቱ እንመልከት፤
ü  ባለትዳሮች (ባል ከሚስት ወይም ሚስት ከባል ጋር)
ü  ወላጆች (ቤተሰብ) ከልጆች ጋር ልጆች ከቤተሰብ/ከወላጅ ጋር፤ (ቤተሰብ በጠቅላላዉ እርስ በርስ ሠላም ዝር የማይልበት ቤት
ü  ፍቅረኞች (ወንዱ ከሴቷ ሴቷ ከወንድ ፍቅረኛዋ ጋር)
ü  ጓደኛሞች (ወንዶች ከወንዶች፣ ሴቶች ከሴቶች፣ ወንዱ ከሴት፣ ሴቷም ከወንድ ጋር ) ትንሽ በሚባሉ ችግሮች የሚፈጠሩ አለመግባባቶች
ü  መንግስትና ህዝብ (ባለመደማመጥና ባለመከባበር እኔ ነኝ የምገዛህ ወይም የማስተዳድርህ፣ አንተ አትገዛኝም ወይም አታስተዳድረኝም አለበለዚያም ወደ ሥልጣን ያመጣሁህ እኔ ነኝ … እንዳመጣሁህ አወርድሃለዉ….)
ü  መንግሥት ከመንግሥታት/ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች (በተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች እና ኃይልን ለማሳየት በሚሞከር ትንኮሳ፣ በጉርብትና፣ በድንበር ጉዳይ፣ ቅኝ ለመግዛት በማሰብ እና ላለመገዛት መወሰን፣….)
ü  መንግሥት ከተቋማት ጋር (በሪፖርት፣ በዜና እወጃ፣ ምሥጢር በማዉጣት፣ ጫና በመፍጠር ፣ ጥቅማ ጥቅሞችን በማስቀረት፣ ሌሎች ወገኖችን በማሳመፅ፣ አላስፈላጊና አወዛጋቢ አዋጆችን በማወጅ፣ ….)
ü  ወዘተ
ችግሮች የሚፈጠሩበትን አካባቢ እንዲህ በጥቂቱ ከዘረዘርን በማዕከልነት መፍትሔዎችን እንዲሁ በጥቂቱ ማንሳቱ አወያይ እና ሌሎችንም ሻል ያሉ ምፍትሔዎችን በተጠና መልኩ ያመጣሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ለጊዜዉ ጥናቱን ለባለሙያዎቹ ልተዉና ይሆናሉ የምላቸዉን እነሆ ብያለሁ፡-

