በአንድም በሌላም እንናገራለን:ጆሮ ያለዉ ይስማ:ልብ ያለዉ ልብ ይበል፡፡ የታዘብነዉን የምንናገርበት፣ የምናዉቀዉን ለትምህርት እና ለእርምት የምናዉልበት ከወገንተኝነት ነፃ የሆነ መድረክ ነዉ፤ …ሁሌም ቢሆን አስተያየቶችን እና መልዕክቶችን ለመቀበል ዝግጁ ነን፡፡
ማክሰኞ 18 ማርች 2014
‹‹ቅዳሴ››
ያለው ዕለት ለንጋቱ ቦታውን ለመልቀቅ መሰናዶውን ያጠናቀቀ ይመስላል በቤቴ መስኮት ቀዳዳ የሚገባው የንጋት ብርሃን “ነግቷል ተነስ” የሚል ሰው ያህል ከፊት ለፊት በቀዳዳው እየገባ ይጎነትለኛል የጭላንጭሉን ብርሃን ተልዕኮ የሚያጨናግፈው ድብርት “አይዞህ ተኛ ገና ነው” እያለ ያዘናጋኛል፤ አሁንም በመስኮቱ የሚገባው የብርሃን ጭላንጭል ገብቶ ገብቶ ቤቱን በሰፊው ተቆጣጥሮታል፣ አካላቴ ሁሉ ሳምንቱን መንገድ ሲጓዝ እንደከረመ አንጓዎቼ በሙሉ የመዛል ስሜት ይሰማባቸዋል፡፡ ከሁለቱ አንደኛዋ አይኔ ብቻ ብርታት ይሰማታል እንጂ ሁለተኛዋ ጭራሽ የለችም ማለት ይችላል፤ አንደኛው ሲተኛ እርሷ ነቅታለች እርሱን ለመቀስቀስ ባደረገችው ጥረት እርሷም ድካም ተሰምቷት ማሸለብ ጀመረች የሌላት ልብሴን ገላልጣ ለመውጣት ጡንቻዋን ያፈረጠመችው ክንዴ ብርድ ሲያኮማትራት ተመልሳ ከብርድልብሱ ሾልካ ገባች ገና ተመኝታ የተገናኘች ይመስል እንቅልፍ ጣማት በዚያቹ በቀጫጫ ክንዷ ራሷን በራሷ እቅፍ አድርጋ ጋደም እንዳለች የእንቅልፍ ማዕበል ይዟት ጥርግ አለ፡፡ በልቦናዋ በብርቱው ምሽት ያሰበችው የዕለት ሰንበት የቅዳሴ መርሃግብርና ጠዋት በብርሃኑ ጭላንጭል መካከል ትዝ ያላት ልቡናዋን እንደብል በልቶ ጨርሷታል ሰውነቴ ለእንቅልፍ ተማርካ ከሞቀው መኝታዋ በመሆን ቅዳሴን ታስቀድስ ጀመር፤ ልክ ከመቅደሱ ፊት እንደቆመ አስቀዳሽ አሁን ለዛለችው ገላዬ ንፍቁ ዲቆኑ “ጸልዩ በእንተ ያበውኡ መባእ …” የሚለውን አዚሞ ሕዝቡም “ተወከፍ መባኦሙ ለአኃው” የሚለውን ጨርሶ ዲያቆኑ በድጋሜ “ስግዱ ለእግዚአብሔር በፍርሃት” ብሏል የዛለው ገላዬም “ቅድሜከ እግዚኦ ንሰግድ ወንሴብሐከ” ብላ ሰግዳለች
ደንበኛ ይሁኑ ለ፡
ልጥፎች (Atom)
ጦማሩን ስለጎበኙ አመሰግናለሁ!
መልካም ነገርን ለሌሎች ማጋራት ባህላችን እናድርግ፤ ላልደረሰዉ በማጋራት ድርሻችንን እንወጣ፡፡
-
ያለው ዕለት ለንጋቱ ቦታውን ለመልቀቅ መሰናዶውን ያጠናቀቀ ይመስላል በቤቴ መስኮት ቀዳዳ የሚገባው የንጋት ብርሃን “ ነግቷል ተነስ” የ ሚል ሰው ያህል ከፊት ለፊት በቀዳዳው እየገባ ...
-
እናቴ አትሙቺ ልሙትልሽ እኔ ከጎኔኮ ሳጣሽ ይባክናል ዐይኔ ዛሬ ዛሬ የነ ሻኪራ፡ የነ ቢዮንሴ፡ ቱፓክ፡ሮናልዶ፡ ሜሲ፡ … እና ሌሎችም ታዋቂ ሰዎች ፎቶ ገበያዉንና ቤታችንን ከማጨናነቁ በፊት፡ ከከተማዉም አል...
-
የስኬት ሚስጢር ምንድን ነው ? የስኬት ሚስጥር ለአንዱ የሚሰራው ለሌላው ሊለይ ቢችልም፣ በአብዛኛው ስኬታማ ሰዎች ህይወት ውስጥ የሚታዩ ዋና ዋና ምሰሶዎች አሉ። ስኬት በአንድ ጀምበ...
የዝምታው አደጋ፡ የጋራ ቤተሰብን የመገንባት ስልቶች
የዝምታው አደጋ፡ የጋራ ቤተሰብን የመገንባት ስልቶች በአንድ ቤተሰብ ዉስጥ መነጋገርም ሆነ መጨቃጨቅ የለም፤ በቤት ወጪ ላይም ሆነ በልጆች አስተዳደግ ላይ መወያየት የለም፡፡ ዝም ብሎ መዉጣት መግባት ብቻ ነዉ ልጆችም ...