እሑድ 8 ጁን 2014

ክፍል ስድስት… … … አጋጣሚ



ረጅም ዕድሜን ባልኖርም ሊደርሱብኝ የሚችሉትን አስተናግጃለሁ፣ ማየት የነበረብኝን አይቻለሁ፣ ደስታንም ሃዘንንም ከእህቴ የበለጠ አዉቃለሁ፣ ( ከእህቴ እንደምበልጥ የማረጋግጥልህ እሷ በህይወቴ ጣልቃ እየገባች አዉቅልሻለሁ ስትለኝ ይህንን ሁሉ እንደማዉቅ አለማወቋ በቂ ማረጋገጫ ነዉ፤ እስኪ እኔን ከእናቴ ፈርማ ተረክባ ቢሆን አሁን ያለሁበት ሁኔታ ለምን እንደሚዳርጋት አስበኸዋል? ) አሁን ከምነግርህ በላይ አዉቃለሁ፤ ነገር ግን እስካሁን የማዉቀዉ መጥፎ ነገሮችን ነዉ ጥሩ የተባሉትንም ቢሆን ከእርሷ የተሻለ አዉቃለሁ፡፡ የሚገርመዉ ስለግል ህይወቴ ዕድል ሳትሰጠኝ ስለ አገር ጉዳይ ቁጭ አድርጋ ታወራኛለች፤ እስኪ አስበኸዋል እኔ አሁን ስለ አገር የሚያገባኝ ሴት ነኝ የኔን ነፃነት ነፍጋኝ ዲሞክራሲ ስለጠማት እና ስለራባት አገር እኔ ምን አግብቶኝ ነዉ ከእሷ ጋር ስለ አገር ጉዳይ ለማዉራት በጠረጴዛ ዙሪያ የምሰደረዉ? ስለፍቅር እየተከለከልኩ ስለ ፖለቲካ የሚፈቀድልኝ እንዴት ነዉ ነገሩ? እኔ የሚገርመኝ ፖለቲካል ሳይንስ ታጥና ህክምና ግራ ግብት ይለኛል፡፡ ለምን አታገቢም ስትላት መጀመሪያ አገር ባለቤት ይኑራት ትልሃለች፤ ለምንድን ነዉ የራስሽ ነገር የማይኖርሽ ስትላት አሁን ጊዜዉ አይደለም ስንት አንገብጋቢ ነገር እያለ ትልሃለች፤ እሷን የሚያንገበግባት የእኔና የአገር ጉዳይ ብቻ ነዉ፡፡
ልብ በለህ ስማኝ እሷ ወንድ የምታዉቀዉ ስለፖለቲካ ጉዳይ ለማዉራትና በህክምና ሊረዳ በስራ ቦታዋ ሲመጣ ብቻ ነዉ፤ ባለፈዉ አንዱ ከቤት ድረስ ቢመጣ ሁላችን ደስ ብሎን ( መቸስ በባህላችን ሴት ልጅ ወንድ ይዛ እቤት ድረስ ስትመጣ የቱንም ያህል ደስ የማይል ጉዳይ መሆኑ ግልፅ ቢሆንም ይህ የሚያሳየዉ የጉጉታችን ልክ መጠነ ሰፊ መሆኑን ያመላክታል ) ግድግዳዉ ላይ ጆሮአችንን ለጥፈን ( አንድያዉን ለስነን ብትለዉ ይቀላል) ብናዳምጥ ብናዳምጥ አንዳች ነገር አጣንባት ከጆሮዬ ይሆን ብዬ አብራኝ የነበረችዉን የቤታችን አባል ሰራተኛይቱን ብጠይቅ እሷም እንደኔዉ ተበሳጭታ ኖሮ እሷቴ አናዳችም ስለሴትና ወንድ ያወራችዉ ነገር እንደሌለ ነገረችኝ፤ ያዉ የፈረደበትን ፖለቲካ እቤት ድረስ ይዛ መጥታ ታቦካዉ ጀመረ እንጂ፡፡ አሁን እስቲ ማን ይሙት ‹‹ የዘመናችን ብቸኛዋ ፖለቲከኛ ሴት ለመባል ነዉ ወይስ … ›› እስኪ እንደዉ ብቻ ተወኝ፤ ነገረ ዓለሙ ሁላ ፖለቲካ ፖለቲካ የሸተተበት ዘመን ላይ ደርሰን ህጻን አዋቂዉ አልጋና ትራሱ ሁሉ ፖለቲካ ሆኖ ፍቅር ጠፋ አንዴ እኔ ብገኝ በምን እናጥፋሽ ብለዉ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡
( እነማን ናቸዉ ለማለት ፈለኩና የሞቀ ወሬያችንን በኔ ጣልቃ ገብነት እንዳልገታዉ ፈራሁና እየተከታተልኳት መሆኔን አንገቴን ላይ ታች በመነቅነቅ ገለጽኩላት፤) 
ከዚህ ቀደም እንዳወራነዉ ከልጅነት ጓደኛዬ ሌላ ተባራሪዎቹን ሳንቆጥር አንድ ሶስት ወንዶችን በደንብ አዉቃለሁ፤ ነገር ግን ይህቺ ክፉ እህቴ ሁሌ ጥላዋን እያጠላችብኝ እንደዛፍ ላይ እንቅልፍ አስሬ እየባነንኩ ነበር የምኖረዉ፡፡ የመጀመሪያዉ በጣምም ሃብታም ባይባል ለኔ ከበቂ በላይ ሊይዘኝ የሚችለዉ አቅም ነበረዉ ከነበረዉ ገንዘብ ይልቅ ፍቅሩ ይግደለኝ፣ እንክብካቤዉስ ብትል፣ በተለይ በተለይ የትም ስንገባ የነበረዉ ክብር እመቤት የሆንኩ ያህል ነበር የሚሰማኝ ወንበር ስቦ አስቀምጦ፣ የመኪና በር ከፍቶ አዉርዶ አስገብቶ፣ … ስንቱን ልበልህ ከልቡ ነበር ግን ‹‹ ባሪያ ላመሉ … ›› እንደሚባል ልክስክስ ነበር፤

ሐሙስ 22 ሜይ 2014

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››

የዳንኤል እይታዎች Daniel Kibret's views: ‹‹የሚገሥጹንን ሁሉ መቅጣት የለብንም››: click here for pdf ብጹዕ አቡነ ዮሐንስ በሊቅነታቸው፣ በቆራጥነታቸው፣ ለየት ባለ አስተሳሰባቸውና ለነገሮች በሚሰጡት አስደናቂ ምላሽ የሚታወቁ የትግራይ ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ እስካሁንም እርሳቸውን በተመለከተ ...

እሑድ 18 ሜይ 2014

ክፍል አምስት … … አጋጣሚ



ከመች ወዲህ ነዉ እንዲህ ማምሸት የጀመረችዉ? ከቤት እንዳትወጣ አላልኩሽም? ለመሆኑ ስንት ሰዓት ነዉ የወጣችዉ? ቆይ ስራ በቃኝ! ለተወሰነ ግዜ ማረፍ እፈልጋለሁ ብላ ሥራዋን በገዛ ፈቃዷ የለቀቀችዉ ለመዞር ነዉ እንዴ? እንደከብት እሷን ለመጠበቅ እኔ የግድ እዚህ መዋልና ማምሸት አለብኝ? …. … (ለጥያቄዎቿ መልስ የሚመልስላት ስታጣ ብቻዋን አዉርታ አዉርታ ሲበቃት ስልኳን መደወል ጀመረች፤ ) ደግሞ ስልኳንም ዘግታዋለች፡፡
ነይ እስኪ ወደዚህ ምንድን ነዉ አላማችሁ? ቆይ እስኪ እናንተ ከብቶች ናችሁ እንዴ ያለጥበቃ የማትኖሩት? አልበዛም እንዴ? (ቁጣዋ እየጨመረ መጣ የሚሰማት ሰዉ ግን አልነበረም፤) ምን ይዘጋሻል!
‹‹ እኔን ነዉ? ››
እና ማን አለ? እስካሁን የማወራዉ ለማን መስሎሻል?
‹‹ እስካሁን አዉሪ እንጂ አንዱም አይመለከተኝም፤ … … እኔኮ የቤቱ ጠባቂ እንጂ የሰዉ ጠባቂ አይደለሁም፡፡ ቆይ እስኪ ስራዬ ምንድን ነዉ? ገረድ ነኝ ወይስ እናንተ በተበጣበጣችሁ ቁጥር ሸምጋያችሁ ነኝ? ድርሻዬን አሳዉቁኝ …. ….›› ( በዚህ ቤት ዉስጥ ለመጀመሪያ ጊዜዋ ነዉ እንዲህ አይነት ቃላት ስትናገር፤ )

ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!

መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡

የዝምታው አደጋ፡ የጋራ ቤተሰብን የመገንባት ስልቶች

  የዝምታው አደጋ፡ የጋራ ቤተሰብን የመገንባት ስልቶች በአንድ ቤተሰብ ዉስጥ መነጋገርም ሆነ መጨቃጨቅ የለም፤ በቤት ወጪ ላይም ሆነ በልጆች አስተዳደግ ላይ መወያየት የለም፡፡ ዝም ብሎ መዉጣት መግባት ብቻ ነዉ ልጆችም ...